አርባምንጭ⬆️
በአሁን ሰዓት በአርባ ምንጭ ከተማ ደማቅ የሆነ የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል። የቀድሞ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ በሩጫው ተሳትፈዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአሁን ሰዓት በአርባ ምንጭ ከተማ ደማቅ የሆነ የሩጫ ውድድር እየተካሄደ ይገኛል። የቀድሞ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ በሩጫው ተሳትፈዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
"አርባ ምንጭ የዛሬው የ8 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ መድረሻውን አምዩ አባያ ካምፓስ አድርጎ የተለያዩ ዝግጅቶች እየተከናወኑ ነው። ብዙ እንግዶችም የተገኙ ሲሆን የቀድሞው የኢፌድሪ ቀዳማዊት እመቤት ሮማን፣ አትሌት መሀመድ አማን እና ሌሎችም ተገኝተዋል" መባ/ከአርባ ምንጭ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ/
ፎቶ: MEBA እና የጋሞ ዞን ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: MEBA እና የጋሞ ዞን ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
አርባ ምንጭ⬆️
"በአሁን ሰዓት የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው አርባ ምንጭ ተገኝተዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል" #MEBA
ዮ...ዮ ማስቃላ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በአሁን ሰዓት የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳው አርባ ምንጭ ተገኝተዋል። ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ ንግግር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል" #MEBA
ዮ...ዮ ማስቃላ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
በአርባ ምንጭ በተካሄደው የ8 ኪሎ ሜትር ሩጫ አሸናፊዎቹ ተለይተው ታውቀዋል፦
1ኛ. አልብሶ ማላ ... ከደቡብ ፖሊስ
2ኛ. እርገጤ ኤሌ... በግል
3ኛ. ልዑል ወልዴ ... በግል አሸንፈዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1ኛ. አልብሶ ማላ ... ከደቡብ ፖሊስ
2ኛ. እርገጤ ኤሌ... በግል
3ኛ. ልዑል ወልዴ ... በግል አሸንፈዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
አዲስ አበባ⬆️
የኢትዮጵያ ጦማሪያን መድረክ በአሁን ሰዓት በስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ይህ መርኃግብር የኢትዮጵያ ጦማሪያንን አቅም ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ ነው፡፡ በመድረኩ ከተለያዩ ሀገራት የተገኙ ሰዎች ልምዳቸውን በማካፈል ላይ ይገኛሉ፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጦማሪያን መድረክ በአሁን ሰዓት በስካይ ላይት ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ይህ መርኃግብር የኢትዮጵያ ጦማሪያንን አቅም ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀ የስልጠና መድረክ ነው፡፡ በመድረኩ ከተለያዩ ሀገራት የተገኙ ሰዎች ልምዳቸውን በማካፈል ላይ ይገኛሉ፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
«ክልሎች ባልተጠና መልኩ ሕገወጥ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ መጀመራቸውም አስግቶኛል›› የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
በአራት ክልሎች በመገንባት ላይ የሚገኙ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች እንደሚተላለፉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። «ክልሎች ባልተጠና መልኩ ሕገወጥ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ መጀመራቸውም አስግቶኛል›› ብሏል።
በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተቀናጀ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ አያልነህ አባዋ በተለይ እንዳስታወቁት፣ ግብርናውን ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር ከጥምረቱ ፍሬ ተጠቃሚ ለመሆን በ2009 ዓ.ም የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ተጀምሯል። ለዚህም 17 ቀጣናዎች የተለዩ ሲሆን፣ በፓይለት ፕሮጀክት ደረጃ የጥሬ ዕቃዎች ምርት መገኛ መሆናቸውን መሠረት በማድረግ የመጀመሪያዎቹ ፓርኮች ግንባታ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይና በደቡብ ክልል ተግባራዊ ተደርጓል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24-2
በአራት ክልሎች በመገንባት ላይ የሚገኙ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በታኅሣሥ መጨረሻ ለባለሀብቶች እንደሚተላለፉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ። «ክልሎች ባልተጠና መልኩ ሕገወጥ የኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ መጀመራቸውም አስግቶኛል›› ብሏል።
በንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተቀናጀ የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ አያልነህ አባዋ በተለይ እንዳስታወቁት፣ ግብርናውን ከኢንዱስትሪ ጋር በማስተሳሰር ከጥምረቱ ፍሬ ተጠቃሚ ለመሆን በ2009 ዓ.ም የአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርክ ግንባታ ተጀምሯል። ለዚህም 17 ቀጣናዎች የተለዩ ሲሆን፣ በፓይለት ፕሮጀክት ደረጃ የጥሬ ዕቃዎች ምርት መገኛ መሆናቸውን መሠረት በማድረግ የመጀመሪያዎቹ ፓርኮች ግንባታ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በትግራይና በደቡብ ክልል ተግባራዊ ተደርጓል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24-2
September 24, 2019
#UPDATE ከባድ ተሽከርካሪ የባቡር ሃዲድ ጥሶ መግባቱን ተከትሎ ተቋርጦ የነበረው የአዲስ አበባ ቀላል ተሽከርካሪው በመነሳቱ የአካባቢው ትራንስፖርት ስምሪት ወደ ነበረበት ተመልሷል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
Photo: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም
Photo: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
በራይድ እና ዛይ ራይድ መካከል ውዝግብ ተነስቷል!
በራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት እና ዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መካከል ከንግድ ስም ባለቤትነት እና ከፈጠራ ባለቤትነት መብቶች ጋር በተያያዘ በተነሳው ውዝግብ ራይድ ባቀረበው አቤቱታ መሰረት በንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ምርመራ ተጀመረ።
ከአራት ወራት በፊት ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት የስያሜው የባለቤትነት መብት ይገባኛል በሚል ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት እና ለንግድ ውድድር እና ሸማቾች መብት ጥበቃ ባለሥልጣን ማመልከቻ ማስገባቱን ተከትሎ ነው ምርመራው የተጀመረው።
‹‹ራይድ›› የሚለው ቃል በራሱ አገልግሎትን የሚያመላክት ገላጭ ቃል እንጂ ስያሜ መሆን የሚችል ቃል አይደለም ያሉት የዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀብታሙ ታደሰ፣ ከራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት ከአንድ ዓመት ቀድመው ወደ ሥራ መግባታቸውን እና በዘርፉ መጀመሪያው መሆናቸውንም ይናገራሉ።
‹‹የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ለራይድ ከአንድ ዓመት በፊት የንግድ ስያሜ ባለቤትነት ማረጋገጫ መፍቀዱ አግባብ ያልሆነ መሆኑን እያወቅን፣ ያለው ገበያ ሰፊ መሆኑን ተከትሎ አብሮ ለመሥራት እና ለመነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም›› ሲሉም ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግረዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24-3
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት እና ዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መካከል ከንግድ ስም ባለቤትነት እና ከፈጠራ ባለቤትነት መብቶች ጋር በተያያዘ በተነሳው ውዝግብ ራይድ ባቀረበው አቤቱታ መሰረት በንግድ ውድድር እና ሸማቾች ጥበቃ ባለሥልጣን ምርመራ ተጀመረ።
ከአራት ወራት በፊት ራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት የስያሜው የባለቤትነት መብት ይገባኛል በሚል ለኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት እና ለንግድ ውድድር እና ሸማቾች መብት ጥበቃ ባለሥልጣን ማመልከቻ ማስገባቱን ተከትሎ ነው ምርመራው የተጀመረው።
‹‹ራይድ›› የሚለው ቃል በራሱ አገልግሎትን የሚያመላክት ገላጭ ቃል እንጂ ስያሜ መሆን የሚችል ቃል አይደለም ያሉት የዛይ ራይድ ሜትር ታክሲ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀብታሙ ታደሰ፣ ከራይድ ትራንስፖርት አገልግሎት ከአንድ ዓመት ቀድመው ወደ ሥራ መግባታቸውን እና በዘርፉ መጀመሪያው መሆናቸውንም ይናገራሉ።
‹‹የኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ጽሕፈት ቤት ለራይድ ከአንድ ዓመት በፊት የንግድ ስያሜ ባለቤትነት ማረጋገጫ መፍቀዱ አግባብ ያልሆነ መሆኑን እያወቅን፣ ያለው ገበያ ሰፊ መሆኑን ተከትሎ አብሮ ለመሥራት እና ለመነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም›› ሲሉም ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ ተናግረዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24-3
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
#አርባምንጭ
የደቡብ ብ/ብ/ክ/መ ምክትል ርዕሰ መስተደድር አቶ ርዕስቱ ይርዳው፣ የመከላከያ ሚኒስተር ደኤታ አምባሳደር ሌላዓለም ገ/ዮሐንስ፣ የቀድሞ ቀዳማዊትእመቤት ሮማን ተስፋዬ እና የጋሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ በዮ ጋሞ ማስቃላ በዓል ላይተገኝተዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደቡብ ብ/ብ/ክ/መ ምክትል ርዕሰ መስተደድር አቶ ርዕስቱ ይርዳው፣ የመከላከያ ሚኒስተር ደኤታ አምባሳደር ሌላዓለም ገ/ዮሐንስ፣ የቀድሞ ቀዳማዊትእመቤት ሮማን ተስፋዬ እና የጋሞ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ በዮ ጋሞ ማስቃላ በዓል ላይተገኝተዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
#አርባምንጭ
በወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ #ዳጋቶ_ኩምቤ የተመራ ከፍተኛ አመራር በጋሞ "ዩ-ማስቃላ" ክብረ-በዓል ላይ ለመታደም አርባ ምንጭ ከተማ ገብቷል፡፡ አመራሮቹ አርባ ምንጭ ሲገቡ የጋሞ ዞን አስተዳዳሪ ደማቅ አቀባበል አደርገውላቸዋል፡፡ የሁለቱም ዞን አስተዳዳሪዎች የሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ የተገለፀ ሲሆን በህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ዙሪያ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡ የጋሞ ዞን አቻቸው በተመሣሣይ በወላይታ የጊፋታ በዓል ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
Via #GMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ #ዳጋቶ_ኩምቤ የተመራ ከፍተኛ አመራር በጋሞ "ዩ-ማስቃላ" ክብረ-በዓል ላይ ለመታደም አርባ ምንጭ ከተማ ገብቷል፡፡ አመራሮቹ አርባ ምንጭ ሲገቡ የጋሞ ዞን አስተዳዳሪ ደማቅ አቀባበል አደርገውላቸዋል፡፡ የሁለቱም ዞን አስተዳዳሪዎች የሁለቱን ወንድማማች ህዝቦች ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰሩ የተገለፀ ሲሆን በህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱ ዙሪያ እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡ የጋሞ ዞን አቻቸው በተመሣሣይ በወላይታ የጊፋታ በዓል ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
Via #GMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
#ETHIOPIA|"የሐሰት ወሬ፣ የግጭት ቅስቀሳ፣ የብሔር ጥላቻ፣ በየኮሌጆቹ በየማህበራዊ ሚዲያዎቹ ይልካሉ፡፡ እርስ በርሳችሁ እንድትጠራጠሩ፣ #እንድትከፋፈሉና እንድትበጣበጡ ያደርጋሉ፡፡ በመጨረሻም በገዛ እጃችን ወደ ቆፈሩልን ጉድጓድ ሰተት ብለን እንገባለን። እነርሱ ምንም አይሆኑም። በድኻው ልጅ ሕይወትና ሕልም ግን ይጫወታሉ። ተዋጉ ብለው ከቢጤዎቻቸው ጋር #በግፍ በሰበሰቡት ገንዘብ ራት ይገባበዛሉ።" ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
’"የግብጽ አዲስ ሀሳብ የድርድር ጭብጥ የለውም" ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ
.
.
‹‹ግብጽ በድርድር ስም በቅርቡ ያቀረበችው ‹አዲስ ሀሳብ› የድርድር ጭብጥ የለውም›› ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ፕሮፌሰርና የውሃ ፖለቲካ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ አስታወቁ። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ ለልማት ማዋልን ዋና ጉዳይ አድርጎ መስራቱም መዘንጋት እንደሌለበት ገልፀዋል። ፕሮፌሰር ያዕቆብ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፤ ግብጽ ከግድቡ አሞላልና አለቃቀቅ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ይዛ የቀረበችው ‹‹አዲስ›› ሀሳብ በአንድ ወይም በሌላ መልኩ የተለመደ ነው። ‹‹የግብጽ ሀሳብ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የሚያስከትለው የረባ ተጽእኖ ይኖራል ብዬ አላስብም›› ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ኢትዮጵያም ሱዳንም የአሁኑን የግብጽ ሀሳብ ያልተቀበሉበት ምክንያት ሀሳቡ የድርድር ጭብጥ የሌለው መሆኑን በጥብቅ በመገንዘባቸው ይመስለኛል ሲሉ ተናግረዋል።
Via አዲስ ዘመን ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
‹‹ግብጽ በድርድር ስም በቅርቡ ያቀረበችው ‹አዲስ ሀሳብ› የድርድር ጭብጥ የለውም›› ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ክፍል ፕሮፌሰርና የውሃ ፖለቲካ ተመራማሪ ፕሮፌሰር ያዕቆብ አርሳኖ አስታወቁ። የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ ለልማት ማዋልን ዋና ጉዳይ አድርጎ መስራቱም መዘንጋት እንደሌለበት ገልፀዋል። ፕሮፌሰር ያዕቆብ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፤ ግብጽ ከግድቡ አሞላልና አለቃቀቅ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ይዛ የቀረበችው ‹‹አዲስ›› ሀሳብ በአንድ ወይም በሌላ መልኩ የተለመደ ነው። ‹‹የግብጽ ሀሳብ በህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ የሚያስከትለው የረባ ተጽእኖ ይኖራል ብዬ አላስብም›› ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ ኢትዮጵያም ሱዳንም የአሁኑን የግብጽ ሀሳብ ያልተቀበሉበት ምክንያት ሀሳቡ የድርድር ጭብጥ የሌለው መሆኑን በጥብቅ በመገንዘባቸው ይመስለኛል ሲሉ ተናግረዋል።
Via አዲስ ዘመን ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
"የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በአገሪቱ ዩኒቨርስቲዎች ለሚማሩ ተማሪዎች በ2012 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለመፍጠር የተማሪዎች የግቢ ደህንነት አጠባበቅ ስርዓት በተሪዎች፣ በወላጆች እና በዩኒቨርሲቲ መካከል የሚገባ የኃላፊነት መውሰጃ ውል ከትምህርት መምሪያ የሚገኝ በመሆኑ የሚጠበቅባችሁን በማሟላት ፎርሙን በመሙላት እንድትወስዱ እናሳውቃለን።" የባህር ዳር ከተማ ትምህርት መምሪያ
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
#UPDATE የትምህርት ሚኒስቴር በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ያሰባሰቡትን የመማሪያ ቁሳቁሶች ለየክልሉ ትምህርት ቢሮ ያስረከቡ ሲሆን የየክልሉ ትምህርት ቢሮም ኃላፊነቱን ተረክቦ በ2011 ዓ.ም በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ትምህርታቸው ለተስተጓጎለባቸው ተማሪዎች እንደሚያስረክብ አስታውቋል፡፡ በዚህ ተግባር ለተሳተፉ ሁሉ ትምህርት ሚኒስቴር ምስጋናውን ገልጿል፡፡ ቲክቫህ ኢትዮጲያም ሥራውን እየተከታተለ ሲያሳውቃችሁ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
#መደመር
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ”መደመር” በሚል ርዕስ ያዘጋጁት አዲስ መጽሐፍ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ በአማርኛ እና በኣፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ለገበያ እንደሚውል ተሰምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር ፍልስፍና ይዘው ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ጽፈውታል የተባለው ይህ መጽሐፍ ህትመቱ የተጠናቀቀ ሲሆን ገቢው በገጠር ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ይውላል። በሦስት መቶ ብር ወይም በ 30 የአሜሪካን ዶላር ለገበያ የሚውለው ይህ መጽሐፍ 365 ገፆች ሲኖሩት በ16 ምዕራፎች የተከፋፈለ ነው።
Via #ADDISMALEDA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ”መደመር” በሚል ርዕስ ያዘጋጁት አዲስ መጽሐፍ በሳምንታት ጊዜ ውስጥ በአማርኛ እና በኣፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ለገበያ እንደሚውል ተሰምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመደመር ፍልስፍና ይዘው ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ጽፈውታል የተባለው ይህ መጽሐፍ ህትመቱ የተጠናቀቀ ሲሆን ገቢው በገጠር ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ይውላል። በሦስት መቶ ብር ወይም በ 30 የአሜሪካን ዶላር ለገበያ የሚውለው ይህ መጽሐፍ 365 ገፆች ሲኖሩት በ16 ምዕራፎች የተከፋፈለ ነው።
Via #ADDISMALEDA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
አርቲስት መሉዓለም/ሙሌ/ በቅርቡ ወደ ህንድ ይጓዛል፤ እህቱም ኩላሊት ትለግሳለች ተብሏል!
በሀበሻ ዊክሊ አስተባባሪነት ለአርቲስት ሙሉዓለም(ሙሌ) የህክምና ወጪ የፊታችን ቅዳሜ መስከረም 17/2012 ዓ/ም በሞዛይክ ሆቴል ለሚካሄደው "ለጋሽ ነኝ" ኮንሰርት የመግቢያ ዋጋ መደበኛ፦ 300 ብር፣ ቪአይፒ፦ 500 ብር ሲሆን ትኬት ሽያጩ ከዛሬ ጀምሮ ይጀምራል ሙሉዓለም ለህክምና በቅርቡ ወደ ህንድ ሀገር ይጓዛል በምነው ሸዋ የተከፈተው ትክክለኛው ጎፈንድሚ እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ 27000$ ደርሷል ተብሏል፡፡
ትኬቱ የሚገኝባቸው ቦታዎች፦
ኤድናሞል፣ መድሀኒያለም ሞል፣ ማፊ ሲቲ ሞል፣ጎላጎል ታወር፣ ዘፍመሽ፣ አቻሬ ጫማ፣ ሞዛይክ ሆቴል፣መድሀኒያለም ህንፃ የሀበሻ ዊክሊ ቢሮ ከዛሬ 9:00 ጀምሮ ይሸጣል።
ምንጭ፦ ዋልተንጉስ ዘሸገር/ከዳሰሳ አዲስ የተገኘ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሀበሻ ዊክሊ አስተባባሪነት ለአርቲስት ሙሉዓለም(ሙሌ) የህክምና ወጪ የፊታችን ቅዳሜ መስከረም 17/2012 ዓ/ም በሞዛይክ ሆቴል ለሚካሄደው "ለጋሽ ነኝ" ኮንሰርት የመግቢያ ዋጋ መደበኛ፦ 300 ብር፣ ቪአይፒ፦ 500 ብር ሲሆን ትኬት ሽያጩ ከዛሬ ጀምሮ ይጀምራል ሙሉዓለም ለህክምና በቅርቡ ወደ ህንድ ሀገር ይጓዛል በምነው ሸዋ የተከፈተው ትክክለኛው ጎፈንድሚ እስከ ዛሬዋ እለት ድረስ 27000$ ደርሷል ተብሏል፡፡
ትኬቱ የሚገኝባቸው ቦታዎች፦
ኤድናሞል፣ መድሀኒያለም ሞል፣ ማፊ ሲቲ ሞል፣ጎላጎል ታወር፣ ዘፍመሽ፣ አቻሬ ጫማ፣ ሞዛይክ ሆቴል፣መድሀኒያለም ህንፃ የሀበሻ ዊክሊ ቢሮ ከዛሬ 9:00 ጀምሮ ይሸጣል።
ምንጭ፦ ዋልተንጉስ ዘሸገር/ከዳሰሳ አዲስ የተገኘ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
ያሆዴ መስቃላ!
በሃዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የ"ያሄዴ ማስቃላ" በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። የአከባበር ስነ ስርዓቱ በሀገሪቱ ዋናው የቴሌቪዥን ጣቢያ ኢቲቪ በቀጥታ እየተሰራጨ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሃዲያ ዞን ሆሳዕና ከተማ የ"ያሄዴ ማስቃላ" በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። የአከባበር ስነ ስርዓቱ በሀገሪቱ ዋናው የቴሌቪዥን ጣቢያ ኢቲቪ በቀጥታ እየተሰራጨ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
የኢትዮጵያ ጦማሪያን ፎረም⬆️
#በዩኔስኮ አዘጋጅነት በስካይ ላይት ሆቴል እየተዘጋጀ በሚገኘው በዚህ መድረክ ላይ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ እንዴት ሀሰተኛ መረጃዎችን ልናጣራ እንችላለን በሚል በ Cayley Clifford(ከአፍሪካ ቼክ) አቅራቢነት መነሻ ኃሳብ ተነስቶ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በከሰዓቱ መርኃግብር ደግሞ በኢትዮጵያ የጦማርያን አሶሴሽን በማቋቋም ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#በዩኔስኮ አዘጋጅነት በስካይ ላይት ሆቴል እየተዘጋጀ በሚገኘው በዚህ መድረክ ላይ በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ እንዴት ሀሰተኛ መረጃዎችን ልናጣራ እንችላለን በሚል በ Cayley Clifford(ከአፍሪካ ቼክ) አቅራቢነት መነሻ ኃሳብ ተነስቶ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ በከሰዓቱ መርኃግብር ደግሞ በኢትዮጵያ የጦማርያን አሶሴሽን በማቋቋም ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
#AddisAbeba
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሪሽን /ኢሠማኮ/ የአሠሪዎች ኮንፌዴሬሽን እና የኢንዱስትሪ አሰሪዎች ፕሬዚዳንቶች፣ የህዝብ ተወካዮች እና የተለያዩ የሲቪክ ማህበራት እና ጋዜጠኞች በተገኙበት በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሠራተኛ ሚናና መርሆች በሚል ርዕስ ወይይት በመደረግ ላይ ይገኛል።
Via Assefa/#TIKVAH_ETHIOPIA/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሪሽን /ኢሠማኮ/ የአሠሪዎች ኮንፌዴሬሽን እና የኢንዱስትሪ አሰሪዎች ፕሬዚዳንቶች፣ የህዝብ ተወካዮች እና የተለያዩ የሲቪክ ማህበራት እና ጋዜጠኞች በተገኙበት በመጪው ሀገራዊ ምርጫ ላይ የሠራተኛ ሚናና መርሆች በሚል ርዕስ ወይይት በመደረግ ላይ ይገኛል።
Via Assefa/#TIKVAH_ETHIOPIA/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
September 24, 2019
የሲዳማ ሁኔታ ምክክር በሐዋሳ ከተማ!
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ከመስከረም 7-9 ቀን 2012 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘውን አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ እና ራዕይ ተከትሎ በኮሚሽኑ ውስጥም ስለሚደረገው የለውጥ መርሃ-ግብር ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ለማድረግ ሲሆን፤ በዚሁ አጋጣሚም በሐዋሳ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ድንገተኛ ጉብኝት በማድረግ በቅርቡ ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ እስረኞችንና የአያያዛቸውን ሁኔታ ጐብኝተዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24-4
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ከመስከረም 7-9 ቀን 2012 ዓ.ም በሐዋሳ ከተማ የሥራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ የጉብኝቱ ዋና ዓላማ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘውን አዲስ የፖለቲካ ምዕራፍ እና ራዕይ ተከትሎ በኮሚሽኑ ውስጥም ስለሚደረገው የለውጥ መርሃ-ግብር ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ለማድረግ ሲሆን፤ በዚሁ አጋጣሚም በሐዋሳ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት ድንገተኛ ጉብኝት በማድረግ በቅርቡ ተከስቶ በነበረው ግጭት ምክንያት በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ እስረኞችንና የአያያዛቸውን ሁኔታ ጐብኝተዋል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-09-24-4
September 24, 2019