በ4 ቢሊዮን ብር በደብረ ማርቆስ ፣ ሚዛን አማን፤ ጎሬ መቱ፣ በነገሌና ያቤሎ 71 ሰው የሚጭኑ አውሮፕላኖች ማረፊያ ለመገንባት መታቀዱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አስታወቀ፤ ግንባታዎቹን በ2 ዓመት ተኩል ለማጠናቀቅ ታቅዷል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-17-3
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-17-3
በሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ትምህርት ቤት "ወ/ሮ አየለች ዳገፉ መታሰቢያ" ከተመዘገቡት ከፍተኛ ውጤቶች መካከል የነዚህ እንስቶች ውጤት ይጠቀሳል፦
#BERSABEH 600
#ETSUBDINK 612
#BETLHEM 611
#BERUKTAWIT 605
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BERSABEH 600
#ETSUBDINK 612
#BETLHEM 611
#BERUKTAWIT 605
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአንድ ዓመት ነጻ የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎት!
የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት 20 ለሚደርሱ ህሙማን የአንድ ዓመት ነጻ ዕጥበት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ነው ለህሙማኑ አገልገሎቱን መስጠት የጀመረው፡፡
የኢትዮጵያ መድህን ድርጅትም ለህሙማኑ ለአንድ ዓመት ሙሉ የዕጥበት ክፍያ የሚውል የ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ሰጥቷል፡፡ የድርጅቱ የቢዝነስ ልማትና ሪስክ ማኔጅመንት ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ መንግስቱ መሃሩ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለማገዝ ሰፊ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው በማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ የሚያደርገውን ተሳትፎም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በሰጠው የገንዘብ ድጋፍ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የሚገኙ 20 የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ለአንድ ዓመት በነፃ እንዲጠቀሙ ተደርጓል ብለዋል፡፡
የአገልግሎቱ ጠቃሚ ህሙማንም በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡ ሌሎች የመንግስትና የግል ድርጅቶችም እየጨመረ የመጣውን የኩላሊት ህመም ጉዳት ለመቀነስ እንዲረባረቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Via ኤ ኤም ኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት 20 ለሚደርሱ ህሙማን የአንድ ዓመት ነጻ ዕጥበት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ድርጅቱ ከኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ነው ለህሙማኑ አገልገሎቱን መስጠት የጀመረው፡፡
የኢትዮጵያ መድህን ድርጅትም ለህሙማኑ ለአንድ ዓመት ሙሉ የዕጥበት ክፍያ የሚውል የ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ሰጥቷል፡፡ የድርጅቱ የቢዝነስ ልማትና ሪስክ ማኔጅመንት ምክትል ስራ አስፈጻሚ አቶ መንግስቱ መሃሩ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ለማገዝ ሰፊ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰው በማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ የሚያደርገውን ተሳትፎም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡
የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ የኢትዮጵያ መድን ድርጅት በሰጠው የገንዘብ ድጋፍ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል የሚገኙ 20 የኩላሊት ዕጥበት አገልግሎት ተጠቃሚዎች ለአንድ ዓመት በነፃ እንዲጠቀሙ ተደርጓል ብለዋል፡፡
የአገልግሎቱ ጠቃሚ ህሙማንም በተደረገላቸው ድጋፍ ደስተኞች መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡ ሌሎች የመንግስትና የግል ድርጅቶችም እየጨመረ የመጣውን የኩላሊት ህመም ጉዳት ለመቀነስ እንዲረባረቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Via ኤ ኤም ኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጀግኒት
ተማሪ ZEHARA #ከBAHIRDAR 615፣ HILANI ከአዳማ #ODA_SPECIAL_BOARDING 606፣ NEBUS #ከBISHOFTU 607 በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና ያስመዘገቡ እንስቶች ናቸው! #ኢትዮጵያዊት
#BAHIDAR
#BISHOFTU
#ODA_SPECIAL_BOARDING
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተማሪ ZEHARA #ከBAHIRDAR 615፣ HILANI ከአዳማ #ODA_SPECIAL_BOARDING 606፣ NEBUS #ከBISHOFTU 607 በዘንድሮው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና ያስመዘገቡ እንስቶች ናቸው! #ኢትዮጵያዊት
#BAHIDAR
#BISHOFTU
#ODA_SPECIAL_BOARDING
@tsegabwolde @tikvahethiopia
138 ሞተሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ!
