TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በአማራ ክልልና በኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ የተፈጠረውን ግጭት ተከትሎ ከመተሃራ ከተማ ተፈናቅለው በአዋሽ ከተማ ለተጠለሉ ዜጎች እርዳታ ተጠየቀ። በግጭቱ የ7 ሰዎች ህይዎትም አልፏል።

Via ELU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በሚያስተዳድራቸው ሁለት መቶ ያህል ወረዳዎች እና 20 የዞን አስተዳደሮች በሀላፊነት ያስቀመጣቸውን አመራሮች በአዳዲስ ለመተካትና አንዳንዶቹንም በአዲስ ሀላፊነት ለመሾም እየተዘጋጀ መሆኑ ተሰምቷል። ዋዜማ ራድዮ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸው ምንጮች ሰምቻለሁ እንዲሁም ከክልሉ አንድ ከፍተኛ ተሿሚ አረጋግጫለሁ ብሎ እንደዘገበው የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) በሚያስተዳድረው የኦሮምያ ክልል የተሻለ #ብቃትና #ልምድ ያላቸውን አመራሮች ለመመደብ ዝግጅቱን አጠናቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ #አብራሪዎቹን ለማሰልጠን የሚያስችሉ የተሟሉ ሰባት ምስለ በረራዎች ወይም የበረራ ማሰልጠኛዎች አሉት።

•በአሁን ወቅት ብቁና የተሟሉ ኪው 400፣ ቢ737 ኤን ጂ፣ ቢ 737 ማክስ፣ ቢ 767 ፣ ቢ 787 ፣ ቢ 777 እና ኤ 350 የተሰኙ ሰባት ምስለ በረራዎች አሉት።

•በዋሽንግተን ፓስት የወጣው መረጃ በመረጃ ላይ ያልተደገፈና #የተሳሳተ ነው።

•ማነነታቸው ካልታወቁ አካላት ተገኙ ተብሎ የሚሰራጨው መረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ከበረራ ስለታገደው #ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን ትኩረት ለማስቀየር ነው፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሁን🔝

የአፄ ቴዎድሮስ ፀጉር (ቁንዳላ) በኢትዮጵያ ብሄራዊ ሙዚየም አቀባበል እየተደረገለ ነው፡፡ በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ አርበኞች፣ አርቲስቶች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከ150 ዓመታት በላይ በብሪታኒያ የቆየውን የንጉሱን ቁንዳላ የኢትዮጵያ መንግስት መጋቢት 11/2011 ዓ.ም ነበር በይፋ የተረከበው፡፡ የኢፌዴሪ መንግስት በባህል እና ቱሪዝም ሚንስትር በኩል በልዩ ልዩ መንገዶች ከሀገር የወጡ ቅርሶችን የማስመለስ ስራ አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል፡፡

Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ‼️

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመላ ሀገሪቱ ለተፈናቀሉ ዜጎች የ100 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ። ባንኩ ከብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በገኝው የተፈናቃዮች መረጃ መሰረት ከንዘቡን ለክልሎች እንደሚከተለው ማከፋፈሉን አስታውቋል፦

•ለሶማሌ ክልል 35 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር፣

•ለኦሮሚያ ክልል 33 ነጥብ 1 ሚሊየን ብር፣

•ለደቡብ ክልል 18 ሚሊየን ብር፣

•ለአማራ ክልል 4 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር፣

•ለትግራይ ክልል 3 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር፣

•ለቤኒሻንጉልጉሙዝ ክልል 3 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር፣

•ለጋምቤላ ክልል 454 ሺህ ብር፣

•ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር 387 ሺህ ብር እና ለሀረሬ ክልል 62 ሺህ ብር ባንኩ ድጋፍ አድርጓል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ያለፈውን አንድ ዓመት በኢትዮጵያ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖሊቲካዊ የለውጥ ሂደትን የሚቃኘው አዲስ ወግ መድረክ የሁለተኛ ቀን ውይይት እየተካሄደ ይገኛል። አዲስ ወግ የመቻቻልና የመከባበር ውይይትና የንግግር ባሕልና የሚያስተዋውቅ መድረክ ነው። መጋቢት 14 ቀን 2011 ጠዋት እየተደረጉ ባለው ውይይት አቶ ደሳለኝ ራሕማቶ፣ ዶ/ር ሰዒድ ኑሩ፣ አቶ ኢየሱስ ወርቅ ዛፉና ወ/ሮ ብርሃኔ አሰፋ የኢትዮጵያ ምጣኔ ሀብት፤ የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ሥራ ፈጠራና ማኅበራዊ አካታችነት ዙሪያ በግብርና ምርታማነት፣ የጥቅል ኢኮኖሚው ሚዛን መዛባትና የዕዳ ጫና ላይ በስፋት እየተወያዩ ነው።

#PMOEthiopia #አዲስወግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia