#update መጋቢት 29 በሚጀመረው የህዝብና ቤት ቆጠራ ግጭት ያለባቸው አካባቢዎችና #የተፈናቀሉ ዜጎችን ያማከለ ቆጠራ እንደሚካሄድ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ግጭት ያለባቸው አካባቢዎችንና የተፈናቀሉ #ዜጎችን ጉዳይ በተመለከተ እያንዳንዱ ክልል ከለውጡ በኋላ ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ ከሁለት ወራት በፊት ስብሰባ ተደርጎ መገምገሙን በኤጀንሲው የህዝብ ግንኙነትና መረጃ አሰባሰብ ዳይሬክተር አቶ ሳፊ ገመዲ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ሁሉም ክልል የየራሱን ሪፖርት ካቀረበ በኋላ፣ የቆጠራ ኮሚሽኑ መሰረታዊ ነጥቦች ላይ በሰፊው ውይይት አድርጎ ውሳኔ ማስተላለፉን ኃላፊው አመልክተዋል፡፡ በዚህም ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች የህዝብና ቤት ቆጠራውን ለማካሄድ እንደ አማራጭ ክልሎች በአስቸካይ ተነጋግረው ችግሮችን በፈቱባቸው አካባቢዎች የቆጠራ ካርታ መሰራቱንም ገልጸዋል፡፡ አቶ ሳፊ እንደሚሉት ክልሎች ችግሩን መፍታት ባልቻሉባቸውና የቆጠራ ካርታ ባልተሰራባቸው አካባቢዎች ‘’ልዩ የቆጠራ ቦታ’’ ‘’Special Enumeration area’’ ተብሎ ተይዞ ቆጠራው ይካሄዳል።
Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል በ1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር የማስፋፊያ ግንባታ እያካሄደ መሆኑን አስታውቋል።
ምንጭ፦ አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update 9 ፐርሰንቱ የኢትዮጵያ ህዝብ እርዳታ ፈላጊ ሆኗል ተባለ። መንግስት ዛሬ በሰጠው መግለጫ እንዳመለከተው 8.8 ሚልዮን ኢትዮጵያውያን የሰብአዊ #እርዳታ ይሻሉ ብሏል። ከፍተኛው እርዳታ ፈላጊ በኦሮሚያ ክልል (3.88 ሚልዮን) ሲሆን የሶማሌ ክልል 1.8 ሚልዮን ተረጂዎች አሉበት። በአማራ ክልል ደሞ ወደ 980,000 እርዳታ ፈላጊዎች እንዳሉ ገልጿል። ለዚህም መንግስት የ1.3 ቢልዮን ዶላር ገንዘብ #ያስፈልገኛል ብሎ ለእርዳታ ድርጅቶች እና ለጋሽ ሀገራት ጥሪ አቅርቧል። ከእርዳታ ፈላጊዎች ውስጥ 3.1 ሚልዮኑ ተፈናቃዮች ሲሆኑ ይህም በብሄር ተኮር ግጭት የተሰደዱ ናቸው ተብሏል።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሠረት(https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሠረት(https://www.facebook.com/Elias-Meseret-517243322140049/)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኦሮሚያ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ‼️
(20/80ና 40/60)
የ20/80ና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ይፋ ከመሆን ጋር ተያይዞ ቦታው የኦሮሚያ ነው በሚል ከ10 በላይ በሚሆኑ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞዎች ተቀስቅሰዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሆነው የአዲስ አበባ መስተዳድር ውሳኔ የሚያሳልፈው እንዴት ነው፤ ለተፈናቃዮቹ አርሶ አደሮች የተሰጠው ካሳ እዚህ ግባ የማይባል ነው፤ የተቀናጀው ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ሀሳቦችን ተቃዋሚዎቹ አንስተዋል።
#በምስራቅ_ኦሮሚያ ጪሮ ከተማ ቢቢሲ ያነጋገረው አንድ ሰልፈኛ " በዚህ ተቃውሞ ላይ ዋነኛ መልዕክታችን በአዲስ አበባ አካባቢ ያሉት መሬቶች ለኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ሊመለስ ይገባል" የሚል ነው። ተቃዋሚው ጨምሮም ለብዙዎች ሞት ምክንያት የሆነው አወዛጋቢው የተቀናጀ ማስተር ፕላን ሊመለስ አይገባም ብሏል።
ተቃውሞዎቹ በሻሸመኔ፣ ጪሮ፣ ጂማ፣ አሰላ፣ አዳማና ሂርና ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የተስፋፉ ሲሆን በሻሸመኔ አካባቢ የሚገኙ ሰልፈኞች "ኦዲፒ ያልነውን ረስታችሁታል፤ መሬታችን የደም ስራችን ነው" የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ነበር።
በትናንትናው ዕለት 51 ሺህ 229 የጋራ መኖሪያ ቤቶች በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የዕጣ ማውጫ ስነ ስርአት ለተጠቃሚዎች የተላለፈ ሲሆን፤ ከአካካቢው ለተነሱ አርሶ አደሮችና ልጆቻቸው ያለ እጣ እንዲሰጣቸው በከተማው አስተዳደር ካቢኔና በቤቶች አስተዳደር ውሳኔ መሰረት ያለ ዕጣ እንዲተላለፍ መወሰኑን ምክትል ከንቲባ #ታከለ_ኡማ በትናንትናው ዕለት ገልፀዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ሲገነቡ የተጎዱ ሰዎች እንዳሉ ያልደበቁት ምክትል ከንቲባው "በተለይም የእርሻ መሬታቸውን ለነዚህ ተግባራት ሲሉ የለቀቁና ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ቀውስ የተዳረጉ የአርሶ አደር ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ህመማችሁ የእኛ መሆኑን እንድታውቁ" የሚል መልእክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ከንቲባው ይህንን ቢሉም ኦሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለረጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ የሚነገርለትና ከ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ትችቶችም እየተሰሙ ነው።
ምንም እንኳን የተቀናጀው ማስተር ፕላን ከፍተኛ ተቃውሞዎችን ተከትሎ ውድቅ ቢደረግም የቀድሞው የአዲስ አበባ ከንቲባና ኦህዴድ ሊቀ መንበር አቶ ኩማ ደመቅሳ ጉዳዩ ከመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ "ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል" ብለው ለቢቢሲ መናገራቸው የሚታወስ ነው።
ምንም እንኳን ከመንግሥት በኩል ምንም አይነት መግለጫ ባይሰጥም በቅርቡ ከውጭ ሀገር የተመለሰው የተባበሩት ኦነግ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ያለውን ድንበር መወሰን ያለበት የኦሮሚያ ክልል ነው የሚል ነው።
በ13ኛው ዙር የ20/80 ቤቶች 32ሺ 653 ቤቶችና በ2ኛ ዙር የ40/60 ቤቶች ለተጠቃሚዎች የሚተላለፉ ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 1ሺ 248 ስቱዲዮ፣ 18ሺ 823 ባለ አንድ መኝታ፣ 7ሺ 127 ባለሁለት መኝታ እና 5ሺ455 ደግሞ ባለ ሶስት መኝታ መሆናቸው ተገልጿል።
በ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውስጥ የሚካተቱትም በ1997 ተመዝግበው በ2005 ዓ.ም በነባር መደብ የተመዘገቡና በ2005 ዓ.ም የአዲስ ባለ ሶስት መኝታ ተመዝጋቢ ደንበኞች መሆኑ ተገልጿል።
Via BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
(20/80ና 40/60)
የ20/80ና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ይፋ ከመሆን ጋር ተያይዞ ቦታው የኦሮሚያ ነው በሚል ከ10 በላይ በሚሆኑ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞዎች ተቀስቅሰዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ የተገነቡባቸው አካባቢዎች በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሆነው የአዲስ አበባ መስተዳድር ውሳኔ የሚያሳልፈው እንዴት ነው፤ ለተፈናቃዮቹ አርሶ አደሮች የተሰጠው ካሳ እዚህ ግባ የማይባል ነው፤ የተቀናጀው ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ሀሳቦችን ተቃዋሚዎቹ አንስተዋል።
#በምስራቅ_ኦሮሚያ ጪሮ ከተማ ቢቢሲ ያነጋገረው አንድ ሰልፈኛ " በዚህ ተቃውሞ ላይ ዋነኛ መልዕክታችን በአዲስ አበባ አካባቢ ያሉት መሬቶች ለኦሮሚያ ክልል አስተዳደር ሊመለስ ይገባል" የሚል ነው። ተቃዋሚው ጨምሮም ለብዙዎች ሞት ምክንያት የሆነው አወዛጋቢው የተቀናጀ ማስተር ፕላን ሊመለስ አይገባም ብሏል።
ተቃውሞዎቹ በሻሸመኔ፣ ጪሮ፣ ጂማ፣ አሰላ፣ አዳማና ሂርና ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የተስፋፉ ሲሆን በሻሸመኔ አካባቢ የሚገኙ ሰልፈኞች "ኦዲፒ ያልነውን ረስታችሁታል፤ መሬታችን የደም ስራችን ነው" የሚሉ መፈክሮችን ይዘው ነበር።
