TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61K photos
1.55K videos
215 files
4.24K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ ታስረው ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡

አቶ ክርስቲያን በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሐምሌ 4 ቀን 2011 ዓ.ም. ነው፡፡ በፌዴራል ፖሊስ ታስረው የሚገኙ የአብን አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎችን ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እስር ቤት ጠይቀው ሲመለሱ መሆኑን የአብን ሊቀመንበር ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ አመራሮቻቸውና አባሎቻቸው የታሰሩት በቀዝቃዛ ቦታ፣ የፀሐይ ብርሃን በማያገኙበትና ቤተሰብ ሊጠይቃቸው በማይችል ሁኔታ በመሆኑ እንዲሻሻልላቸው ከፖሊስ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተው ሲወጡ፣ መውጫ በር ላይ አቶ ክርስቲያንን እንደያዟቸው ሊቀመንበሩ ተናግረዋል፡፡

በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው መርማሪ ፖሊስ በነጋታው ሐምሌ 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ፣ ምድብ ወንጀል ችሎት እንዳቀረባቸውም አስረድተዋል፡፡

መርማሪ ፖሊስ ለምን አቶ ክርስቲያንን በቁጥጥር ሥር እንዳዋላቸውና እንዳሰራቸው ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ፣ ተጠርጣሪው ወጣቶችን መሣሪያ እንደሚያስታጥቁና እንደሚያደራጁ በማስረዳት ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት መጠየቁም ታውቋል፡፡

ተጠርጣሪው አቶ ክርስቲያንም ወጣቶችን መመልመልና ማደራጀት ሥራቸው መሆኑንና ከእስርም ሲለቀቁ የሚቀጥሉት ሥራቸው እንደሆነ ተናግረው፣ መሣሪያ ያስታጥቃሉ ስለተባለው ግን ፖሊስ ማስረጃ ካለው እንዲያቀርብ ጠይቀዋል፡፡

ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ ፖሊስ ምርመራውን እንዲያጠናቅቅ የሰባት ቀናት ተጨማሪ ጊዜ በመፍቀድ፣ ለሐምሌ 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Via #Reporter
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ስብሰባውን ረግጦ የወጣ አንድም የማዕከላዊ ኮሜቴ አባል የለም።" #ደኢህዴን #SEPDM

"...በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ስብሰባውን ረግጠው የወጡ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አሉ ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ ከእውነት የራቀ መሆን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ ጓድ ሞገስ ባልቻ ገልፀዋል።" #ደኢህዴን

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአድዋ ማዕከል ግንባታ ተጀምሯል!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአድዋ ጀግኖችን ለመዘከር እና የታሪካዊ ድሉን ሁለንተናዊ ይዘት ለትውልድ ለማሻገር ሊገነባ የታሰበው የአድዋ ማዕከል በዛሬው ዕለት ግንባታው ተጀምሯል፡፡

የአድዋ ማዕከል ግንባታ ለረዥም ጊዜያት ሳይለማ በቆየው እና ከሚድሮክ ተመላሽ በተደረገው ቦታ ላይ የሚካሄድ ሲሆን የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ የሚሸፈን ይሆናል፡፡

የዓድዋ ማዕከል ግንባታው ሲጠናቀቅ ከሚሰጠው ማህበራዊና ታሪካዊ ፋይዳ በተጨማሪ በውስጡ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች በጥቂቱ ፦

✿ የአድዋ ሙዚየም
✿ ከ2000 ሰው በላይ የሚይዝ የዓድዋ አዳራሽ
✿ እያንዳንዳቸው 400 ሰው የመያዝ አቅም ያላቸው ሶስት አዳራሾች
✿ የሲኒማ አዳራሽ
✿ ቤተ-መፅሐፍ
✿ የስፖርት ማዘውተርያዎች እና ጂሞች
✿ የህፃናት መጫወቻ እና የማቆያ ስፍራ
✿ የጌጣጌጥ መደብሮች
✿ የቤተ-ስዕል ማዕከላት
✿ ዘመናዊ የባስ እና የታክሲ ማቆሚያ
✿ ከ600 መቶ መኪና በላይ የመያዝ አቅም ያለው ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ ተርሚናል
✿ ካፌዎች እና የምግብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት
✿ ለንባብ አገልግሎት የሚሆኑ የአረንጓዴ ስፍራ እና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

China Jiangsu International E.T.C.C በተባለ አለም አቀፍ ኩባኒያ ግንባታው የሚካሄደው የአድዋ ማዕከል በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ግንባታውን በማጠናቀቅ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሚደረግ ይሆናል፡፡

የማዕከሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ በውስጡ "ሁሉም ከዚህ ይጀምራል!" የሚል የአዲስ አበባ ከተማ 'ዜሮ(0.00) ኪ.ሜ' ምልክት ያርፍበታል፡፡

Via @mayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#መልካም_ዜና

በእሳት ቃጠሎ ጉዳት የደረሰበት የስሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የሳር ምድር ሙሉ ለሙሉ አገግሟል ተባለ፡፡ የፓርኩን የደን ሽፋን ለማሳደግ 50 ሺህ ችግኞች እንደሚተከሉም ተነግሯል፡፡

Via #ShegerFM
ፎቶ: ፋይል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from Joseph Joseph
አፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜውን ጨዋታ
በቴሌግራም ግሩፓችን
ገምተው ይሸለሙDon't forget subscribe our Telegram channel
Join @hopemusics @josehope
#NewsAlert

"ለሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የምርጫ ቦርድን ስራ በትእግስት መጠባበቅ ይገባል'" አቶ ቃሬ ጫዌቻ
.
.
#የክልልነት ጥያቄው በህገ-መንግስቱ መሰረት ምላሽ እንዲያገኝ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ስራ በመጀመሩ መላው የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በትዕግስት እንዲጠባበቁ የሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አስታወቁ።

ዋና አስተዳዳሪው አቶ ቃሬ ጫዊቻ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ የክልልነት ጥያቄ ዙሪያ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ እንዲቻል ቅድመ-ዝግጅቱን ጀምሯል።

ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ህዝበ ውሳኔውን ለማድረግ እንዲያስችል በደቡብ ክልልና በሲዳማ ዞን መከናወን ያለባቸውን ተግባራት በመለየት ማሳወቁንና እስከ ሐምሌ 19 ድረስ ዝርዝሩን በጽሁፍ ማቅረብ እንዲቻል የጊዜ ገደብ መስጠቱን አስታውቀዋል።

የሲዳማ ዞን አስተዳደር ከክልሉ መንግስትና ከደኢህዴን ጋር በመሆን በጥያቄው ዙሪያ በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙና ምርጫ ቦርድ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ በመግለጹ መላው የሲዳማ ተወላጆችና ወጣቶች ጉዳዩን በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

ቦርዱ በህዝበ ውሳኔ ማደራጀት ዙሪያ ከሲዳማ ዞንና ከክልሉ መንግስት ጋር በተለያዩ ጊዜያት መወያየቱን ያስታወሱት አቶ ቃሬ ህዝበ ውሳኔውን አምስት ወር ባልሞላ ጊዜ አደራጅቶ ለጥያቄው አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert አንድ ታጣቂ፣ በኢራቋ የኩርዶች ከተማ አረቢል ውስጥ በሚገኝ ሬስቶራንት ውስጥ በዛሬው ቀን በፈፀመው ጥቃት፣ እስካሁን በተረረጋገጠው መሠረት አንድ የቱርክ ዲፕሎማት መገደሉን፣ መንግሥዊው የቱርኩ ዜና አውታር ዘግቧል።

መንግሥታዊው ዜና አገልግሎት እንደዘገበው፣ የቱርክ ምክትል ዋና ቆንስላ የነበረው ዲፕሎማት አረቢል ውስጥ በሚገኘው የቆንስላ ጽ/ቤት በሥራ ገበታው ላይ ነበር። ሌሎች በርካታ ሰዎች መሞታቸውና መቁሰላቸው የተዘገበ ቢሆንም፣ እስካሁን ግን የሞቱትንም ሆነ የቆሰሉትን ሰዎች ቁጥር በትክክል ማወቅ አልተቻለም።

Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህር_ዳር_ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ መርሀ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 8 ሺህ የሚደርሱ ተማሪዎች የፊታችን ቅዳሜ ያስመርቃል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ዶክተር ፍሬው ተገኘ ለአብመድ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነው ሐምሌ 13/2011 ዓ.ም የሚያስመርቀው፡፡

በዕለቱም የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጦፋ ሙሃመድ ዑመር ለተመራቂዎች መልዕክት እንደሚያስተላልፉ ይጠበቃል፡፡ ርዕሰ መሥተዳድር ሙስጦፋ ከሀይማት አባቶች፣ ከጎሳ መሪዎች፣ ከመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ከልዩ ልዩ የኅብረሰተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ 100 የልዑክ አባሎቻቸውን ይዘው ወደ ባሕር ዳር እንደሚመጡ ነው የሚጠበቀው፡፡

የልዑኩ አባላትም የባሕር ዳርና አካባቢዋን የመስህብ ሥፍራዎች እንደሚጎበኙና የሕዝብ ለሕዝብ ትሥሥርን የሚያጠናክሩ ውይይቶችን እንደሚያካሂዱ ይጠበቃል፡፡

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቆቦ አካባቢ ተዘግቶ የነበረው መንገድ አሁን ተከፍቷል!

ጉዳዩ እንዲህ ነው: ትናንት አንድ ነዳጅ የሚጭን ቦቴ መኪና ባጃጅ ገጭቶ ወደ ሀረር ያመልጣል። እሱ መኪና ተመልሶ እንዲመጣ ለማስገደድ ከአዲስ አበባ ወደ ሀረር የሚወስደው መንገድ ላይ ቆቦ አካባቢ (ከጭሮ ትንሽ አለፍ ብሎ) መንገድ ተዘጋ። በዚህ ወቅት የአንዳንድ ቦቴ መኪኖች መስታወት ተሰብሯል። አሁን በምስሉ ላይ የሚታየው ገጭቶ አመለጠ የተባለው ቦቴ ወደ ስፍራው ስለተመለሰ መንገዱ ክፍት ሆኗል።

Via #Elias_Mesert

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ጉባ ቆሪቻ ወረዳ የእርሻ መሬትን ለማስፋፋት ከ1 ሔክታር መሬት በላይ የነበረ ደን ጨፍጭፈዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች እያንዳንዳቸው በአምስት ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን የወረዳው ፍርድ ቤት አስታወቀ።

የጉባ ቆሪቻ አቃቤ ህግ መላው ህብረተሰብ በችግኝ ተከላ ስራ በሚረባረብበት ወቅት ሐምሌ 2 ቀን 2011 ዓ.ም ለግል ጥቅማቸው ሲሉ 1 ሔክታር መሬት ደንን ጨፍጭፈዋል ባላቸው ሁለት ግለሰቦች ላይ ክስ ይመሰርታል።

ግለሰቦቹ በጎሮ ባቴ ቀበሌ በህዝብ የተተከለ ደንን የእርሻ መሬት ለማስፋፋት በሚል ምክንያት በመመንጠርና መሬቱን ለግል ጥቅም በማረስ ህገወጥ ተግባር ፈጥመዋል የሚለውን የአቃቤ ህግ ክስ የወረዳው ፍርድ ቤት ሐምሌ 9 ቀን 2011 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተመልክቶት የቅጣት ውሳኔው አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ ለኢዜአ እንደገለፀው አቶ ስለሺ ከበደና አቶ ንጉሱ ሰኢድ የተባሉት ተከሳሾች ጥተኞች ሆነው በመገኘታቸውና እራሳቸውን ከክሱ መከላከል ባለመቻላቸው የእስራት ቅጣት ውሳኔው ጸንቶባቸዋል።

Via ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባህር_ዳር_ዩኒቨርሲቲ

"በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው በነርቭ እና ድንገተኛ ህክምና ላይ ያተኮረው አለምዓቀፍ ኮንፈረንስ ዛሬ ማምሻውን ተጠናቋል።" A.ነኝ ከ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"....ወደ ኋላ እየተመለከቱ ወደፊት መጓዝ አይቻልም እንደሚባለው ሁሉ፤ እኛም የሚመጣውን ብሩህ እና ያማረ ጊዜ በማሰብ ሀገራችንን ከክፋት፣ ከችጋር፣ ከድንቁርና እና ከልመና ለማሻገር ባለመታከት መስራት ብቻ ሳይሆን መትጋት ግዴታችን ነው፡፡

የእኛ ትውልድ #በንግግር የሚያምን፤ በውይይት የሚግባባ፣ ራሱንም ሆነ ወንድሙን የሚያዳምጥ፣ ማዳመጥ ብቻ ሳይሆን በጋራ መፍትሄ የሚፈልግ ትንታግ ትውልድ እንጂ በጥላቻ እርስ በርሱ የሚገፋፋ የሚከፋፈል ከፍ ሲልም የሚገዳደል አይደለም፡፡

እኛ የዛሬ ተመራቂዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በሚገባ ተረድተን በመተባበር ፣ በመደጋገፍ ፣ ራሳችንን በእውቀት በማሳደግ ሀገራችንን በቅንነት ለማሻገር ከሚተጉት ጋር ሁሉ ወኔና ጉልበት በመሆን አደራችንን እንድንወጣ እየለመንኩ ፤ በሄዳችሁበት ቦታ ሁሉ መልካም ነገር የግጠማችሁ በማለት ንግግሬን በዚሁ እቋጫለሁ፡፡" አማኑኤል ኢቲቻ/የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳንትና የዘንድሮ ተመራቂ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች በደቡብ ሱዳንዋ በአብዬ ግዛት አንድ የተመድ ሰላም አስከባሪ እና አምስት ሰላማዊ ሰዎች መግደላቸው ተነገረ። የተመድ ትናንት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የተገደለው ሰላም አስከባሪ፣ ኢትዮጵያዊ ወታደር ነው። ሌሎች 5 ሰላማዊ ሰዎችም በጥቃቱ ተገድለዋል። አንድ ደግሞ ቆስሏል። በተመድ መግለጫ መሠረት ግድያው የተፈጸመው ሰላም አስከባሪዎቹ መደበኛ ቅኝት በማድረግ ላይ ሳሉ ነው። የአብዬ አስተዳዳሪ እንዳሉት ትናንት ከአብዬ በስተሰሜን በሚገኝ የገበያ ቦታ በተፈጸመው በዚሁ ጥቃት ከሞቱት መካከል አንድ ህጻን ይገኝበታል። በአወዛጋቢዋ በአብዬ ግዛት ከደቡብ ሱዳን ጋር መቀላቀል በሚፈልጉ እና ከሰሜንዋ ሱዳን ጋር መሆን በሚሹ መካከል ግጭት ሲካሄድባት ቆይቷል። ከጎርጎሮሳዊው 2011 አንስቶ የተመድ «ለአብዬ ጊዜያዊ የፀጥታ ኅይል» በምህጻሩ «UNISFA» የተባለ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ አሰማርቷል።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመብራት መቆራረጥ ችግር ቀጥሏል፦

የመብራት ፈረቃ ቀረ ከተባለ ወዲህም መብራት ከአምስት ቀን በላይ እየጠፋ ለችግር እየተጋለጡ መሆኑን የየካ ክፍለ ከተማ ፈረንሳይ አካባቢ ነዋሪዎች ገለጹ።

የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ ችግሩን በማጣራት ለመፍታት እንሰራለን ብለዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/M-07-17-381
"....ወደ ኋላ እየተመለከቱ ወደፊት መጓዝ አይቻልም እንደሚባለው ሁሉ፤ እኛም የሚመጣውን ብሩህ እና ያማረ ጊዜ በማሰብ ሀገራችንን ከክፋት፣ ከችጋር፣ ከድንቁርና እና ከልመና ለማሻገር ባለመታከት መስራት ብቻ ሳይሆን መትጋት ግዴታችን ነው፡፡ የእኛ ትውልድ #በንግግር የሚያምን፤ በውይይት የሚግባባ፣ ራሱንም ሆነ ወንድሙን የሚያዳምጥ፣ ማዳመጥ ብቻ ሳይሆን በጋራ መፍትሄ የሚፈልግ ትንታግ ትውልድ እንጂ በጥላቻ እርስ በርሱ የሚገፋፋ የሚከፋፈል ከፍ ሲልም የሚገዳደል አይደለም፡፡" #አማኑኤል_ኢቲቻ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"የሲዳማ ህዝብ የክልል ጥያቄውን #ለዘመናት ሲጠይቅ ቆይቷል፤ አሁን ግን ምላሽ አግኝቷል" አቶ ሚሊዮን ማትዮስ/የደ/ብ/ብ/ክ/መንግስት ፕሬዝዳንት/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
🎂ሁለተኛ አመታችንን ልናከብር ቀናቶች ቀርተውናል ዝግጁ ናችሁ?🎂

መልካምነትን ለትውልድ ያስተማሩ፣ በማንም ኢትዮጲያዊ ልቦና በበጎ ስማቸው የሚታወሱ፣ የህጻናቱ እናት፣ የደሀው ጧሪ፣ የታመሙትን አስታማሚ ፣ለተራበ አጉራሽ ለተቸገረ ደራሽ ብዙ ብዙ ባልን በወደድን ብቻ ሥራቸው ተዘርዝሮ አይዘለቅም፡፡

ከኢትዮጵያም አልፈው በአፍሪካም በዓለምም መልካምነትን የሰበኩ #ክብርት_ዶክተር_አበበች_ጎበና ክብር ይገባቸዋልና እናከብራቸዋለን፡፡

ዛሬ ላይ ስማቸው ላይጠፋ ከልባችን ተተክሏል ስራቸውስ?

ስንቱን ህጻን ያስተማረ ከጎዳና የታደገ እንደ እናት የተንከባከበ ድርጅታቸውስ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

እናታችንስ ዛሬ ላይ በምን አይነት የጤና ደረጃ ላይ ይገኛሉ?

ሐምሌ 21 ሁላችንም የቲክቫህ ቤተሰቦች በአበበች ጎበና የህጻናት እንክብካቤ እና ልማት ድርጅት #እንገናኝ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ማደራጀትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚናን አመልክቶ በተደጋጋሚ የሚጠየቁ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው፦

1.ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ክልልነት ጥያቄ 5 ወራት ይቀረዋል ያለው ለምንድነው?

ምንም እንኳን የሲዳማ ዞን ምክር ቤት የክልልነት ጥያቄውን ለደቡብ ክልል ያቀረበው ቀደም ብሎ ቢሆንም የማደራጀት ጥያቄውን ለምርጫ ቦርድ ያቀረበው በህዳር 11/2011 ዓ.ም በመሆኑ ቦርዱ ስለጥያቄው እውቅና ኖሮት ዝግጅት የሚጀምረው ከዚሁ ቀን አንስቶ በመሆኑ በተጨማሪም ቦርዱ የህዝበ ውሳኔን የማደራጀት ሃላፊነት የወሰደው ከክልሉ ምክር ቤት በውክልና በመሆኑ ውክልናው በይፋ ከተሰጠበት ከህዳር 11/2011 አንስቶ የቦርዱ ህገመንግስታዊ ገደብ የሚጠናቀቀው ከ5 ወር በኋላ ይሆናል፡፡

2. የምርጫ ቦርድ የሲዳማ ክልልነት ጥያቄ ላይ መልስ ሳይሰጥ እስካሁን ለምን ቆየ ?

እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፉት ስምንት ወራት በአዲስ አመራር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ የቆየ ሲሆን ዋና አላማውም ተቋሙ ተአማኒ እና ብቁ እንዲሆን የሚያደርጉትን ሪፎርሞች ማከናወን ነው፡፡

ከነዚህ ስራዎችም መካከል፦

- ከፍተኛ አቤቱታ ሲቀርብባቸው የነበሩ ህጎችን ለማሻሻል የተለያዩ ምክክሮችን ማድረግ ህጉን ማርቀቅና በተወካዮች ምክር ቤት ማጸደቅ

- በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎ ለወራት ያልተሟሉ የቦርድ አባላትን መሟላት ማስተባበር እና አዳዲስ የቦርድ አባላትን ማሟላት

- ድርጅታዊ መዋቅሮችን ማሻሻል

- የተለያዩ አካላት ጋር መስራት (ከፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሲቪክ ማህበራትና ምሁራን ጋር) ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ ዝግጅትን አስመልክቶ ከሚመለከታቸው የዞን እና የክልል አመራሮች፣ ከተወካዮች ምክር ቤት የሲዳማ ዞን ተወካዮችና ወጣቶች ጋር ውይይቶችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ ቦርዱ በተሟላለት በአንድ ወር ውስጥ አስቸኳይ ውሳኔ ከሰጠባቸው ጉዳዮች አንዱም የሲዳማ ህዝበ ውሳኔ ጥያቄ ነው፡፡

3. ምርጫ ቦርድ ባወጣው መግለጫ ላይ የተለያዩ መሟላት ያለባቸው ጉዳዮች ተጠቅሰዋል ፣ ምርጫ ቦርድ ያንን ለምን አለ ?

ከምርጫ አይነቶች አንዱ የሆነው ሕዝበ ውሳኔ የሚካሄደው ህዝቦች በነጻ መልኩ ምርጫቸውን እንዲያሳውቁ በመሆኑ ሒደቱ እንደማንኛውም ምርጫ የተለያዩ አካላትን ተሳትፎና ዝግጅት ይጠይቃል፡፡ በመሆኑም በህዝበ ውሳኔው ሂደት ላይ የሚመለከታቸው አካላት ሌሎች ምርጫዎች ላይ ዝግጅት እንደሚደረገው ሁሉ ለህዝበውሳኔም ዝግጅት እና ትብብር ማድረግ እንደሚገባቸው ለማመላከት ዋና ዋና የዝግጅት ጉዳዮችን ቦርዱ የሚመለከታቸው አካላትን በማስታወቅ ይሰራል፡፡ እነዚህ ዝግጅቶች መደረጋቸው የሚከናወነውን ህዝበ ውሳኔውን ሰላማዊ ተአማኒ እና ውጤታማ ያደርገዋል፡፡

4. አንዳንዶች ምርጫ ቦርድ በሲዳማ ክልልነት ህዝበ ውሳኔ ጉዳይ ላይ ፓለቲካዊ አቋም አለው ይላሉ፣ ለዚህ የቦርዱ ምላሽ ምንድነው ?

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋናው አላማው ስራውን በግልጽነት በመስራት ተአማኒ እና ብቁ የሆነ ተቋም መገንባት ሲሆን በምንም ምርጫንና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተቋሙ የፓለቲካ አቋም የለውም፣ አድሎም አያደርግም፡፡ በስራውም መሰረታዊ የምርጫ መርሆዎች የሆኑትን በነጻ ምርጫ ላይ መሳተፍ ፣ መረጃ የማግኘት፣ ሰላማዊ ውሳኔ መወሰን ላይ መሰረት በማድረግ ህገ መንግስቱን እና የምርጫ ህጎችን መሰረት አድርጎ የሚሰራ ተቋም ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የወላይታ ዞን አስተዳደር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል፦

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ በመግለጫው እንደገለጹት በደኢህዴን 10ኛው ጉባኤ ላይ በክልሉ በተለያዩ አካባቢዎች የሚነሡ የአደረጃጀት ጥያቄዎች በህገ መንግሥቱና በህዝቦች ፍላጎት ምላሽ እንዲያገኝ አቅጣጫ ማስቀመጡን አስታውሰዋል።

ድርጅቱ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የህዝቦችን ጥያቄ በጥናት ለመመለስ አጥኚ ቡድን ተቋቁሞ ባመጣው ምክረ ሀሳብ ውጤት እና በተለያዩ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ዙሪያ የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ላለፉት 11 ቀናት ሲመክር መቆየቱን ተናግረዋል።

በጥናቱ ምክረ ሀሳብ መሠረት የሲዳማ ህዝብ ክልል ሆኖ ከተደራጀ በኋላ ቀሪዎቹ የክልሉ ህዝቦች በአንድ ላይ ክልል ይሁኑ ተብሎ የቀረበው ምክረ ሀሳብ የወላይታ ህዝብ የክልል ጥያቄ ከዞን እስከ ቀበሌ ድረስ ባሉት እርከኖች ህዝቡ ተወያይቶበትና በየደረጃው ባሉት ምክር ቤቶች ፀድቆ ለደቡብ ክልል ምክር ቤት ታህሳስ 10/2011 ዓ.ም በፅሑፍ ቢቀርብም የክልሉ ምክር ቤት ባለመሰብሰቡ ለውሳኔ ሳይቀርብ መቆየቱን ተከትሎ ጥያቄው ለደቡብ ክልል ምክር ቤት በፍጥነት ቀርቦ ለሚመለከታቸው አካላት እንዲተላለፍ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ በግንቦት 9/2011 ዓ.ም በሠላማዊ ሰልፍ መጠየቁን ወደጎን የተወና የወላይታ ህዝብን ጥቅም የማያስከብር እና የክልል ጥያቄ የማይመልስ በመሆኑ የወላይታ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ሙሉ በሙሉ ሳይቀበሉ መድረኩን ረግጠው በልዩነት መውጣታቸውን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ ወንድም የሆነው የሲዳማ ህዝብ የክልል ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የወላይታ ህዝብን የወከሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በሙሉ ድጋፍ መስጠታቸውን ዋና አስተዳዳሪው ጠቁመዋል።

ሌሎቹ የክልሉ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች በአንድ ላይ መደራጀት አለባቸው የሚለውን ምክረ ሀሳብ የወላይታ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ባለመቀበላቸው የውሳኔ አካል አለመሆናቸውንም ጭምር አቶ ዳጋቶ ተናግረዋል።

የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ባረቀበው ምክረ ሀሳብ ላይ የያዘው አቋም የመጨረሻ ውሳኔ ባለመሆኑ የወላይታ ህዝብ የክልል ጥያቄ ምላሽ እስከሚያገኝ ድረስ የምያደርጉትን ሰላማዊ ትግል አጠናክረው እንደምቀጥሉ አረጋግጠዋል።

የወላይታ ህዝብ የክልል ጥያቄ ራስን በራስ የማስተዳደር የአደረጃጀት ጥያቄ እንጂ ከህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ጋር ቀጥተኛ መስተጋብር የሌለው መሆኑን በመግለጽ ከአጎራባች ህዝቦች ጋር ለረጅም ዘመናት የዘለቀውን የአብሮነትና የመቻቻል ባህላችንን የሚሸረሽር ባለመሆኑ አጎራባች ህዝቦችም ተገቢውን ድጋፍ እንዲሰጡም ጠይቀዋል።

የወላይታ ህዝብ የክልል ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ እንዲቀጥል ህዝቡ በተለይም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል በተረጋጋ እና በሰከነ መንገድ ሰላማዊ ትግል እንዲያደርግ ጥሪ ያቀረቡት ዋና አስተዳዳሪው መላው የዞኑ ህዝብ ከዚህ ቀደም በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ያሳየው የአብሮነትና የመቻቻል ባህሉ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።

Via Wolaita Zone Administration Public Relation Office

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሲዳማ ህዝብ የክልል ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ የወላይታ ህዝብን የወከሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት #በሙሉ ድጋፍ መስጠታቸውን የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኩምቤ በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሀዋሳ

"ከሀምሌ 11 ጋር ተያይዞ ስጋት ውስጥ የሚጥሉ ነገሮች የሉም" አቶ #ሚሊዮን_ማቲዮስ/የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት/
.
.
የሲዳማ የክልልነት ጥያቄን አስመልክቶ በዞኑ የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎችን ስጋት ላይ የሚጥሉ ጉዳዮች እንደሌሉ፤ ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮችን በቅርበት እየተከታተሉ እንደሆነ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ ተናገሩ። ከሀምሌ 11 ጋር በተያያዘም ዜጎችን ስጋት ላይ የሚጥል ምንም ነገር የለም ብለዋል።

ክቡር ፕሬዘዳንቱ የተናገሩትን ቃል በቃል ከዚህ በታች እንድታነቡት ፅፌላችኃለሁ፦

"የሀዋሳ ከተማን ነዋሪ ወደስጋት ሊጥሉ የሚችሉ ጉዳዮችን በቅርበት እየተከታተልን ከህዝቡ ጋር በመሆን ምላሽ ለመስጠት ሰፊ ስራዎችን ስንሰራ ነው የቆየነው። አሁንም ቢሆን በዚህ ጉዳይ ላይ በተለይም ከሲዳማ አንፃር የተነሳውን ጥያቄ ተንተርሶ ስጋት ውስጥ የሚያስገቡት ነገሮች እንዳሉ ሚደመጡ ነገሮች አሉ ግን ደግሞ የሲዳማ ህዝብ ጥያቄውን ሰላማዊ በሆነ መልኩ ሲያቀርብ ነው የቆየው ይሄ በተለያየ ሂደት አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ የደረሰ በመሆኑ አሁን ባለንበት ሁኔታ የከተማችንን ፀጥታ የሚያውክ ነገር ይፈጠራል ብለን የምንጠብቀው ነገር የለም። ከሀምሌ 11 ጋር ተያይዞ ስጋት ውስጥ የሚጥሉ ነገሮች የሉም የሚል ነገር ነው እየገለፅኩ ያለሁት።"

#TIKVAH_ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia