TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ስያሜያቸው "ብሄር ተኮር" የሆኑ የእግር ኳስ ክለቦች ከቀጣዩ ዓመት ጀምሮ ስያሜያቸውን እንዲያስተካክሉ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ ፌዴሬሽኑ የእግር ኳስ ሜዳዎች ውስጥ ጠብ የማይቆም ከሆነ ጨዋታዎች ካለ ተመልካች እንዲካሄዱ የሚያደርግ ርምጃ ሊወስድ እንደሚችል አክሎ ገልጿል፡፡

Via VOA Amharic
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በጌዲዮና በምዕራብ ጉጂ ዞን ተፈናቅለው የነበሩና ወደ ቀያቸው የተመለሱ ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችል ለአራት ዓመት የሚቆይ መርሃ ግብር ይፋ ተደረገ። መርሃ ግብሩን የተባበሩት የመንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም የሚመራው ሲሆን፥ 20 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚያስፍልግ መሆኑም የብሄራዊ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

Via #fbc
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ #አስቸኳይ ስብሰባ ማድረግ ጀምሯል፡፡ #ደኢሕዴንም ስብሰባ እያካሄደ ነው፤/የደኢህዴን ስብሰባ ለ3 ቀናት ተብሎ ነበር የተጀመረው ስብሰባው ዛሬም #እንደቀጠለ ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢ/ር ታከለ ኡማ ከጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዶ/ር አሚን አማን ጋር በመሆን የጥቁር አንበሳ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የእድሳት በዛሬው ዕለት አስጀምረዋል፡፡ ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የጥቁር አንበሳ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ላለፉት በርካታ ዓመታት የውስጥም ሆነ የውጪ እድሳት ሳይደረግለት ቆይቷል፡፡

Via @mayorofficeAA
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#NewsAlert በሲዳማ ዞን የሚንቀሳቀሱ ሦስት የፖለቲካ ፓርቲዎች የሲዳማ ህዝብ በክልል ለመደራጀት የቀረበውን የህዝበ ውሳኔ ቀን በአስቸኳይ ይፋ እንዲደረግ ጠየቁ። ጥያቄውን ያቀረቡት የሲዳማ አርነት ንቅናቄ «ሲአን»፣ የሲዳማ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ «ሲብዴ ፓ» እና የሲዳማ ሀድቾ ዴሞክራሲያዊ ደርጅት« ሲሀዴ ድ» ናቸው ።

Via #DW
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ከተማ 249 የጦር መሳሪያዎች መያዛቸውን የከተማው ፖሊስ አስታወቀ። የከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ጉተን ሌሊሳ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት76 ሽጉጦች፣ 138 ጠብመንጃዎችና 35 ጩቤዎች የተያዙት ሰሞኑን በመኖሪያ ቤትና በኬላ ላይ በተደረገ ፍተሻ ነው። ከዚህም በተጨማሪ 90 የሺሻ እቃዎች መያዛቸውንም ተናግረዋል፡፡ ኮማንደር ጉተን እንዳሉት መሳሪያዎቹ ሊያዙ የቻሉት ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ በተደረገ ክትትል ነው። ወንጀልን በጋራ ለመከላከል ህብረተሰቡ ላደረገው ትብብር ኮማንደሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Via #ኢዜአ
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNews የአማራ ክልል ልዩ ኃይል #ሊፈርስ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ/በተለይም በfacebook/ የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#FakeNews ሌተናል ጄነራል #ሃሰን_ኢብራሂም ታሰሩ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #ሀሰት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ጎንደር #Gondar

ጎንደር ከተማ #ሰላማዊ መሆንዋን ምክትል ከንቲባ በሪሁን ካሣዉ ገልፀዋል። ትላንት አነስተኛ ውዝግብ ከተማ ውስጥ መፈጠሩን ያነሱት ምክትል ከንቲባው የነበረውን አነስተኛ ዉዝግብ ተጠቅመዉ ረብሻ ለማስነሳት የሞከሩ እና አንዳንድ ያልተገባ ነገር ለመፈፀም የሞከሩ፤ ድርጊታቸዉን ሳይፈፅሙ በቁጥጥር ስር አውለናቸዋል፤ #ከጀርባቸዉ ማን እንዳለም እያጣራን ነዉ ሲሉ ለጀርመን ራድዮ ተናግረዋል።

Via #DW
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በትላንትናው ዕለት በጎንደር ከተማ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር አንዳንድ የንግድ ተቋማት ላይ #ጉዳት መድረሱን፤ የደረሰውን የጉዳት መጠንም የማጣራት ስራ መጀመሩን #የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኦፊሰር ኮማንደር ማረልኝ ወንድሙ ተናግረዋል። በጥፋቱ የተሳተፉ ግለሰቦችም በቀጣይ የማጣራት ስራ ከተከናወነ በኋላ በህግ #ተጠያቂ እንደሚደረጉም ገልፀዋል።

🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ሙሉ በሙሉ ለባለሀብቶች ሊሰጥ ነው፡፡ ከሆንግ ኮንግ የመጡ የባለሀብቶች ቡድን አባላት የኢንዱስትሪ ፓርኩን #ነገ እንደሚረከቡ ታውቋል፡፡