በደቡብ ክልል ሆሳእና ከተማ 138 ሞተር ብስክሌቶች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኮማንድ ፖስቱ ዛሬ ገለጸ፡፡ የከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የኮማንድ ፖስት አባል አቶ ዳዊት ኪበሞ ለኢዜአ እንደገለጹት ሞተር ቢስክሌቶቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ለኅብረተሰቡ ደህንነት ስጋት በመሆናቸው ነው፡፡ ሠሌዳ ቁጥር ሳይኖራቸው ሲንቀሳቀሱ በመገኘታቸው አገልግሎት እንዳይሰጡ መታገዳቸውን አስረድተዋል። ኮማንድ ፖስቱ የአካባቢዉን ኅብረተሰብ ደህንነት ለስጋት የሚጥሉ ጉዳዮችን በመለየት እርምጃ መውሰዱን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ ክልል ሆሳእና ከተማ 138 ሞተር ብስክሌቶች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኮማንድ ፖስቱ ዛሬ ገለጸ፡፡ የከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የኮማንድ ፖስት አባል አቶ ዳዊት ኪበሞ ለኢዜአ እንደገለጹት ሞተር ቢስክሌቶቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ለኅብረተሰቡ ደህንነት ስጋት በመሆናቸው ነው፡፡ ሠሌዳ ቁጥር ሳይኖራቸው ሲንቀሳቀሱ በመገኘታቸው አገልግሎት እንዳይሰጡ መታገዳቸውን አስረድተዋል። ኮማንድ ፖስቱ የአካባቢዉን ኅብረተሰብ ደህንነት ለስጋት የሚጥሉ ጉዳዮችን በመለየት እርምጃ መውሰዱን እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ የሱዳን ተቃዋሚዎች ስብስብ ከሆነው የነፃነትና የለውጥ ሀይል አባላት ጋር ተወያዩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የነፃነትና የለውጥ ሀይል አባላት በሱዳን የይቅርታ እና የአንድነት ባህልን እንዲያዳብሩ አበረታተዋል፡፡
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ካርቱም
የሱዳን ሲቪል አስተዳደር የሚሰረትበት ስምምነት የፊርማ ሥነ-ሥርዓት እየተካሔደ ይገኛል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማኅማት በሰነዱ ላይ ፈርመዋል።
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱዳን ሲቪል አስተዳደር የሚሰረትበት ስምምነት የፊርማ ሥነ-ሥርዓት እየተካሔደ ይገኛል። ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማኅማት በሰነዱ ላይ ፈርመዋል።
Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአክሱም ዩኒቨርስቲ የሽሬ ካምፓስ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶችን በእርዳታ አገኘ። ካምፓሱ ድጋፉን ያገኘው #ከካናዳ መንግስት የማአድን ዘርፍ ትምህርትና ስጠልና ማጠናከርያ ፕሮጀክት መሆኑን የካምፓሱ ዲን አቶ መአርግ በላይ ገልጸዋል። #ENA
@tsegabwolde @tivahethiopia
@tsegabwolde @tivahethiopia
#ካርቱም
የሱዳን ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና የተቃዋሚ መሪዎች ስልጣን #ለመጋራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በይፋ ተፈራራሙ። ስምምነቱ በሲቪል የሚመራ የሽግግር መንግስት ለመመስረት መንገድ ይጠርጋል ተብሎለታል። በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የደቡብ ሱዳን አቻቸው ሳልቫ ኪር ተገኝተዋል።
Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱዳን ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና የተቃዋሚ መሪዎች ስልጣን #ለመጋራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በይፋ ተፈራራሙ። ስምምነቱ በሲቪል የሚመራ የሽግግር መንግስት ለመመስረት መንገድ ይጠርጋል ተብሎለታል። በስምምነት ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የደቡብ ሱዳን አቻቸው ሳልቫ ኪር ተገኝተዋል።
Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከመመሪያ ውጪ የትብብር ስልጠና ሲሰጡ የተገኙ የመንግስት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስልጠናውን እንዲያቋርጡ ተወሰነ!
የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የተላለፈውን ውሳኔ በመተላለፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን የሚሰጡትን የትብብርት ስልጠናዎች እንዲቋረጡ ማድረጉን ገለጸ።
የትብብር ስልጠናውን ሲሰጡ የነበሩ ተቀዋማትም ዮም ኢንስቲትዩት ኦፍ ኢኮኖሚ ደቨሎፐመንት ከደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ጋር፣ አዲስ ኮንቲነንታል የጤና አጠባበቅ ኢንስቲትዩት ከሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ጋር እና ናሸናል ኮሌጅ ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር ናቸው፡፡
ከኤጀንሲው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በዚሁ መንገድ ተቀብለው ያስመረቋቸውን እና በመማር ላይ ያሉትን የተማሪዎች የተሟላ ዝርዝር መረጃ በሶስት የስራ ቀናት ውስጥ ለኤጀንሲው እንዲያቀርቡ በማሳሰብ ለዮም ኢንስቲትዩት ኦፍ ኢኮኖሚ ደቨሎፐመንት፣ ለአዲስ ኮንቲነንታል የጤና አጠባበቅ ኢንስቲትዩት እና ለናሸናል ኮሌጅ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ የተላለፈውን ውሳኔ በመተላለፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን የሚሰጡትን የትብብርት ስልጠናዎች እንዲቋረጡ ማድረጉን ገለጸ።
የትብብር ስልጠናውን ሲሰጡ የነበሩ ተቀዋማትም ዮም ኢንስቲትዩት ኦፍ ኢኮኖሚ ደቨሎፐመንት ከደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ጋር፣ አዲስ ኮንቲነንታል የጤና አጠባበቅ ኢንስቲትዩት ከሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ጋር እና ናሸናል ኮሌጅ ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር ናቸው፡፡
ከኤጀንሲው የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው በዚሁ መንገድ ተቀብለው ያስመረቋቸውን እና በመማር ላይ ያሉትን የተማሪዎች የተሟላ ዝርዝር መረጃ በሶስት የስራ ቀናት ውስጥ ለኤጀንሲው እንዲያቀርቡ በማሳሰብ ለዮም ኢንስቲትዩት ኦፍ ኢኮኖሚ ደቨሎፐመንት፣ ለአዲስ ኮንቲነንታል የጤና አጠባበቅ ኢንስቲትዩት እና ለናሸናል ኮሌጅ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ታግደዋል
አራት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ከግል ኮሌጆች ጋር በትብብር የማስተርስ ድግሪ መርሃ ግብር እንዳይሰጡ ማገዱን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ እግዳው የተጣለባቸው፦
√የጅማ ዩኒቨርሲቲ ABH ከሰተኘ ተቋም ጋር፣
√ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከዮም ኮሌጅ ጋር፣
√ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ከናሽናል ኮሌጅና
√ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ ኮንቲነንታል የጤና ኢንስቲትዩት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አራት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ከግል ኮሌጆች ጋር በትብብር የማስተርስ ድግሪ መርሃ ግብር እንዳይሰጡ ማገዱን የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ እግዳው የተጣለባቸው፦
√የጅማ ዩኒቨርሲቲ ABH ከሰተኘ ተቋም ጋር፣
√ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከዮም ኮሌጅ ጋር፣
√ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ከናሽናል ኮሌጅና
√ሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ ኮንቲነንታል የጤና ኢንስቲትዩት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወቂያ09-12-20111.pdf
176.3 KB
#ለደብረ_ማርቆስ_ዩኒቨርሲቲ_ተማሪዎች
በ2011 የትምህርት ዘመን በቴክኖሎጅ ኢንስትቲዩት የማጠቃለያ ፈተና በራሳቸው ፈቃድ ላልወሰዱ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዓመት መደበኛ የቅድመ – ምረቃ ተማሪዎች!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በ2011 የትምህርት ዘመን በቴክኖሎጅ ኢንስትቲዩት የማጠቃለያ ፈተና በራሳቸው ፈቃድ ላልወሰዱ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዓመት መደበኛ የቅድመ – ምረቃ ተማሪዎች!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ...
"....እንደ ተማሪ #ተቀብሎ እናንተን በሙሉ ኃላፊነት የሚጠብቃችሁ፣ መብታችሁንም የሚያስጠብቅላችሁ በ2012 የትምህርት ዘመን ሁለተኛ ሴሚስተር የማጠቃለያ ፈተና ወቅት ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከዚያ ውጭ ወደ ዩኒቨርሲቲው በመምጣት ከሚደርስባችሁ እንግልት እና አላስፈላጊ ወጭ ራሳችሁን እና ቤተሰባችሁን እድትጠብቁ እንዲሁም ተጨማሪ ተያያዥ ችግሮችን ለመከላከል የበኩላችሁን እንድታደርጉ መረጃዎችን ከዩኒቨርሲቲው ብቻ እንድትቀበሉ በጥብቅ ያስታውቃል።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"....እንደ ተማሪ #ተቀብሎ እናንተን በሙሉ ኃላፊነት የሚጠብቃችሁ፣ መብታችሁንም የሚያስጠብቅላችሁ በ2012 የትምህርት ዘመን ሁለተኛ ሴሚስተር የማጠቃለያ ፈተና ወቅት ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከዚያ ውጭ ወደ ዩኒቨርሲቲው በመምጣት ከሚደርስባችሁ እንግልት እና አላስፈላጊ ወጭ ራሳችሁን እና ቤተሰባችሁን እድትጠብቁ እንዲሁም ተጨማሪ ተያያዥ ችግሮችን ለመከላከል የበኩላችሁን እንድታደርጉ መረጃዎችን ከዩኒቨርሲቲው ብቻ እንድትቀበሉ በጥብቅ ያስታውቃል።"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሱዳን ፖለቲከኞች ሥልጣን ለመጋራት በመስማማታቸው ደስታቸውን ለመግለፅ ወደ ኻርቱም ያቀኑ የአትባራ ሰዎች በተጓዙበት ባቡር አናት ቆመው ሰንደቅ ዓላማ ያውለበልቡ ነበር።
Via #Eshete
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via #Eshete
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ከዚህ በኃላ ፍትህን ከመንግስት ሳይሆን ከእግዜያብሄር ነው የምጠብቀው"
በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረዉን ሁከት #ቀስቅሰዋል በሚል ተጠርጥረው የተያዙ ዘጠኝ ግለሰቦች በዋስ እንዲፈቱ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የወሰነላቸው ቢሆንም እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ ከእስር እንዳልተፈቱ ቤተሰቦቻቸው ለTIKVAH-ETH ተናገሩ። ፍርድ ቤቱ ትላንት በዋለው ችሎት በዋስ እንዲፈቱ ከወሰነላቸዉ ተጠርጣሪዎች መካካል የሲዳማ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ስራ አስኪያጅ ጌታሁን ደጉዬ ፣ ምክትላቸው አቶ ታሪኩ ለማ እና የጣቢያው የቦርድ አባል የሆኑት በላይ ባልጉዳ ይገኙበታል።
በጉዳዩ ላይ ለTIKVAH-ETH የተናገሩት ከታሳሪዎቹ ቤተሰቦች አንደኛው ይህን ብለዋል፦
"የዋስትና ደብዳቤውን በጊዜ ነው ጨርሰን የሄድነው፤ ፖሊስ ግን ሊፈታቸው ፍቃደኛ አልነበረም። ፖሊስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ደብዳቤ አስገብቻለሁ አለን፤ ነገር ግን ሄደን ስናይ ያስገባውና የተፈቀደለት እግድ የለም ነገር ግን ልጆቹን አልሠጣችሁም አለን። የፖለቲካ እስረኞች ናቸው ህጉ የሚፈታው አይደለም። ...እዚህ አገር ላይ ከፍርድ ቤትና ከህግ የሚበልጠው እላይ ያለው ደውሎ ልቀቅ የሚል ሰው ነው ይህ እኛ እንደተረዳነው የፖለቲካ ጉዳይ ነው። በሚዲያ ቀርቦ የምናገኘው ፍትህ የለም። ለውጥ የሚባል ነገር የሌለበት ሀገር ላይ ነው ያለነው። ፍትህን ከእግዚያብሄር ጠብቀን እንኖራለን። አሁንም ቢሆን የሲዳማ ህዝብ ልጆቹ ይለቀቃሉ ብሎ ጠብቆ ነበር። በቦታው የነበረው ሰው ሀላሌ ይፍታልን ብሎ ነው የሄደው። የሲዳማ ህዝብ ሲዳማ ብቻ ስለሆኑ የታሰሩ ልጆች ላይ የሚደረገውን ጭቆና አይቶ አሁንም ቢሆን መንግስት ፍትህን ይሰጣል ብሎ አይጠብቅም፤ አይጠይቅም። ከእግዚያብሄር ነው ፍትህን የሚጠብቀው ይህ ህዝብ"
#ቲክቫህ
በሲዳማ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረዉን ሁከት #ቀስቅሰዋል በሚል ተጠርጥረው የተያዙ ዘጠኝ ግለሰቦች በዋስ እንዲፈቱ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የወሰነላቸው ቢሆንም እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ ከእስር እንዳልተፈቱ ቤተሰቦቻቸው ለTIKVAH-ETH ተናገሩ። ፍርድ ቤቱ ትላንት በዋለው ችሎት በዋስ እንዲፈቱ ከወሰነላቸዉ ተጠርጣሪዎች መካካል የሲዳማ ሚዲያ ኔትዎርክ ዋና ስራ አስኪያጅ ጌታሁን ደጉዬ ፣ ምክትላቸው አቶ ታሪኩ ለማ እና የጣቢያው የቦርድ አባል የሆኑት በላይ ባልጉዳ ይገኙበታል።
በጉዳዩ ላይ ለTIKVAH-ETH የተናገሩት ከታሳሪዎቹ ቤተሰቦች አንደኛው ይህን ብለዋል፦
"የዋስትና ደብዳቤውን በጊዜ ነው ጨርሰን የሄድነው፤ ፖሊስ ግን ሊፈታቸው ፍቃደኛ አልነበረም። ፖሊስ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ደብዳቤ አስገብቻለሁ አለን፤ ነገር ግን ሄደን ስናይ ያስገባውና የተፈቀደለት እግድ የለም ነገር ግን ልጆቹን አልሠጣችሁም አለን። የፖለቲካ እስረኞች ናቸው ህጉ የሚፈታው አይደለም። ...እዚህ አገር ላይ ከፍርድ ቤትና ከህግ የሚበልጠው እላይ ያለው ደውሎ ልቀቅ የሚል ሰው ነው ይህ እኛ እንደተረዳነው የፖለቲካ ጉዳይ ነው። በሚዲያ ቀርቦ የምናገኘው ፍትህ የለም። ለውጥ የሚባል ነገር የሌለበት ሀገር ላይ ነው ያለነው። ፍትህን ከእግዚያብሄር ጠብቀን እንኖራለን። አሁንም ቢሆን የሲዳማ ህዝብ ልጆቹ ይለቀቃሉ ብሎ ጠብቆ ነበር። በቦታው የነበረው ሰው ሀላሌ ይፍታልን ብሎ ነው የሄደው። የሲዳማ ህዝብ ሲዳማ ብቻ ስለሆኑ የታሰሩ ልጆች ላይ የሚደረገውን ጭቆና አይቶ አሁንም ቢሆን መንግስት ፍትህን ይሰጣል ብሎ አይጠብቅም፤ አይጠይቅም። ከእግዚያብሄር ነው ፍትህን የሚጠብቀው ይህ ህዝብ"
#ቲክቫህ
የኬንያን ባህላዊ የአልኮል መጠጥ በድብቅ ሲያመርቱ የነበሩ ቻይናዊያን በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ ቻንጋ የተባለውን የኬንያ ባህላዊ የአልኮል መጠጥ በድብቅ አምርተው ሲሸጡ የተገኙት ቻይናዊያን ዋንግ ያላን እና ዋንግ ሃይጂያን ይባላሉ፡፡
ማቻኮስ በተባለው አካባቢ በሚገኝው የቻይናዊያኑ መኖሪያ ቤት ውስጥ 3ሺህ ሊትር ያለቀለት የአልኮል መጠጥ (ቻንጋ) ፤ 800 ሊትር ሜታኖል ፣ የአልኮል ድፍድፍ የያዙ በርካታ በርሜሎች፣ ትላልቅ የውሃ ማጠራቀሚያዎች እና ለአልኮሉ መስሪያ የሚውሉ የተለያዩ የእህል አይነቶችን ተገኝተዋል፡፡
ፖሊስ ቻይናዊያኑ ባህላዊ መጠጡን በከፍተኛ መጠን ማምረት የሚያስችላቸው ትልልቅ የፋብሪካ መሳሪያዎችን ቤታቸው ወስጥ ተክለው አግኝቻለሁ ብሏል፡፡ ሜታኖል ሰዎች በቀላሉ እንዲሰክሩ የሚያደርግ አደገኛ ኬሚካል ከመሆኑ ባሻገር ለአይነ ስውርነት እና ለሞት ሊዳርግ ይችላል፡፡
የኬንያዊያንን ባህላዊ መጠጥ ቻንጋን በፋብሪካ ደረጃ አምርተው በማሸግ ለገበያ እያቀረቡ እንደነበር የተጠረጠሩት ቻይናዊያኑ ሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል፡፡
Via #BBC/AHADU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማቻኮስ በተባለው አካባቢ በሚገኝው የቻይናዊያኑ መኖሪያ ቤት ውስጥ 3ሺህ ሊትር ያለቀለት የአልኮል መጠጥ (ቻንጋ) ፤ 800 ሊትር ሜታኖል ፣ የአልኮል ድፍድፍ የያዙ በርካታ በርሜሎች፣ ትላልቅ የውሃ ማጠራቀሚያዎች እና ለአልኮሉ መስሪያ የሚውሉ የተለያዩ የእህል አይነቶችን ተገኝተዋል፡፡
ፖሊስ ቻይናዊያኑ ባህላዊ መጠጡን በከፍተኛ መጠን ማምረት የሚያስችላቸው ትልልቅ የፋብሪካ መሳሪያዎችን ቤታቸው ወስጥ ተክለው አግኝቻለሁ ብሏል፡፡ ሜታኖል ሰዎች በቀላሉ እንዲሰክሩ የሚያደርግ አደገኛ ኬሚካል ከመሆኑ ባሻገር ለአይነ ስውርነት እና ለሞት ሊዳርግ ይችላል፡፡
የኬንያዊያንን ባህላዊ መጠጥ ቻንጋን በፋብሪካ ደረጃ አምርተው በማሸግ ለገበያ እያቀረቡ እንደነበር የተጠረጠሩት ቻይናዊያኑ ሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሏል፡፡
Via #BBC/AHADU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የምዕራብ ኦሮሚያ ሰባት ዞኖች የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ(ኦዲፒ)ወጣቶች ሊግ ስብሰባ በነቀምቴ ከተማ እየተካሄደ ነው። በስብሰባው ከዞኖቹ የተውጣጡ ከ1ሺህ 500 በላይ ወጣቶች በመካፈል ላይ ናቸው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለስ ተችሏል"- ኮማንድ ፓስቱ
.
.
በሀዋሳ ከተማና በሲዳማ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ የነበረውን አለመረጋጋት የአካባቢውን ህብረተሰብ በማሳተፍ ዜጎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ አስታወቀ። ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመቆጣጠር የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት ያከናወናቸውን አበይት ተግባራት አፈጻጸም ዛሬ ገምግሟል፡፡
በግምገማውም በሀዋሳና በሲዳማ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በተፈጠረው የጸጥታ ችግር የተዘረፉ ንብረቶችን ህብረተሰቡን በማሳተፍ ማስመለስ የተቻለ ሲሆን በግጭቱ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀዬ አቸው እዲመለሱ ተረደርጓል ብሏል፡፡ እንዲሁም የተሰባበሩ ቤቶች እና ንብረቶች እንዲጠገኑ መደረጉንም ኮማንድ ፖስቱ አስታውቋል።
ኮማንድ ፓስቱ በሀዋሳ ከተማ ፣ በሲዳማ ዞን እና በክልሉ አንዳንድ ዞኖች በህገወጥ መንገድ የተሰቀሉ ሰንደቅ አላማዎች እና ታፔላዎች ወርደው በምትኩ ህጋዊ ሰንደቅ አላማዎች እና ታፔላዎች እንዲሰቀሉ ማድረጉን ከከልሉ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ህገ ወጥ የወጣት አደረጃጀቶች ወደ ህጋዊ መስመር እንዲገቡ የተጀመረው ስራ አበረታች መሆኑን ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ አስታውቋል፡፡ ሀምሌ 11 ቀን 2011 ዓም በነበረው የጸጥታ ችግር ተጠርጥረው በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት 1 ሺህ 384 ሰዎች ውስጥ የማጣራት ስራ በመስራት 481 ተጠርጣሪዎች የተለቀቁ ሲሆን ቀሪ 903 ተከሳሾች በክስ ሂደት ላይ መሆናቸውን ኮማንድ አስታውቋል፡፡
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
በሀዋሳ ከተማና በሲዳማ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የተፈጠረውን የጸጥታ ችግር ተከትሎ የነበረውን አለመረጋጋት የአካባቢውን ህብረተሰብ በማሳተፍ ዜጎች በሰላም ወጥተው እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ አስታወቀ። ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ በሀዋሳ ከተማ እና በሲዳማ ዞን ተከስቶ የነበረውን የጸጥታ ችግር ለመቆጣጠር የተቋቋመው ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስት ያከናወናቸውን አበይት ተግባራት አፈጻጸም ዛሬ ገምግሟል፡፡
በግምገማውም በሀዋሳና በሲዳማ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በተፈጠረው የጸጥታ ችግር የተዘረፉ ንብረቶችን ህብረተሰቡን በማሳተፍ ማስመለስ የተቻለ ሲሆን በግጭቱ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ቀዬ አቸው እዲመለሱ ተረደርጓል ብሏል፡፡ እንዲሁም የተሰባበሩ ቤቶች እና ንብረቶች እንዲጠገኑ መደረጉንም ኮማንድ ፖስቱ አስታውቋል።
ኮማንድ ፓስቱ በሀዋሳ ከተማ ፣ በሲዳማ ዞን እና በክልሉ አንዳንድ ዞኖች በህገወጥ መንገድ የተሰቀሉ ሰንደቅ አላማዎች እና ታፔላዎች ወርደው በምትኩ ህጋዊ ሰንደቅ አላማዎች እና ታፔላዎች እንዲሰቀሉ ማድረጉን ከከልሉ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ህገ ወጥ የወጣት አደረጃጀቶች ወደ ህጋዊ መስመር እንዲገቡ የተጀመረው ስራ አበረታች መሆኑን ጊዜያዊ ኮማንድ ፖስቱ አስታውቋል፡፡ ሀምሌ 11 ቀን 2011 ዓም በነበረው የጸጥታ ችግር ተጠርጥረው በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉት 1 ሺህ 384 ሰዎች ውስጥ የማጣራት ስራ በመስራት 481 ተጠርጣሪዎች የተለቀቁ ሲሆን ቀሪ 903 ተከሳሾች በክስ ሂደት ላይ መሆናቸውን ኮማንድ አስታውቋል፡፡
Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia