TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#HARAR የደመራና የመስቀል በዓል በደመቀና በሰላማዊ ሁኔታ እንዲከበር አስፈላጊ ዝግጅት ማድረጉን የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethioia
#update የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ በተመለከተ ተቀማጭነታቸውን በአዲስ አበባ ላደረጉ ዲፕሎማቶች ማብራሪያ ተሰጠ። ማብራሪያውን የሰጡት የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒሰትር ዴኤታ ወይዘሮ ሂሩት ዘመነ ናቸው፡፡

https://telegra.ph/TIKVAH-09-27

ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

@tsegabwolde @tikvahethioia
#DEBRE_MARKOS

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር የሚገኙ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የመስቀል ደመራ በዓል የሚከበርበትን የንጉሥ ተክለሃይማኖት አደባባይ አካባቢን አፅድተዋል።

በበጎ ተግባሩ ላይ የተሳተፉ የደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ወጣቶች ለክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethioia
እስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና የሃይማኖት አባቶች የመስቀል በዓል የሚከበርትን አካባቢ አጸዱ!

በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ አስተዳደር የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና የሃይማኖት አባቶች የመስቀል በዓል የሚከበርባቸውን አካባቢዎች ሲያጸዱ አርፍደዋል፡፡

በከተማዋ የቆየውንና ያለውን አብሮነት፣ መተሳሰብና አንድነት ለትውልድ ለማስተላለፍ በተግባር የአንደኛው ሃይማኖት ተከታይ ለሌላኛው ሃይማኖት ተከታይ አጋር መሆኑን ያሳዩበት ተግባር መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

ከዚህ ቀደምም #የደባርቅ_ከተማ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች በዓል ለማክበር በሚዘጋጁበት ወቅት የመስጅድና ሌሎችም የሶላት መስገጃ አካባቢዎችን ማጽዳታቸውን የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethioia
#BONGA የካፊቾ ብሔር የዘመን መለወጫ ”ማሽቃሬ ባሮ” በዓል በቦንጋ ከተማ ተከብሯል። በዞኑ ከቀበሌ ጀምሮ በሁሉም ወረዳዎች ላለፉት ሶስት ቀናት ሲከበር የቆየው ይኸው በዓል ትናንት በዞኑ ዋና ከተማ ቦንጋ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተጠናቋል።

Photo: ZELALEM/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethioia
ከአንድ አካባቢ የሚመጡ ተማሪዎችን በአንድ «ዶርም» አይመደብም!

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ለተማሪዎች ቅበላ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ገለጸ። በተቋሙ ከአንድ አካባቢ የሚመጡ ተማሪዎች በአንድ ዶርም እንደማይመደቡ ተጠቁሟል፡፡ የተማሪዎች ማደሪያ ሕንፃም ቁጥጥር የሚደረገው በትምህርት ክፍሎች አማካኝነት መሆኑ ታውቋል፡፡

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር ደረጀ አንዳርጌ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ዩኒቨርሲቲው ለ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የማደሪያ ሕንፃዎችን ለአገልግሎት ዝግጁ የሚሆኑበት ደረጃ ላይ የማድረስ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ሲሆን፤ በዚህም ባለፈው ዓመት ከነበረው ችግር የተነሳ የተጎዱ ማደሪያ ክፍሎችን የመጠገን ሥራው በመጠናቅ ላይ ይገኛል።

ከዚህም ባለፈ ምድረ ግቢውን ጽዱ የማድረግ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ጤፍና አትክልትን ጨምሮ ለተማሪዎች የምግብ ፍጆታ የሚውሉ ግብዓቶችን በማሟላት ላይም ነው ብለዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው መሠረታዊ ችግር ሊሆን የሚችለው የውሃ አቅርቦት መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፤ የውሃ እጥረትን ሊፈታ በሚችል መልኩ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን፤ መምህራንን ከማሟላት አኳያም ቅጥር እየተካሄደ መሆኑንና በሚሰጡት የትምህርት ዓይነቶች ድልድል እየተካሄደ መሆኑን፤ የማስተማሪያ ግብዓቶችም በመሟላት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
•የአፋር ህዝብ ፓርቲ
•የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ
•የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ/ኦዲፒ/
•የጋምቤላ ህዝቦች ፍትህ ለሰላምና ዴሞክራሲ ንቅናቄ

https://telegra.ph/TIKVAH-09-27-2

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና እና የስም ቅየራ የተሰጣቸው ፓርቲዎችን ለህዝብ ማሳወቅ አለበት በሚለው የህግ ድንጋጌ መሰረት ከላይ የተጠቀሱት ፓርቲዎች የስም ቅየራ እና የእውቅና ሰርተፍኬት ተሰጥቷቸዋል።

ምንጭ፦ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ማደሪያ ሕንፃ ቁጥጥር የሚደረገው በትምህርት ክፍሎች አማካኝነት እንደሆነ አስታውቋል፡፡ #DEBRE_BERHAN_UNIVERSITY

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ያዳምጡ⬆️

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በደመራ ስነ ስርዓት ወቅት በህገ መንግስቱ ከተፈቀደው ሰንደቅ ዓላማ ውጪ የተለያዩ አርማዎችን ይዞ መገኘት አይችልም ያለበትን ምክንያት ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አስረድቷል፤ ካላይ ያለውን ፋይል ከፍታችሁ ሙሉውን አድምጡ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ፦

"...በዓሉን ወደፖለቲካ ለመቀየር፤ የፖለቲካ መጠቀሚያ ለማድረግ የተዘጋጀ ኃይል አለ። ይሄንን ወደሌላ እንዳይሄድ ነው። ፖሊስ የህዝቡን ደህንነት ከመጠበቅ አንፃር ነው እየሰራ ያለው እንጂ ሌላ ምንም ትርጉም የለውም። ፌደራል ፖሊስ ፓርቲም አይደግፍም፣ብሄርም አይደግም ሃይማኖትም አይደግፍም...የለውም! እኛ ውዥንብር እንዳይፈጠር ችግር እንዳይፈጠር ነው። አንድ ብሄራዊ ሰንደቅ አላማ ይዞ ይሄ ሀገር አቀፍ በዓል ነው። በአለም አቀፍ ደረጃም ተቀባይነት ያለው በዓል ነው። በጥሩ ሁኔታ በድምቀት የለምንም ልዩነት በሰላም እንዲጠናቀቅ ነው፤ ረብሽ ሳይነሳ እንዲጠናቀቅ ነው።...እኛ ጥንቃቄ ከማድረግ አንፃር ነው። እንዴት እኛ ሃይማኖት ውስጥ ገብተን የሃይማኖት ጉዳይ እንከለክላለን? ፖሊስ ያውቃል የሃማኖት ነገር የቱ ነው፤ የሃይማኖት ያልሆነው የቱ ነው የሚለውን በደንብ ነው የሚያውቀው። ፖለቲካ እና ሃይማኖት መቀላቀል የለበትም። ለፖለቲካ አርማ የሚጠቀሙትን እዛው ፖለቲካ ቦታ ይውሰዱ ፤ ረብሽ ማስነሺያ ስለሆነ ነው። ማቀጣጠያ ነው። የቤተክርስቲያንን አርማ አልነካንም እኛ ቤተክርስቲያን የራሷ አርማ አላት እዛ ውስጥ አልገባንም። "

@tsegabwolde @tikvahethioia
ከጅማ⬆️

"ዛሬ በጅማ በሰማ አካባቢ ልጆች አስተባባሪነት የደም ልገሳ ፕሮግራም እየተካሄደ ነው፤ በጣም ብዙ ሰው ደም ለግሷል። በተለይ የአካባቢው ወጣት፣ ሴት ወንድ ሳይል ብዙ ሰው ተሳትፏል። ለመላው የእርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የመስቀል ደመራ በዓል እንዲሆንም እንመኛለን!"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#DebreTabor

የደብረ ታቦር ከተማ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች የመስቀል በዓል የሚከበርበትን የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ አደባባይን ዛሬ አጽድተዋል። ‹‹የእስልምና ሃይማኖት ከክርስትና ሃይማኖት ጋር አብሮ የኖረ እና የተዛመደ በመሆኑ አብሮነታችንን ለመግለፅ የጽዳት ሥራውን አከናውነናል›› ብለዋል። ‹‹አንዳንድ አካላት የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖትን በማጋጨት የራሳቸውን የፖለቲካ አጀንዳ ለማስተላለፍ ቢጥሩም አብሮነታችንን ከጥንት ጀምሮ የቆየ በመሆኑ ሊነጣጥሉን አይችሉም›› የሚል መልዕክትም አስተላልፈዋል።

ባለፈው የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች በዓል በሚያከብሩበት ወቅት የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች መስጅድ እና የመስገጃ ቦታዎችን ማጽዳታቸው የሚታወስ ነው።

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"...ምንም የተደበቀ ዓላማ የለውም!" የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን
.
.
ትላንት መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ.ም በሚዲያ አማካኝነት የተሰራጨው ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የራሷ አርማና ሎጎ መያዝ አትችልም አላልንም እኛ ያልነው የኢትዮጵያ ህዝብ ያልተግባበት የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አርማ ይዞ መምጣት አይቻልም ነው ያልነው። ምክንያቱም በዓሉ የሀይማኖት መሆኑ ቀርቶ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተጠልፎ የፖለቲካ አጀንዳ መጠቀሚያ ሆኖ ወደ ግጭት እንዳያመራ ነው። ይህንን ታላቅ በዓል በርካታ የዓለም ሚዲያዎች የሚዘግቡት ስለሆነ መንገዱን ስቶ ገጽታችንን ማበላሸት የለበትም ፣ ወደ ግጭት የሚያመሩ ነገሮች ሁሉ ይወገዱ፤ ህዝበ ክርስቲያን ይህንን በዓል በድምቀት አክብሮ አምላኩን አመስግኖ በደስታ ያለምንም የፀጥታ ችግር ወደ ቤቱ እንዲመለስ ነው። ከዚህ ውጭ ምንም የተደበቀ ዓላማ የለውም።

ፖሊስ ለሰላም፤ ሰላም ለሁሉም!

ETHIOPIAN FEDERAL POLICE COMMISSION

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ሽጉጥና ልዩ ልዩ ድምፅ የሌላቸው መሳሪያዎች በትናንትናው ዕለት መያዛቸውን ፖሊስ አስታወቀ!

በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ በመንገድ ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ሽጉጥና ልዩ ልዩ ድምፅ የሌላቸው መሳሪያዎች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመጣመር በምሽቱ ክፍለ ጊዜ በአስሩም ክፍለ ከተሞች ድንገተኛ የመንገድ ላይ ፍተሻ አድርጓል፡፡

በዚህም በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ልዩ ስፍራው ሳሪስ አቦ አካባቢ ዓይነቱ ካሪና የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2-69099 አ.አ መኪና ውስጥ 8 ስታር ሽጉጦች ከአምስት ተጠርጣሪዎች ጋር ተይዟል፡፡ በተመሳሳይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ከ12 ግለሰቦች ላይ 3 ገጀራ፣ 12 ጩቤ እንዲሁም ዓይነቱ ቪትዝ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2B-36293 አ.አ ተሽከርካሪ ውስጥ 1300 የአሜሪካ ዶላር መያዙን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

በህገ-ወጥ ተግባሩ ላይ የተሳተፉ ግለሰቦችን ጉዳይ እያጣራ መሆኑን ኮሚሽኑ አስታውቆ ህብረተሰቡ የፀጥታ ጉዳይ የጋራ ጉዳይ መሆኑን በመረዳት በፍተሻ ወቅት ላደረገው ከፍተኛ ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡ ይኸው የህብረተሰቡ ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ኮሚሽኑ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

Via Addis Abeba Police Commission
@tsegabwolde @tikvahethioia
#AAWSA

በቀን 40 ሺህ ሜትር ኪዩብ ውሃ የሚያመርተው የለገዳዲ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ በኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ምክንያት ከትናንት ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ አለመሆኑን የአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

በመሆኑም ቦሌ አራብሳ፣ ቦሌ አያት (1፣ 2፣ 3፣ እና 4)፣ ሰሚት ኮንዶሚኒየም፣ አያት፣ የካ አባዶ፣ የካ ጣፎ እና ኮተቤ ገብርዔል አካባቢ ላሉ ደንበኞቹ ውሃ ማሰራጨት አለመቻሉን የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን የስራ ሂደት መሪ ሰርካለም ጌታቸው ተናግረዋል፡፡

የኢ/ኤ/ አ ለተፈጠረው የትራንስፎርመር ችግር መፍትሄ ለመስጠት እየሰራሁ ነው ቢልም እስካሁን ለችግሩ እልባት መስጠት አለመቻሉን የተናገሩት ወይዘሮ ሰርካለም ጌታቸው የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጡ በዚህ ወር በተደጋጋሚ የተከሰተ መሆኑንም አክለው ገልፀዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
እፀገነት አንተነህ⬆️ "የ27 አመቷ የአየር መንገድ ሒሳብ ሰራተኛ እፀገነት አንተነህ ትናንት ማክሰኞ ጠዋት ወደ ሰራ በምታመራበት ወቅት #ጭካኔ በተሞላበት ወንጀል አቃቂ መንገድ ላይ ተገድላ ተጥላ ተገኘች። ፓሊስ ምርመራ ላይ ነው። ቀብሯ ዛሬ ተፈፅሟል። ቀለበት አድርጋ ሰርግ ለመደገስ ዝግጅት ላይ ነበረች።" ጋዜጠኛ ተስፋዬ ጌትነት/#CAPITAL/ @tsegabwolde @tikvahethiopia

እፀገነትን የገደሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የነበረችውን ወ/ሮ እፀገነት አንተነህን የገደሉ ሦስት #ተጠርጣሪዎች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ወ/ሮ እፀገነት አንተነህ መስከረም 6 ቀን 2012 ዓ.ም በግምት ከጠዋቱ 12 ሰዓት 30 አቃቂ ቃሊት ክፍለ ከተማ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ወደ ስራ ለመሄድ ትራንስፖርት በመጠበቅ ላይ እንዳለች ሦስቱ ተጠርጣሪዎች ወንጀል ለመፈፀም አቅደው የትራንስፖረት አገልግሎት የሚሰጡ በማስመሰል ሟችን በባጃጅ ተሽከርካሪ ከሳፈሯት በኋላ አንቀው እንደገደሏት ተጠርጥረዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ የሟችን አስክሬን በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሰላም ፍሬ ጤና ጣቢያ አካባቢ መንገድ ላይ ጥለዋት እንደተሰወሩ ነው ፓሊስ የገለፀው፡፡ ወንጀሉን የፈፀሙ ግለሰቦች አለመታወቁ የፖሊስን ስራ እጅግ አስቸጋሪ ቢያደርገውም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀሉ ከተፈፀመ ጀምሮ ቀንና ሌሊት ባደረገው ከፍተኛ ክትትል ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በዘጠነኛው ቀን በትናትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በርካታ የአካባቢው ሰዎችና የሟች ቤተሰቦች በተገኙበት መስከረም 16 ቀን 2012 ዓ/ም ወንጀሉን እንዴት እንደፈፀሙት መርተው አሳይተዋል፡፡

ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ፒያሳ አካባቢ በአንድ ግለሰብ ላይ የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦችን በአጭር ጊዜ ውስጥ መያዙን አስታውሷል፡፡ ህብረተሰቡም ወንጀለኞችን አጋልጦ በመስጠት እና ምስክር በመሆን እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አድንቆ ይህንኑን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አቅርቧል፡

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸እፀገነትን የገደሉት ሦስት ተጠርጣሪዎች ወንጀሉን እንዴት እንደፈፀሙ መርተው አሳይተዋል፡፡ #AddisAbeba
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ እነዚህን #ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ለማዋል ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ከፍተኛ ክትትል እንዳደረገና፤ ሦስቱን ወንጀል ፈፃሚዎች ወንጀሉን በፈፀሙ በዘጠነኛው ቀን መስከረም 15 ቀን 2012 ዓ/ም በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ገልጿል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸እፀገነትን የገደሉት ተጠርጣሪዎች ወንጀሉን እንዴት እንደፈፀሙ መርተው ባሳዩበት ወቅት በርካታ የአካባቢው ሰዎችና የሟች ቤተሰቦች ተገኝተው ነበር።

Photo: Addis Abeba Police Commission

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸በትላንትናው ዕለት የጅማ ከተማ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች አሁን የመስቀል ደመራ የተከናወነ የሚገኝበትን ቦታ አፅድተዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸በጅማ ከተማ የደመራ በዓል ስነ ስርዓት #ሰላማዊ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ይገኛል። በስፍራው የሚገኙ የበዓሉ ተሳታፊዎች ያለውን ድባብ በፎቶ አስደግፈው ልከውልናል።

PHOTO: MILVER/TIKVAH-ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸በዛሬው ዕለት በዓዲግራት ከተማ እየተከበረ ያለው #ደማቅ የመስቀል በዓል ምክንያት በማድረግ የተካሄደው ታላቅ ሩጫ #መስቀል_ዓጋመ #ADIGRAT #ETHIOPIA

PHOTO: JOHN/TIKVAH-ETHIOIA
@tsegabwolde @tikvahethioia