TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የዘጠኙ ተጠርጣሪዎች ዋስትና ታገደ!

የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሀዋሳ ከተማና በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ተከስተው የነበሩ ሁከቶችን አስተባብረዋል ለተባሉ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች የስር ፍርድ ቤት የፈቀደውን ዋስትና አገደ። ፍርድ ቤቱ የእግድ ትዕዛዙን የሰጠው ፖሊስ ዋስትናውን በመቃወም ያቀረበውን የይግባኝ አቤቱታ በመቀበል ነው።

በእነ ታሪኩ ለማ መዝገብ የተጠረጠሩ ዘጠኝ ሰዎችን የጊዜ ቀጠሮ ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለተጠርጣሪዎች የዋስትና መብት የፈቀደው ባለፈው አርብ ነሐሴ 10 በዋለው ችሎት ነው። ፍርድ ቤቱ እያንዳንዳቸው ተጠርጥሪዎች የ50 ሺህ ብር ዋስትና በማቅረብ ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ወስኖ ነበር።

በተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ፖሊስ አርብ ዕለት ለደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አቤቱታ በማስገባቱ ተጠርጣሪዎቹ ሳይፈቱ ቀርተዋል። አቤቱታውን ዛሬ የተመለከተው የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ለተጠርጣሪዎቹ በተፈቀደላቸው ዋስትና ላይ የእግድ ትዕዛዙን አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ ግለሰቦቹ የተጠረጠሩበት ወንጀል የዋስትና መብትን የሚፈቅድ ወይም የሚከለክል መሆኑን ለማከራከር እና ለፖሊስ የተሰጠው የምርመራ ጊዜ በቂነቱን በመመርመር ብይን ለመስጠት ለነሐሴ 24 ቀን 2011 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል። በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን ተከስተው ከነበሩ ሁከቶች ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል የሲዳማ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ስራ አስኪያጅ ጌታሁን ደጉዬ ፣ ምክትላቸው ታሪኩ ለማ እና የእዚሁ ጣቢያ የቦርድ አባል የሆኑት በላይ ባልጉዳ ይገኙበታል።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአዲስ አበባ አማራ ወጣት ማህበር አዘጋጅነት የተሰናዳው የቡሄ፣ የሻደይ፣ አሸንድዬ እና የሶለን በዓል በጃን ሜዳ እየተከበረ ይገኛል።

Via Henok View
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ዛሬ በሁሩታ ከተማና ባካባቢዉ ካሉ ቀበሌዎች ጋር የቡሄ በአልን #በጅራፍ ግርፍ በዚህ መልኩ አክብረናል።" መክብብ ከሁሩታ

@tikvahethiopia @tsegabwolde
ፎቶ📸በ2011 #አርባምንጭ ከቱሪስት ፍሰት ከ82 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘቷን ሸገር ራድዮ ዘግቧል። #ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የለውጥ ስራዎችን ማስጀመሪያ ውይይት መድረክ!

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በአገራችን የመጀመሪያውን የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ከሶስት ዓመታት በላይ ከፈጀ የዝግጅት ምዕራፍ በኃላ ከ2012 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡ ይህ ፍኖተ ካርታ አጥኚ ቡድን ተቋቁሞ የትምህርትና ስልጠና ስርዓቱ ያለበትን ሁኔታ ከፈተሸ ወዲያ የደረሰባቸውን ችግሮች ሊቀርፉ የሚችሉ የመፍትሄ ሃሳቦች የተካተቱበት ነው፡፡ ፍኖተ ካርታው እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የሚተገበር ሲሆን 2012 ዓ.ምም የመጀመሪያው የትግበራ ዓመት ይሆናል፡፡ ፍኖተ ካርታው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ያሉ ችግሮችን ለይቶ መፍትሔዎችን አስቀምጧል፡፡

በፍኖተ ካርታ ዝግጅት ወቅት የተለዩ ችግሮች፦

•የሥርዓተ ትምህርት አዘገጃጀት ይዘትና ትግበራ ችግር
• የዩኒቨርስቲዎችዎች በተልዕኮ አለመለየት
• የትምህርት አደረጃጀት ችግር
• የህጎች፣ የአሠራሮችና ስታንደርዶች አለመኖርና አለመናበብ
• በቂና ብቁ የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ግብዓቶች ከትምህርት መስፋፋቱ ጋር አለመጣጣም
• ዩኒቨርስቲ-ኢንዱስትሪ ትስስር ዝቅተኛ መሆን/አለመኖር
• የሲቪል ሰርቪሱ አለመዘመን - ሥልጠና መስክና የሥራ ገበያ አለመጣጠም
ሲሆኑ በዚህ ምክንያት የመጡ ችግሮች ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
• የስነምግባር እና የሞራል ውድቀት
• ስርዓት አልበኝነትና ምክንያታዊ ያለመሆን
• የስራ ጠባቂነትና ጥገኝነት
• የወቅታዊ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን ያለማወቅና ያለመረዳት
• የተግባቦትና የመረዳዳት ችግር
• ዘመኑ የደረሰበት የቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ይዞ አለመገኘት

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-19
New Year New Thinking

ከተነሱ የመፍትሄ ምክረ-ሃሳቦች፦

• የዩኒቨርስቲ ትምህርት ቆይታ 4 አመት እንዲሆን (ለኢንጂነሪንግ 5፤ ለሜዲሲን 6)፣ 2 አመት Masters, 4 ዓመት Ph.D.

Ministry of Science and Higher Education - Ethiopia

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደቡብ ክልል የ2012 በጀት አለመጽደቅ ውዝግብ አስነሳ!

የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት ላለፉት ስምንት ወራት መሰብሰብ ባለመቻሉ የክልሉን በጀት ያላፀደቀ ሲሆን የ2011 በጀት ላይ በመመስረት የአንድ ወር በጀት ብቻ ታስቦ መለቀቁ የዋጋ ግሽበትን ያላማከለ እና የዞን አመራሮችን ጫና ውስጥ የከከተ ነው ተባለ።

‹‹የተለቀቀው አንድ አስራ ሁለተኛ በጀት ያለፈው አመት ቀመር ላይ በመመስረቱ መደበኛ ስራዎችን ለማከናወንም ሆነ ለአስቸኳይ ወጪዎች በቂ አይሆንም፡፡ በተጨማሪም ገንዘቡ የግብር ከፋዩ ገንዘብ እንደመሆኑ ይህንን መከልከል አግባብነት የለውም›› ሲሉ የወላይታ ብሄራዊ ንቅናቄ (ወብን) የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ተከተል ላቤና ገለፀዋል።

የክልሉ ፕሬስ ሴክሪታሪያት ኀላፊ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው የመንግስት ሰራተኞችን ደመወዝ ለመክፈል፣ መደበኛ ስራዎችን ለማስኬድ እንዲሁም #አስቸኳይ ስራዎችን ለማከናወን ጊዜያዊ በጀቱ በቂ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አክለውም ክልሉ የገቢ ግብር ማሰባሰብ ስራውን በማካሄድ ላይ መሆኑን ገልጸው የገንዘብ እጥረት አይኖርም ብለዋል፡፡

ምክር ቤቱ በየትኛውም አይነት ሁኔታ ተሰብስቦ መደበኛ ስራውን መስራት በአዋጅ የተሰጠው ተግባሩ ነው ያሉት የወብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ይህንን ስራውን በተቀመጠለት ጊዜ ገደብ ማከናወን አለመቻሉም አግባብ አይደለም ሲሉ ይተቻሉ፡፡

#አዲስማለዳ

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-19-2
የደብረ ታቦር (ቡሄ) በአል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ በተገኙበት እየተከበረ ነው። #ETHIOPIA #AddisTV

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ📸የቡሄ ትውፊታዊ ስርዓት በከተማ አስተዳደሩ ቅጥር ጊቢ ውስጥ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ኢ/ር ታከለ ኡማ የጅራፍ ማጮህ ትውፊታዊ ክንውን አድርገዋል፡፡

Via MayorOfficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር #ዛሬ በይፋ ተመስርቷል። ማህበሩ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመረጃ ነጻነትና የመደራጀት መብቶች እንዲከበሩ የህግ፣ የፖሊሲና የማዕቀፎች እንዲሁም የአፈጻጸም ማሻሻያዎች እንዲስፋፉ ለማድረግ ያለመ ነው ተብሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሞሞና ኤፍ ኤም 96.4

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ ተኮር የማሕበረሰብ ሬድዮ ጣብያ ሞሞና ኤፍ ኤም 96.4 የሙከራ ስርጭቱን ጀምረዋል። የሙከራ ስርጭቱ በኤፍ ኤም 96.4 ሜጋኸርዝ ወደ አድማጮቹ በመድረስ ላይ ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
❤️ከ3000 በላይ አባል❤️

6710 ላይ የህፃናት የልብ ህክምናን ለማገዝ በተከፈተው ግሩፕ ላይ እስካሁን ከ3 ሺህ የሚበልጡ የቤተሰባችን አባላት ተቀላቅለውናል!! በሺዎች የሚቆጠር ገንዘበ እንደ አቅማችን አስተዋፆ እያደረግን እንገኛለን!! ሀገር ወዳድነት መገለጫው ይህ ነው!!

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://t.iss.one/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ

እኔ ካለኝ ላይ አካፍያለሁ?? እናተስ??

ለአንድ መልዕክት የሚቆርጠው 1 ብር ብቻ ነው!!


በትንሹ 3 መልዕክት ይላኩ!

#አንድነት #ተስፋ #መተሳሰብ #ፍቅር #ቲክቫህ
እኛ አለንላችሁ!!
6710


❤️"ልባችን ከናተው ጋር ነው!"
❤️"እኔም የአቅሜን አረጋነሁ፤ እነሱም የኔ ልጆች ናቸው፤ እስከመጨረሻው እረዳለሁ"
❤️"ህመማቸው ህመሜ ነው"
❤️"1 ልብ በ1 ብር"

የቤተሰባችን አባላት፦

•በሀገራቸው ስም
•በባለቤታቸው ስም
•በልጆቻቸው ስም
•በፍቅረኛቸው ስም
•በሚወዷቸው ታዋቂ ሰዎች ስም
•በአባባሎች ... 6710 ላይ እንደ ዜጋ ሃላፊነታቸውን እየተወጡ ነው። እርሶስ?

ወደዚህ ግሩብ ግቡና እየሆነ ያለውን ተመልከቱ፤ ሀገር አለን የምንለው ለዚህ ነው። ሁሌም ለበጎ ስራ አብረን ስለቆምን!!

Screenshot ወደዚህ ግሩፕ👇

https://t.iss.one/joinchat/FCD9AhWFZJX_rX95-4rWNQ
ዩኒቨርሲቲዎች የፌዴራል ተቋምነታቸው ሊረጋገጥ፤ የአካዳሚክ ነጻነታቸውም ሊከበር ይገባል!

አሁን ባለው ሁኔታ ዩኒቨርሲቲዎች የሚስተዋለው እንደ ፌዴራል ሳይሆን እንደ አንድ አከባቢ ተቋም የመንቀሳቀስ አዝማሚያ ፈር ሊበጅለትና የፌዴራል ተቋምነታቸው ሊረጋገጥ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ የአካዳሚክ ነጻነታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ ማድረግ እንደሚያስፈልግም ተጠቁሟል፡፡

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ተቋምም ምልከታው ተገቢና ሊታረም እንደሚገባው በመጠቆም፤ ዩኒቨርሲቲዎች የፌዴራል ተቋም ሆነው እንዲሰሩ እንደሚደረግና የአካዳሚክ ነጻነታቸው እንዲከበር የሚያስችሉ እርምጃዎችም እንደሚወሰድ አረግግጧል፡፡

በ2012 የትምህርት ዘመን ወደትግበራ የሚገባውን የትምህርት ፍኖተ ካርታ አስመልክቶ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴት አዘጋጅነት ዛሬ በሸራተን አዲስ በተካሄደው የባለድርሻዎች የውይይት መድረክ ላይ እንደተገለጸው፤ ዩኒቨርሲቲዎች በአደረጃጀታቸውም ሆነ በአሰራራቸው የፌዴራል ሳይሆን የአከባቢ ተቋማት መስለዋል፡፡

ከተማሪዎች ምደባ እስከ መምህራንና አስተዳደር አካላት ያለው እውነትም ይሄንኑ ያሳያል፡፡

ይህ ደግሞ በዩኒቨርሲቲዎች ለሚስተዋለው አለመረጋጋት ጭምር ምክንያት ስለሚሆን ሊታረም፤ ዩኒቨርሲቲዎችም የፌዴራል ተቋምነታቸው ሊረጋገጥ ይገባዋል፤ ሲሉ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/et-08-19-3

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቡሄ በዓል ባህላዊና ሃይማኖታዊ ይዘቱን እንደጠበቀ በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረ ታቦር ኢየሱስ ተራራ ላይ ተከበረ። በዓሉ ከትውልድ ወደትውልድ እንዲተላለፍ ከጎንደር፣ ከላል ይበላና መሰል የቱሪዝም ሃብቶች ጋር በማስተሳሰር ለቱሪስት መስህብ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን የደብረ ታቦር ከተማ ከንቲባ አቶ አበባው እምቢአለ በበዓሉ ላይ ገልፀዋል።

Via #ENA
ፎቶ፡ ዳኒ/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE

የአቶ አብዲ ጠበቆች ይዘው የሚቀርቡትን የክስ መቃወምያ ለመቀበል ችሎቱ ዛሬ ረፋድ ላይ ቢሰየምም ጠበቆች ግን ሳይሰየሙ ቀርተዋል።

አቶ አብዲ ኢሌ በበኩላቸው ባለፈው ቀጠሮ ከተፈጠረው ሁኔታ በኋላ ተነጋግረናል መቃወምያውም በምን መልኩ መቅረብ እንዳለበት ስንመካከር ነበር ዛሬ ለምን እንዳልቀረቡ አላውቅም ብለዋል።

ችሎቱ ጠበቆች ያልተሰየሙበትን ምክንያት በፅሁፍ እንዲያስረዱና መቃወምያቸውን እስከ ነሀሴ 30 እንዲያቀርቡ ቢያዝም ብይኑን ግን ለ2012 ጥቅምት አሻግሮታል።

Via ሳምራዊት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ቃጠሎ ክስ በቀረበባቸው አራት እስረኞች ላይ የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። ተከሳሾቹ “ክሱን እውቅና ሰጥተን የፍርድ ማቅለያ አናቀርብም” ሲሉ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል።

ፍርድ ቤቱ ነሐሴ 1 ቀን 2011 ዓ. ም. በዋለው ችሎት በአራቱም ተከሳሾች ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ያሳለፈ በመሆኑ በዛሬ ውሎው የተከሳሾችን የቅጣት ማቅለያ ተቀብሎ የቅጣት ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ተጠብቆ ነበር። ሆኖም በዛሬው ችሎት ዳኞቹ ሰፋ ያለ ጊዜ የወሰዱት ተከሳሾች በባለፈው ችሎት ጥፋተኛ ሲባሉ ያሳዩት ተግባር ተገቢ እንዳልነበር በመምከር ነበር። ተከሳሾቹ “ወንበር መሰባበራቸውን እና ጥይት እስኪተኮስ ድረስ መረበሻቸውን” ዳኞቹ አስታውሰው ይህ ተገቢ አለመሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል።

የዛሬው የችሎት ውሎም ከወትሮው በተለየ ጠንከር ባለ ጥበቃ ስር የተከናወነ ነበር። በስፍራው የነበረው የዶይቼ ቬለ ዘጋቢ በችሎት አዳራሽ ውስጥ ብቻ 30 ፖሊሶች እንደነበሩ ተመልክቷል። የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡ በዛሬው የችሎት ውሎ የተጠየቁት አራቱ ተከሳሾች ጌታቸው እሸቴ፣ ፍጹም ጌታቸው፣ ሸምሱ ሰይድ እና አቶ ቶፊቅ ሽኩር “ባልፈጸምነው ወንጀል የጥፋት ማቅለያ አናቀርብም፤ የፈለጋችሁትን ፍረዱብን፤ የእውነት አምላክ ይፈርዳል” በማለት በቁጣ ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ተከሳሾቹ “ድራማ” ሲሉ ለጠሩት ክስ “እውቅና” እንደማይሰጡም ለችሎቱ ተናግረዋል። “በዚህ ጉዳይ 159 ሰዎች ተከስሰን ነበር ግማሹ ከግንቦት 7 እና ኦነግ ጋር ተደራርድሮ ሲወጣ እኛ ድሆች ስለሆንን፤ የሚጮህልን የፖለቲካ ፓርቲ እና ሚዲያ ስለሌለ ብቻ ይሄው ታስረን ጥፋተኛ ለመባል በቅተናል” ሲሉም ለችሎቱ ተናግረዋል።

https://telegra.ph/ETH-08-19-2

Via #DW
በአቶ አብዲ መሐመድ ዑመር የክስ መዝገብ ስር የተከሰሱ ሰዎች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ተወስኗል!

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ የወንጀል ችሎት በቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ መሐመድ ዑመር /አብዲ ኢሌ/ የክስ መዝገብ ተጠቅሰው ያልተገኙ 11 ተከሳሾች ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ብይን ሰጠ።

በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ ተደርጎላቸው ሳይቀርቡ በሌሉበት ጉዳያቸው እንዲታይ ከተበየነባቸው ተከሳሾች የክልሉ ልዩ ኃይል አዛዥ የነበሩት ጄኔራል አብዱራህማን አብዱላሂ፣ ሻለቃ ሼክ ሙክታር እና ሄጎ የተሰኘውን የአመፅ ቡድንን በምክትልነት ሲመሩ ነበር የተባሉት የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ መሐመድ አህመድ ይገኙበታል።

ችሎቱ ከነዚህ በተጨማሪ በክስ መዝገቡ የመኖሪያ አድራሻ ተፈልገው ያልተገኙ ሌሎች 7 ተከሳሾችም እንዲቀርቡ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጥሪ እንዲደርሷቸው ትዕዛዝ ሰጥቷል።
በተሻሻለው ክስ ላይ 1ኛው ተከሳሽ የቀድሞ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አብዲ ዑመር ከጠበቆች ጋር ተማክሬ የክስ መቃወሚያ አቀርላሁ ብለዋል።

ጉዳያቸውን በአካል እየተከታተሉ ከሚገኙ 14 ተከሳሾች የተፋጠነ ፍትሕ ተጠቃሚ መሆን አልቻልንም፤ ጉዳያችንን ፍርድ ቤቱ በትኩረት ይመልከትልን በማለት አመልክተዋል።

እንደ ኢቢሲ ዘገባ ችሎቱ የክስ መዝገቡ በጋራ የሚታይ በመሆኑ የተከሳሾች የግል አቤቱታ የክስ መቃወሚያ እና ከሌሎች መሰል ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የተጠቀሰውን ጊዜ ሊቆጠር ችሏል ብሏል፡፡

Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በህገ ወጥ መንገድ ከአገር ሊወጣ የነበረ 8 ነጥብ 79 ኪሎ ግራም ወርቅና የተለያዩ የውጭ አገር የገንዘብ ኖቶች መያዛቸውን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ። የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ እንደገለጹት በቁጥጥር ስር የዋለው 8 ነጥብ 79 ኪሎ ግራም ወርቅ፣ 41 ሺህ ዩሮ፣ 55 ሺህ ሪያል እንዲሁም ሁለት ተሽከርካሪዎች ይገኙበታል።

በቁጥጥር ስር የዋለው በሶማሌ ክልል ሞምባስ ኬላ በኩል ከለሊቱ 10 ሰዓት ላይ በህገ ወጥ መንገድ ከአገር ሊወጣ ሲል መሆኑን ገልጸዋል። የተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎችና የገንዘብ ኖቶች ዛሬውኑ ለብሄራዊ ባንክ ገቢ መደረጋቸውንም ተናግረዋል። ባለፈው ሀምሌ ወር ብቻ 134 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ ኮንትሮባንድ የገቢና ወጪ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም አስታውሰዋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ኢትዮጵያ

የሚወደውን ሰው፣ አምላክ ይፈትናል
ቃሉም እውነት አለው፣ ያንቺ #ስቃይ በዝቷል
ፈተናሽም ታይቷል፣ ስቃይሽም በዝቷል
ኢትዮጵያ ሀገሬ፣ ምድራዊ ገነት
ለበጎ ይሆን ወይ፣ ያንቺ ስቃይ መብዛት
ያንቺ ስቃይ መብዛት
ያንቺስ ድህነት
ኋላ ቀርነት።

ታንፀን፣ በሰላም፣ #በተስፋ፣ በፍቅር፣ እምነት
ማለፍ እንድንችል ፣ ስንፍና ይውጣ ከቤት
እኛ ተቀምጠን ፣ ስለምን ወገኔ ይራባል
ጠንክረን ከሰራን ፣ ልመና ታሪክ ይሆናል
ያልተነካ ጉልበት ኦሆ ከቤት ተቀምጦ ኦሆ
ወገን ለምን ይለቅ ኦሆ በጠኔ ተውጦ ኦሆ
ልጅ አዋቂ ሳንል ኦሆ ሁላችን ባንድነት ኦሆ
እንውጣ ከችግር ኦሆ የሰው እጅ ከማየት ኦሆ
የያዝነውን ይዘን ኦሆ ተባብረን እንስራ ኦሆ
ስሟም ያገራችን ኦሆ በበጎ ይጠራ ኦሆ

ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ

ቅድስት ሀገሬ፡ ኢትዮጵያ
የብሄር አምባ፡ መጠለያ
ታሪካዊት ናት፡ እናታችን
ሁሉም ሙሉ ነው፡ ከቤታችን
ዞር ብለን ለምን፡ እንይ ሌላ
እያለችን ዋርካ፡ መጠለያ
ይለወጥ ስሟ፡ ያገራችን
በስራ ጥረት፤ በክንዳችን

#MisikerAwol

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-EDU ላለፉት ወራት ተቋርጦ የነበረው የቋንቋ ትምህርት ቀጥሏል። ዛሬ የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ 6ኛው ቀን ትምህርት ይቀጥላል።

√የትግርኛ
√ግዕዝ ትምህርቶችም እንዲቀጥሉ ይደረጋል!

በቋንቋ ትምህርት ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ የቤተሰባችን አባላት መድረኩ ክፍት ነው። የኢትዮጵያን ቋንቋዎችና ባህሎች ለወንድሞቻችን እናስተምራለን፤ እንማማራለን ለምትሉ ሁሉ መድረኩ ክፍት ነው።

ሀገርን መውደድ የኛ የኢትዮጵያውያን ዜጎች የሆኑ ነገሮችን ከማክበርና ከመውደድ ይጀምራል!!

TIKVAH-EDU👇
https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEWA_-Jt2zIM5COJqw