በትናንትናው ዕለት 51 ሺህ 229 የጋራ መኖሪያ ቤቶች በኢንተር ኮንቲኔንታል ሆቴል የዕጣ ማውጫ ስነ ስርአት ለተጠቃሚዎች የተላለፈ ሲሆን፤ ከአካካቢው ለተነሱ አርሶ አደሮችና ልጆቻቸው ያለ እጣ እንዲሰጣቸው በከተማው አስተዳደር ካቢኔና በቤቶች አስተዳደር ውሳኔ መሰረት ያለ ዕጣ እንዲተላለፍ መወሰኑን ምክትል ከንቲባ #ታከለ_ኡማ በትናንትናው ዕለት ገልፀዋል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ሲገነቡ የተጎዱ ሰዎች እንዳሉ ያልደበቁት ምክትል ከንቲባው "በተለይም የእርሻ መሬታቸውን ለነዚህ ተግባራት ሲሉ የለቀቁና ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ቀውስ የተዳረጉ የአርሶ አደር ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ህመማችሁ የእኛ መሆኑን እንድታውቁ" የሚል መልእክት አስተላልፈዋል።
ምክትል ከንቲባው ይህንን ቢሉም ኦሮሚያ ውስጥ ተቀስቅሶ ለረጅም ጊዜ ለዘለቀው ሕዝባዊ ተቃውሞ መነሻ ምክንያት እንደሆነ የሚነገርለትና ከ2006 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የአዲስ አበባና በዙሪያዋ ያሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ ማስተር ፕላን ቅጥያ ነው የሚሉ ትችቶችም እየተሰሙ ነው።
ምንም እንኳን የተቀናጀው ማስተር ፕላን ከፍተኛ ተቃውሞዎችን ተከትሎ ውድቅ ቢደረግም የቀድሞው የአዲስ አበባ ከንቲባና ኦህዴድ ሊቀ መንበር አቶ ኩማ ደመቅሳ ጉዳዩ ከመፈናቀል ጋር አብሮ ስለመጣ እንጂ "ተራማጅ አስተሳሰብ ነው ብዬ አስባለሁ፤ ጊዜ ሊወስድ ይችላል እንጂ ማስተር ፕላኑ አንድ ቀን ተመልሶ ይመጣል" ብለው ለቢቢሲ መናገራቸው የሚታወስ ነው።
ምንም እንኳን ከመንግሥት በኩል ምንም አይነት መግለጫ ባይሰጥም በቅርቡ ከውጭ ሀገር የተመለሰው የተባበሩት ኦነግ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ያለውን ድንበር መወሰን ያለበት የኦሮሚያ ክልል ነው የሚል ነው።
በ13ኛው ዙር የ20/80 ቤቶች 32ሺ 653 ቤቶችና በ2ኛ ዙር የ40/60 ቤቶች ለተጠቃሚዎች የሚተላለፉ ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 1ሺ 248 ስቱዲዮ፣ 18ሺ 823 ባለ አንድ መኝታ፣ 7ሺ 127 ባለሁለት መኝታ እና 5ሺ455 ደግሞ ባለ ሶስት መኝታ መሆናቸው ተገልጿል።
በ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውስጥ የሚካተቱትም በ1997 ተመዝግበው በ2005 ዓ.ም በነባር መደብ የተመዘገቡና በ2005 ዓ.ም የአዲስ ባለ ሶስት መኝታ ተመዝጋቢ ደንበኞች መሆኑ ተገልጿል።
Via BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ አካባቢ አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል የስራ ባልደረባውና #ባለቤቱ የሆነችውን የፖሊስ አባል ዛሬ ረፋድ ላይ በጥይት #መግደሉ ተሰማ። የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ምክትል ሃላፊ ኮማንደር #ተስፋዬ_ምትኩ ለኢዜአ እንደገለጹት ተጠርጣሪው የፖሊስ አባል የሆነችውን የትዳር አጋሩን ስድስት ኪሎ በሚገኘው የፌዴራል ፖሊስ ካምፕ መግደሉን አረጋግጠዋል። መንስኤው ገና #በመጣራት ላይ ቢሆንም ግድያው የተፈፀመው በመካከላቸው በተፈጠረው ጊዜያዊ አለመግባባት መሆኑም ታውቋል።
Via ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethioia
Via ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethioia
#update በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 105 #ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያ #በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ ህገወጥ የጦር መሳሪያው በቁጥጥር ስር የዋለው ትናንት ለሊት #በቡራዩ_ከተማ ነው፡፡ የጦር መሳሪያው በአይሱዙ ተሽከርካሪ ውስጥ ተጭኖ #ከጋምቤላ ወደ #አማራ_ክልል ሊጓጓዙ የነበረ ነው ተብሏል፡፡ የተያዘው የጦር መሳሪያ 42 ታጣፊና 63 ባለሰደፍ በድምሩ 105 ክላሽንኮቮች፣ 95 #የክላሽንኮቭ_መጋዝኖች እና 5 ጥይት ነው፡፡ ከአይሱዙ ኤፍ.ኤስ.አር የጭነት #ተሽከርካሪው ፊት በመሄድ ሁኔታዎችን #ሲያመቻች የነበረ አንድ ዶልፊን ሚኒባስም ተይዟል፡፡
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
(የካቲት 27/2011 ዓ.ም.)
#የሀዋሳ_ኢንዱስትሪ_ፓርክ ሠራተኞች ሥራ የማቆም አድማ መትተዋል። ሠራተኞች አድማ የመቱበት #ምክንያት በተደጋጋሚ ጊዜ አቅርበናል ያሉት #የደመወዝ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ መሆኑን ተናግረዋል። ሠራተኞቹ #ደኅንነታቸው እንደማይጠበቅና ለፆታዊ ጥቃትና ለዝርፊያም እንደሚጋለጡ ገልፀዋል።
በኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥራ አስኪያጅ አቶ #በላይ_ኃይለሚካኤል “ችግሩ የአንዳንድ ኩባንያዎችና የአስተዳደር በደል ነው” ብለዋል።
ምንጭ፦ VOA አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የሀዋሳ_ኢንዱስትሪ_ፓርክ ሠራተኞች ሥራ የማቆም አድማ መትተዋል። ሠራተኞች አድማ የመቱበት #ምክንያት በተደጋጋሚ ጊዜ አቅርበናል ያሉት #የደመወዝ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ መሆኑን ተናግረዋል። ሠራተኞቹ #ደኅንነታቸው እንደማይጠበቅና ለፆታዊ ጥቃትና ለዝርፊያም እንደሚጋለጡ ገልፀዋል።
በኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥራ አስኪያጅ አቶ #በላይ_ኃይለሚካኤል “ችግሩ የአንዳንድ ኩባንያዎችና የአስተዳደር በደል ነው” ብለዋል።
ምንጭ፦ VOA አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከሁለት ዓመታት በፊት በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ #ተጥለው የተገኙት ሁለት ኢትዮጵያውያን ህጻናት #በስደተኞች መጠለያ ቆይተው አሳዳጊ በማግኘታቸው ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ ገቡ። ህጻናቱ በቤት ሰራተኝነት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተወለዱ መሆናቸው ታውቋል።
Via ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን እና ሶማሌ ክልል ዳዋ ዞን መካከል ነገ #በሞያሌ ከተማ ለሚካሄደው የሠላም ኮንፈረንስ ዝግጅቱ መጠናቀቁ ተነግሯል፡፡ በኮንፈረንሱ ላይ ለመሳፍ የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልል የፀጥታ እንዲሁም የዞን እና የወረዳ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ ኡጋዞች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ወጣቶችና ሴቶች ሞያሌ ከተማ እየገቡ ይገኛሉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለዘመናት አብረዉ የኖሩትን የአማራና የትግራይ ወንድማማች ህዝቦች ወደ #ጦርነት ለመዉሰድ የሚደረገዉ ፀብ አጫሪነት በምንም መልኩ ተቀባይነት የለዉም ሲል የአማራ ክልል ምክር ቤት ገለጸ።
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/የአማራ-ክልል-ምክር-ቤት-12ኛ-መደበኛ-ጉባኤ-03-07
ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/የአማራ-ክልል-ምክር-ቤት-12ኛ-መደበኛ-ጉባኤ-03-07
Telegraph
የአማራ ክልል ምክር ቤት 12ኛ መደበኛ ጉባኤ፦
ትግራይንና የትግራይን ህዝብ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል የሚደረጉ የጥላቻ ንግግሮች ሊቆሙ እንደሚገባ የአማራ ክልል ምክር ቤት አስጠነቀቅ። በትግራይ ክልል አመራሮች በኩል እየተደረገ ያለው የጦርነት ቅስቀሳም መቆም እንዳለበት ምክር ቤቱ አሳስቧል፡፡ በባሕር ዳር እየተካሄደ ያለው የአማራ ክልል 12ኛ መደበኛ ጉባኤ ትናንት በአማራ ክልል የፀጥታና የሰላም ጉዳይ ዙሪያ በዝግ ሲወያይ ውሏል፡፡ የተለያዩ ውሳኔዎችንም…
ሀረሪ❓
በሐረሪ ክልላዊ መስተዳድር ስር በሚገኘው #ጅኔላ_ወረዳ በአካባቢው የሚኖሩ ከስልሳ በላይ ቤቶች ከሌላ አካባቢ መጡ በተባሉ አካላት ጥቃት ተፈፀመባቸው።
የተወሰኑ ነዋሪዎች በሁኔታው በመስጋት ቤታቸውን ጥለው ስለመውጣታቸው ጀርመን ራድዮ ደረሰኝ ባለው መረጃ ጠቁሟል።
ጥቃት ፈጻሚዎቹ ወደ ነዋሪዎቹ መኖሪያ ቤት በመዝለቅ የተለያዩ ንብረቶች ሰባብረዋል ተብሏል። በስፍራው የተገኘው የDW ዘጋቢ የአንዳንድ መኖርያ ቤት አጥሮች ፈርሰው፣ አንዳንዶችም በስለት (ባንጋ) መቆራረጣቸውን ታዝቧል። የውሀ መስመር እና የመብራት ቆጣሪ የተሰባበረበት መኖርያ ቤትንም ተመልክቷል።
ጥቃቱ የተፈጸመው “የአካባቢው መሬት የእኛ በመሆኑ ልቀቁ በሚሉ አካላት” መሆኑን የሚናገሩት ተጎጂ ነዋሪዎች በድርጊቱ ማዘናቸውን ለጀርመን ራድዮ ገልጸዋል። “አሁንም ችግራችንን #አውጥተን ለሚዲያ #ለመናገር እንሰጋለን፤ ህይወታችንም ያሳስበናል፤ ምን ዋስትና አለን” ሲሉ ስማቸውን ለመግለፅ የፈሩ ነዋሪ ተናግረዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ ኃላፊ “ግጭቱ መኖርያ ቤቶቹ ከተገነቡበት ቦታ የይገባኛል ጥያቄ ጋር በተያያዘ የተፈጠረ” መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በግጭቱ የሰው ህይወት ላይ የደረሰ ነገር ባይኖርም በጥይት የተመታ አንድ ሰው ግለሰብን ጨምሮ አራት ሰዎች ተጎድተዋል። በጥይት ተመቷል የተባለው ግለሰብም በሆስፒታል ህክምና እየተከታተለ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በግጭቱ በስልሳ አንድ መኖርያ ቤቶች ላይ ጥቃት ሲደርስ ዝርፊያና ንብረት ማውደም ተፈፅሟልም ብለዋል።
ህብረተሰቡን የማወያየት ስራ እየተሰራ መሆኑ እና የተፈጠረው ሁኔታም #ተረጋግቷል ቢባልም ችግሩ መሰረታዊ መፍትሄ ያላገኘ በመሆኑ በነዋሪዎች አንድ አሁንም ስጋቶች እንዳሉ ናቸው።
#የመከላከያ_ሰራዊት አባላት ግጭቱን ለማረጋጋት በአካባቢው ሲዘዋወሩ የጀርመን ራድዮ ዘጋቢ የተመለከተ ሲሆን ነዋሪዎች ዱላ፣ ስለታም ነገሮች (መቁረጫ ባንጋ) ይዘው አካባቢያቸውን ሲጠብቁ አስተውሏል። ሐኪም ጋራ እየተባለ በሚጠራው በዚህ አካባቢ የተፈጠረው ሁኔታ ባለመረጋጋቱ ከ150 በላይ ነዋሪዎች በየዕለቱ የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅ ተሰባስበው በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸው ታውቋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ (አማርኛው አግልግሎት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሐረሪ ክልላዊ መስተዳድር ስር በሚገኘው #ጅኔላ_ወረዳ በአካባቢው የሚኖሩ ከስልሳ በላይ ቤቶች ከሌላ አካባቢ መጡ በተባሉ አካላት ጥቃት ተፈፀመባቸው።
የተወሰኑ ነዋሪዎች በሁኔታው በመስጋት ቤታቸውን ጥለው ስለመውጣታቸው ጀርመን ራድዮ ደረሰኝ ባለው መረጃ ጠቁሟል።
ጥቃት ፈጻሚዎቹ ወደ ነዋሪዎቹ መኖሪያ ቤት በመዝለቅ የተለያዩ ንብረቶች ሰባብረዋል ተብሏል። በስፍራው የተገኘው የDW ዘጋቢ የአንዳንድ መኖርያ ቤት አጥሮች ፈርሰው፣ አንዳንዶችም በስለት (ባንጋ) መቆራረጣቸውን ታዝቧል። የውሀ መስመር እና የመብራት ቆጣሪ የተሰባበረበት መኖርያ ቤትንም ተመልክቷል።
ጥቃቱ የተፈጸመው “የአካባቢው መሬት የእኛ በመሆኑ ልቀቁ በሚሉ አካላት” መሆኑን የሚናገሩት ተጎጂ ነዋሪዎች በድርጊቱ ማዘናቸውን ለጀርመን ራድዮ ገልጸዋል። “አሁንም ችግራችንን #አውጥተን ለሚዲያ #ለመናገር እንሰጋለን፤ ህይወታችንም ያሳስበናል፤ ምን ዋስትና አለን” ሲሉ ስማቸውን ለመግለፅ የፈሩ ነዋሪ ተናግረዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ ኃላፊ “ግጭቱ መኖርያ ቤቶቹ ከተገነቡበት ቦታ የይገባኛል ጥያቄ ጋር በተያያዘ የተፈጠረ” መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በግጭቱ የሰው ህይወት ላይ የደረሰ ነገር ባይኖርም በጥይት የተመታ አንድ ሰው ግለሰብን ጨምሮ አራት ሰዎች ተጎድተዋል። በጥይት ተመቷል የተባለው ግለሰብም በሆስፒታል ህክምና እየተከታተለ እንደሚገኝም አስረድተዋል። በግጭቱ በስልሳ አንድ መኖርያ ቤቶች ላይ ጥቃት ሲደርስ ዝርፊያና ንብረት ማውደም ተፈፅሟልም ብለዋል።
ህብረተሰቡን የማወያየት ስራ እየተሰራ መሆኑ እና የተፈጠረው ሁኔታም #ተረጋግቷል ቢባልም ችግሩ መሰረታዊ መፍትሄ ያላገኘ በመሆኑ በነዋሪዎች አንድ አሁንም ስጋቶች እንዳሉ ናቸው።
#የመከላከያ_ሰራዊት አባላት ግጭቱን ለማረጋጋት በአካባቢው ሲዘዋወሩ የጀርመን ራድዮ ዘጋቢ የተመለከተ ሲሆን ነዋሪዎች ዱላ፣ ስለታም ነገሮች (መቁረጫ ባንጋ) ይዘው አካባቢያቸውን ሲጠብቁ አስተውሏል። ሐኪም ጋራ እየተባለ በሚጠራው በዚህ አካባቢ የተፈጠረው ሁኔታ ባለመረጋጋቱ ከ150 በላይ ነዋሪዎች በየዕለቱ የአካባቢውን ሰላም ለመጠበቅ ተሰባስበው በመንቀሳቀስ ላይ መሆናቸው ታውቋል።
ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ (አማርኛው አግልግሎት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በምዕራብ ኢትዮጵያ #የጥፋት ኃይሎች በስፋት ሲንቀሳቀሱበት የነበረውን የምዕራብ ኦሮሚያና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የምዕራብ ኢትዮጵያ ኮማንድ ፖስት በወሰደው #እርምጃ ማረጋጋት እንደተቻለ የኢፌዴሪ መከላከያ ምክትል ኢታማጆር ሹም ጀኔራል #ብርሃኑ_ጁላ ተናገሩ ። ዛሬ የምዕራብ ኢትዮጵያ ኮማንድ ፖስት በአሶሳ ከተማ ገምገማ አካሂዷል። በግምገማው ወቅት ህብረተሰቡ ከነበረበት የሥጋት ስሜት ወጥቶ በአካባቢው #ሠላማዊ በሆነ መንገድ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ተገልጿል፤ ቀጣይነቱን ለማረጋገጥ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን ማጠናከር ይገባል ተብሏል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከትግራይ የህዝብ ግንኙነትና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተሰጠ መግለጫ፦
ትላንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ ዋነኛ አጀንዳችን ሰላም፣ ዲሞክራሲና ልማት ነው!!
የአማራ ክልል ምክር ቤት፣ ከየካቲት 26-29/2011ዓ/ም እያካሄደው ባለው 5ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 12ኛ መደበኛ ጉባኤው የተለያዩ ውሳኔዎች ማስተላለፉን አስመልክቶ፣ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ዳይሬክተር፣ የካቲት 27/2011 ዓ/ም ለአማራ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
በዚህ መግለጫ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አስተላለፉዋቸው ከተባሉት ጉዳዮች መካከል የትግራይ ህዝብና መንግስት ጦርነት ለማካሄድ እያደረጉት ካለው ቅስቀሳና ዝግጅት እንዲቆጠቡ የሚል ማስጠንቀቅያ አዘል መልእክት ተሰራጭቷል፡፡
ነገር ግን የትግራይ ህዝብና መንግስት የጦርነት አስከፊነት ስለሚረዱ፣ ዋነኛ አጀንዳቸው የሆነው ሰላም ማስፈን፣ ዲሞክራሲ ማስፋትና መልካም አስተዳደር ማንገስ እንዲሁም ፈጣንና ሁሉም በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት ልማት ለማረጋገጥ በመታተር ላይ ናቸው፡፡ የትግራይ ህዝብና መንግስት በ17 ዓመታት የትጥቅ ትግል ወቅት፣ ወታደራዊ ፋሽሽት ደርግ ለመደምሰስ በተደረገው መራራ ትግል፣ የአማራ ህዝብ፣ ከወንድሙ የትግራይ ህዝብ ጎን ተሰልፎ ተገቢው መስዋእትነት ከፍሏል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ህዝብና መንግስት የታገሉለትን ህዝባዊ መሰመር አንግበዉ ወደፊት ከመገስገስ ዉጭ በወንድም የአማራ ህዝብ ላይ አፈሙዝ የሚያዞርበት አንዳች ምክንያት የላቸዉም፡፡
በመሆኑም የትግራይ ህዝብና መንግስት ባለፉት ዓመታት፣ በተለያዩ ችግሮች የባከኑባቸውን ጊዚያት ለማካካስ፣ ሁለመናቸው ያቀዱት የዲሞክራሲና የትራንስፎርመሽን ዕቅድ ለማሳካት በመሯሯጥ ላይ ናቸው፡፡ በተያያዝነው የበጋ ወቅትም ቢሆን አፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባራት በማሳለጥ ለ2011/2012 የክረምት ስራ ቅድመ ዝግጅት ላይ ናቸው፡፡
ይልቅኑም ማነው በግላጭ ትንኮሳና የጦርነት አታሞ ሲጎስም የከረመው የሚል ጥያቄ ቢነሳ፣ ምላሹ ሰላም ወዳድ ዜጋ ምስክርነት ሊሰጥ ይችላል፡፡ ሽፍቶች ጨምሮ የተለያዩ ፀረ-ሰላምና ፀረ-ልማት ሃይሎች የተለያዩ የሚድያ አማራጮችን ተጠቅመው፣ ላለፉት ሶስት ዓመታት፣ ያለእረፍት ቀንና ለሊት የጦርነት ቅስቀሳና ቱንኮሳ ከማካሄድ አልፎው፣ በትግራይ ወሰኖች ሄድ መለስ ሲሉ ቆይተዋል፡፡
ትላንት የትግራይ ክልል ብሄር ተወላጆች ብቻ በመሆናቸው በአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በድንጋይ ተቀጥቅጦው ሲገደሉ፣ ከ50 ሺ በላይ ዜጎች ጥረው ግረው ያፈሩት ሃብትና ንብረታቸዉ ተዘርፈው፣ እትብታቸው ከተቀበረበት ቀዮ ሲፈናቀሉ፣ እንዲሁም የአማራና የትግራይ ህዝብ እንዳይገናኙ አውራ መንገዶችን ዘግቶ ባይሳከለትም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲሻክር የተፍጨረጨረዉ ፀረ-ሰላምና ፀረ-ልማት ሃይሉ ታሪክ ይቅር የማይለው በደልና ክህደት ፈፅሟል፡፡
በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብና መንግስት ነጋ ጠባ ከፅንፈኛ ሃይሎች የሚወረወርባቸዉ የቃላት ጦርነትና ትንኮሳ ከልክ በላይ ያለፈ ቢሆንም፣ ጦርነት ለየትኛውም ወገን እንደማይጠቅም አሳምረዉ ስለምያዉቁ፣ እስከ አሁን ድረስ ትዕግስትን መርጧል። ይህንን እውነታ ንፁህ ህሊና ያለው ፍጡር የሚያውቀው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ይህ ያደረጉበት ምክንያት ከዋነኛ የሰላምና የልማት አጀንዳቸው ላለመራቅ ነው፡፡ ስለሆነም ትላንትም ሆነ ዛሬ የትግራይ ህዝብና መንግስት ዋነኛ ጠላት ድህነት ነው፡፡ አሁንም ቢሆን ጦርነታቸዉ ከድህነት ጋር በመሆኑ ማንኛውም ሰላም ወዳድ ዜጋ ስጋት ሊገባዉ አይገባም፡፡
በአጭሩ የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዋነኝነት የአማራና የትግራይ ህዝቦች ሰላም ተረጋግጦ የልማት ተቋዳሽ የሚሆኑት፣ በሃገራችን ሕገ-መንግስት ተከብሮ፣ የሕግ የበላይነት ተረጋግጦ፣ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ስርዓቱ ተጠናክሮ ሲቀጥል መሆኑ የማይታበል ሓቅ ነው፡፡
ሰለሆነም የአማራ ክልል ም/ቤት 5ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በፀጥታ ጉዳዮች አስመልክቶ በትግራይ ክልል መንግስትና ህዝብ አስተላልፎታል የተባለው ዉሳኔ ለአማራም ሆነ ለትግራይ ህዝብ ሰለማይበጅ ጉዳይን ዳግም እንዲያጤነዉ የትግራይ ህዝብና መንግስት ጥሪአቸውን ያቀርባሉ፡፡
ዘልአለማዊ ክብር እንከን ለማይነካቸው የትግሉ ሰማእታት!!
የትግራይ የህዝብ ግንኙነትና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
መቐለ-ትግራይ
የካቲት 28/06/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትላንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ ዋነኛ አጀንዳችን ሰላም፣ ዲሞክራሲና ልማት ነው!!
የአማራ ክልል ምክር ቤት፣ ከየካቲት 26-29/2011ዓ/ም እያካሄደው ባለው 5ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 12ኛ መደበኛ ጉባኤው የተለያዩ ውሳኔዎች ማስተላለፉን አስመልክቶ፣ የክልሉ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ዳይሬክተር፣ የካቲት 27/2011 ዓ/ም ለአማራ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
በዚህ መግለጫ፣ የአማራ ክልል ምክር ቤት አስተላለፉዋቸው ከተባሉት ጉዳዮች መካከል የትግራይ ህዝብና መንግስት ጦርነት ለማካሄድ እያደረጉት ካለው ቅስቀሳና ዝግጅት እንዲቆጠቡ የሚል ማስጠንቀቅያ አዘል መልእክት ተሰራጭቷል፡፡
ነገር ግን የትግራይ ህዝብና መንግስት የጦርነት አስከፊነት ስለሚረዱ፣ ዋነኛ አጀንዳቸው የሆነው ሰላም ማስፈን፣ ዲሞክራሲ ማስፋትና መልካም አስተዳደር ማንገስ እንዲሁም ፈጣንና ሁሉም በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበት ልማት ለማረጋገጥ በመታተር ላይ ናቸው፡፡ የትግራይ ህዝብና መንግስት በ17 ዓመታት የትጥቅ ትግል ወቅት፣ ወታደራዊ ፋሽሽት ደርግ ለመደምሰስ በተደረገው መራራ ትግል፣ የአማራ ህዝብ፣ ከወንድሙ የትግራይ ህዝብ ጎን ተሰልፎ ተገቢው መስዋእትነት ከፍሏል፡፡ በመሆኑም የትግራይ ህዝብና መንግስት የታገሉለትን ህዝባዊ መሰመር አንግበዉ ወደፊት ከመገስገስ ዉጭ በወንድም የአማራ ህዝብ ላይ አፈሙዝ የሚያዞርበት አንዳች ምክንያት የላቸዉም፡፡
በመሆኑም የትግራይ ህዝብና መንግስት ባለፉት ዓመታት፣ በተለያዩ ችግሮች የባከኑባቸውን ጊዚያት ለማካካስ፣ ሁለመናቸው ያቀዱት የዲሞክራሲና የትራንስፎርመሽን ዕቅድ ለማሳካት በመሯሯጥ ላይ ናቸው፡፡ በተያያዝነው የበጋ ወቅትም ቢሆን አፈርና ውሃ ጥበቃ ተግባራት በማሳለጥ ለ2011/2012 የክረምት ስራ ቅድመ ዝግጅት ላይ ናቸው፡፡
ይልቅኑም ማነው በግላጭ ትንኮሳና የጦርነት አታሞ ሲጎስም የከረመው የሚል ጥያቄ ቢነሳ፣ ምላሹ ሰላም ወዳድ ዜጋ ምስክርነት ሊሰጥ ይችላል፡፡ ሽፍቶች ጨምሮ የተለያዩ ፀረ-ሰላምና ፀረ-ልማት ሃይሎች የተለያዩ የሚድያ አማራጮችን ተጠቅመው፣ ላለፉት ሶስት ዓመታት፣ ያለእረፍት ቀንና ለሊት የጦርነት ቅስቀሳና ቱንኮሳ ከማካሄድ አልፎው፣ በትግራይ ወሰኖች ሄድ መለስ ሲሉ ቆይተዋል፡፡
ትላንት የትግራይ ክልል ብሄር ተወላጆች ብቻ በመሆናቸው በአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎች በድንጋይ ተቀጥቅጦው ሲገደሉ፣ ከ50 ሺ በላይ ዜጎች ጥረው ግረው ያፈሩት ሃብትና ንብረታቸዉ ተዘርፈው፣ እትብታቸው ከተቀበረበት ቀዮ ሲፈናቀሉ፣ እንዲሁም የአማራና የትግራይ ህዝብ እንዳይገናኙ አውራ መንገዶችን ዘግቶ ባይሳከለትም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲሻክር የተፍጨረጨረዉ ፀረ-ሰላምና ፀረ-ልማት ሃይሉ ታሪክ ይቅር የማይለው በደልና ክህደት ፈፅሟል፡፡
በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብና መንግስት ነጋ ጠባ ከፅንፈኛ ሃይሎች የሚወረወርባቸዉ የቃላት ጦርነትና ትንኮሳ ከልክ በላይ ያለፈ ቢሆንም፣ ጦርነት ለየትኛውም ወገን እንደማይጠቅም አሳምረዉ ስለምያዉቁ፣ እስከ አሁን ድረስ ትዕግስትን መርጧል። ይህንን እውነታ ንፁህ ህሊና ያለው ፍጡር የሚያውቀው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ይህ ያደረጉበት ምክንያት ከዋነኛ የሰላምና የልማት አጀንዳቸው ላለመራቅ ነው፡፡ ስለሆነም ትላንትም ሆነ ዛሬ የትግራይ ህዝብና መንግስት ዋነኛ ጠላት ድህነት ነው፡፡ አሁንም ቢሆን ጦርነታቸዉ ከድህነት ጋር በመሆኑ ማንኛውም ሰላም ወዳድ ዜጋ ስጋት ሊገባዉ አይገባም፡፡
በአጭሩ የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች በዋነኝነት የአማራና የትግራይ ህዝቦች ሰላም ተረጋግጦ የልማት ተቋዳሽ የሚሆኑት፣ በሃገራችን ሕገ-መንግስት ተከብሮ፣ የሕግ የበላይነት ተረጋግጦ፣ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ስርዓቱ ተጠናክሮ ሲቀጥል መሆኑ የማይታበል ሓቅ ነው፡፡
ሰለሆነም የአማራ ክልል ም/ቤት 5ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን፣ 12ኛ መደበኛ ጉባኤ በፀጥታ ጉዳዮች አስመልክቶ በትግራይ ክልል መንግስትና ህዝብ አስተላልፎታል የተባለው ዉሳኔ ለአማራም ሆነ ለትግራይ ህዝብ ሰለማይበጅ ጉዳይን ዳግም እንዲያጤነዉ የትግራይ ህዝብና መንግስት ጥሪአቸውን ያቀርባሉ፡፡
ዘልአለማዊ ክብር እንከን ለማይነካቸው የትግሉ ሰማእታት!!
የትግራይ የህዝብ ግንኙነትና የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
መቐለ-ትግራይ
የካቲት 28/06/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia