TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የ2019 የኖቬል የሰላም ሽልማትን አሸነፉ!

የ2019ኙን የሰላም ኖቤል ሽልማት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሸነፉ፡፡ በአውሮፓዊኑ የዘመን ቀመር 1901 የተጀመረው የኖቤል ሽልማት በተለያዩ ዘርፎች ግለሰብና ድርቶችን ሲሸልም ኖኗል፡፡

በሰላም ዘርፍም የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማትን ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ በዋናነትም ለኢትዮ-ኤርትራ እርቅ ላደረጉት አስተዋፅኦ በሚል እንዳሸነፉ ሸላሚው ድርጅት ይፋ አድርጓል፡፡

ከጠ/ሚንስትሩ ጋር የማሸነፍ ግምትን የ16 ዓመቷ ስዊድናዊት የአየር ንብረት ተማጋች ግሪታ ቱምበርግ፣ ብራዚላዊው የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያ ራኦኒ ሜቱክተይር እና ‘’ሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ’’ የተባለው የመገናኛ ብዙኃን ዘርፍ ተማጋች ድርጅት የመጨረሻ እጩ ስለመሆናቸው ዓለም ዐቀፍ የመገናኛ ብዙኃን አውታሮች መረጃ አግኝተናል በማለት ሲዘግቡ ሰንብተውም ነበር፡፡ በኖርዊጂያን የኖቤል ኮሚቴ የሚሰጠው የኖቤል የሰላም ሽልማት ከሚያሰጠው ከፍ ያለ እውቅና ባሻገር 743 ሺሕ ፓወንድ እንደሚያሸልምም ይገለፃል፡፡

Via Ahadu TV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እንኳን ደስ አሎት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር!

ቪድዮ፦ ስንታየሁ/TIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንኳን ደስ አላችሁ!! እንኳን ደስ አለን!!

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የ2019 የኖቬል የሰላም ሽልማትን አሸንፈዋል፡፡ በTIKVAH-ETH ስም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን ለማለት እንወዳለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#NewsAlert

ቢሾፍቱ ከተማ /ኡኬ ደንካካ የሚባል አካባቢ አነስተኛ የጦር አውሮፕላን ተከስክሷል። አውሮፕላኑ የእህል ማሳ ላይ ነው የወደቀው። በአካባቢው ላይ አምቡላስ እንደተመለከቱም የቤተሰባችን አባላት ገልፀዋል።

Via ሮብኤል/TIKVAH-ETH/

ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሰን እናቀርባለን!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቢሾፍቱ -- ኡኬ ደንካካ!!

የአደጋው ምንክንያት ምን እንደሆነና ስለደረሰው ጉዳት ተጨማሪ መረጃዎችን እንዳገኘን እናጋራለን!

PHOTO: kira Dibenedetto/TIKVAH-ETH/
@tsevabwolde @tikvahethiopia
#Attention

ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ በሚወስደው መንገድ ልዩ ቦታው ጎሃ ፅዮን አካባቢ መንገድ ተዘግቷል። ለመንገዱ መዘጋት ምክንያቱ ምን እንደሆነ አላወቅንም የሚሉት የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች ወደመጣንበት እንድንመለስ ተነግሮናል፤ አንዳንድ መኪኖችም እየተመለሱ ይገኛሉ ብለዋል። በርካታ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ተማሪዎች በጉዞ ላይ ስለሚገኙ የሚመለከታቸው አካላት ችግሩ የሚፈታበትን መንገድ እንዲፈልጉ ጥሪ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች ጥሪ አቅርበዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#PMOEthiopia

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያገኙት የኖቤል የሰላም ሽልማት ለሰላም የተሰጠ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፅህፈት ቤቱ ባወጣው መግለጫ ይህ ለሰላም የተሰጠ ሽልማት በመሆኑም መላው ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ለሰላም እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል።

የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማትም የኢትዮጵያውያን የጋራ ድል መሆኑንም አስታውቋል። ኢትዮጵያን አዲሲቷ የተስፋ አድማስ በማድረግ የበለፀገች እንድትሆን የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የማንቂያ ጥሪ መሆኑንም ነው ያመለከተው። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የ2019 የኖቤል የሰላም ተሸላሚ በመሆን በዘርፉ 100ኛው ተሸላሚ ሆነዋል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሓፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን ተከትሎ ባስተላለፉት የደስታ መግለጫ መልዕክት፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አመራር ለአፍሪካና ለሌች አገራት ምሳሌ ነው ብለዋል፡፡ ዋና ጸሓፊው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ራዕይ በኤርትራና ኢትዮጵያ መካከል ታሪካዊ መቀራረብን ፈጥሯል ብለዋል፡፡

Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
WORLD EXCLUSIVE: Listen to the call between Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed Ali and Olav Njølstad, Secretary of the Norwegian Nobel Committee, recorded shortly after the announcement of the 2019 Nobel Peace Prize.

Via Nobel Prize
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ለጠ/ሚ አብይ የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላፉ!

ግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ በመሆናቸው የአንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላለፉ፡፡ ፕሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና ወንድም የኢትዮጵያ ህዝቦች የ2019 የኖቤል ሽልማት ዶክተር አብይ አህመድ በማሸናፈቸው እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረ "ዘመን ባስ" ተገልብጦ በሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። የደረሰውን ጉዳት አስመልክቶ ተጨማሪ መረጃዎች ሲደርሱን እናጋራለን።

Via ANANIYA/TIKVAH ETH FAMILY/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ችሎት

በነአቶ በረከት ስምዖን የክስ መዝገብ ዛሬ ከሰዓት በኋላ የተሰየመው ችሎት ዐቃቤ ሕግ ያቀረበውን ተጨማሪ ሰነድ መርምሮ የሰነዱ አካል እንዲሆን ብይን ሰጥቷል፡፡ ከፍርድ በፊት የሚቀርብ ማንኛውም ማስረጃ መርምሮ ትክክለኛ ብይን ለመስጠት አጋዥ ስለሚሆን ዐቃቤ ሕግ እንዲያዝለት ያቀረበውን 141 ገፅ ማስረጃ ከዚህ ቀደም የቀረበው የሰነድ ማስረጃ አካል እንዲሆን ሊያያዝ ይገባል ብሏል ፍርድ ቤቱ፡፡ ፍርድ ቤቱ ሰነዱን መርምሮ ብይን ለመስጠትም ለጥቅምት 21 ቀን 2012 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE

ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረ "ዘመን ባስ" ተገልብጦ በደረሰው አደጋ የ4 ሰው ህይወት ማለፉን ተመልክቻለሁ ሲል አንድ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል ገልጾልናል። በሰዓቱ ወደ ሀረር እየተጓዝኩ ነበር ያለን የቤተሰባችን አባል እኔ እያለሁ አራት ሰው መሞቱን አይቻለሁ ብሏል። ተጨማሪ የፎቶ መረጃዎችን አጋርቶናል።

Via Cheery/TIKVAH ETH FAMILY/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
መንገዱ እንደተዘጋ ነው!

አዲስ አበባን ከባህርዳርና ጎንደር የሚያገናኘው መንገድ ጎሃ ጺዮን ከተማ ላይ እንደተዘጋ ነው። በርከት ያሉ ተሽከርካሪዎችም ወደመጡበት እንዲመለሱ ተነግሯቸው ወደመጡበት መመለሳቸውን በስፍራው የሚገኙ የቤተሰባችን አባላት ገልፀዋል። ለምን ግድ መዘጋት ምክንያት የሆነውን ጉዳይ ለማጣራት ጥረት እናደርጋለን።

Via Muhamedanwar Seid/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"One Small Step to Pave a Way"
ጥቆማ!
አንተም አንቺም እኔም ያገባናል!
•በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ስለመጣው የፍቺ ቁጥር
•በትዳር ውስጥ እየታየ ስላለው እርካታና ደስታ ማጣት
•በፍቅር ህይወት የነበሩ መተሳሰቦች እና ሌሎችም በጋብቻ ውስጥ አለመቀጠል
ሁላችንንም ያገባናል!!
እነዚህና መሰል ሀሳቦች የፊታችን ቅዳሜ በ 8:00 ሰአት 6ኪሎ በሚገኘው የስብሰባ ማእከል(አሴምብሊ) ይዳሰሳሉ።

ሰላማዊ አለም እንዲኖረን ሰላማዊ ቤተሰብ እንፍጠር!

ፍኖተ-ጋብቻ

@tsegabwolde @tikvahethiopia