Via #AMMA
🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአገር አቀፍ ደረጃ ተከስቶ የነበረው የኮሌራ ወረርሽኝ በሽታ #እየቀነሰ ቢሆንም ህብረተሰቡ ሳይዘናጋ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳስቧል።

ተጨማሪ ያብቡ👇
https://telegra.ph/CH-07-09
#update አትሌት ደራርቱ ቱሉ በኢጣልያ በተካሄደ ዓለም አቀፍ ሽልማት የህይወት ዘመን የስፖርታዊ ጨዋነት ዘርፍ ተሸላሚ ሆነች። ሽልማቱ ኢጣልያ በሚገኝ ”ፕሪሞ ኢንተርናሽናል ፌር ፕሌይ” በተሰኘ ድርጅት በስፖርቱ ታሪክ የሰሩ፣ በታማኝነት የተወዳደሩ እና ዘርፉን ያገለገሉና ስፖርትን በማስፋፋት ታሪክ ለሰሩ ግለሰቦችና ተቋማት እውቅና የሚሰጥበት ነው።

🗞ቀን ሃምሌ 2/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የአዲስ_አበባ_ሞተረኞች...

የሞተር ብስክሌት #እገዳው በኑሯቸው ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን–የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ተናግረዋል።

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/Mot-07-09-2
የዕለቱ መልዕክት፦

"ሰዎች ንቃተ–ህሊና ቢኖራቸው ኖሮ በአለም ላይ በርካታ #ጦርነቶችን ማስወገድ ይችሉ ነበር!" #ጉጅረየፍ
___________________________________________

ህሊናዊ ንቃት ማለት #እውነታውንና #ገሀዳዊውን አለም በትክክል #መረዳት ማለት ነው፤ ይህ ብቻ ሳይሆን አንድ ሰው እርሱም ሆነ ሌሎች የሚያደርጉትን ነገር ውጤቱን ወይንም #መዘዙን የሚረዳ መሆን አለበት።

ራሳችንን እንፈትሽ!
ሰላም እደሩ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቅዱስ ጊዮርጊስ እግር ኳስ ቡድን ‹‹ፍትሕ ካልተሰጠኝ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በሚያዘጋጀው ማንኛውም ውድድር አልሳተፍም›› ብሏል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/STG-07-10

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert የፌደራሉ ጠቅላይ አቃቢ ህግ በቀድሞ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አማረ አምሳሉን ጨምሮ 10 የሥራ ኃላፊና ሰራተኞች ላይ ክስ መሰረተ።

አቃቢ ህግ በክሱ እንዳመላከተው፤ ተከሳሾች በሶማሌ ክልል የሞባይል ማስፋፊያ የግንባታ የአገልግሎት ግዢ ውል በሚከናወንበት ወቅት ለራሳቸው ብሎም ለብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ጥቅም ለማስገኘት በማሰብ የኢትዮ ቴሌኮምና የመንግስት የግዢ አፈፃፀም መመሪያን ወደጎን በመተው ያለ ውድድር ከ221 ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ገንዘብ ላይ ጉዳት በማድሳቸው ነው።

እንዲሁም 51 የኢትዮቴሌኮም ፕሮጀክቶች ሳይጠናቀቁ ከደንብና መመሪያ ውጪ ርክክብ ሳይደረግ ገንዘብ መክፈላቸውም በክሱ ላይ ተመልክቷል።

Via #ENA
🗞ቀን ሃምሌ 3/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በማዕድን ዘርፉ የተሰማሩ ድርጅቶች ሥራቸውን በተለያየ ምክንያት አቋርጠው ወጥተዋል እየተባለ ያለው #ሀሰት መሆኑን የማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዓለም ዓቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞች መታሰር እንዳሳሰበው ትላንት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/AMN-07-10
Forwarded from TIKVAH-SPORT
ሞሮኳዊው የዳኛ ባምላክ ደብዳቢ ተቀጡ!

ኢትዮጵያዊውን ኢንተርናሽናል አርቢትር ባምላክ ተሰማን የደበደቡት የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት፣ የካፍ ምክትል ፕሬዚዳንትና የሞሮኮው ቤርካን ክለብ የክብር ፕሬዚዳንት ፉዚ ሌክጃ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን የዲስፕሊን ኮሚቴ ለአንድ አመት ከማንኛውም ስፖርታዊ አመራር ታግደዋል።

Via #PetrosAshenafi
@tikvahethsport
#update የአዲስ አበባ አዴፓ ኮሚቴ በአማራ ክልል መስዋእት ለሆኑ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ቤተሰቦች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ለተጎጂ ቤተሰቦች የመስርያ ቦታ ድጋፍ አድርጓል፡፡ የአዲስ አበባ አዴፓ ኮሚቴ ከከተማው ህብረተሰብ በአጭር ቀናት ውስጥ ያሰባሰበውን ከ5 ሚሊዮን በላይ ገንዘብ በአማራ ክልል ሰኔ 15 መስዋእት ለሆኑት አመራሮች ቤተሰቦች ለሶስቱም ቤተሰቦች በእኩል መጠን ትናንት በሸራተን አዲስ ሆቴል ለተጎጂዎቹ ማስታወሻ በተዘጋጀ ስነ ስርዓት ላይ አበርክቷል፡፡

Via #EPA
🗞ቀን ሃምሌ 3/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia