TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢትዮጵያ ልጇን አጣች‼️

ትላንት ምሽት አዲስ አበባ ደንበል አካባቢ በደረሰው #የመኪና_አደጋ የAAiT መምህር የሆኑት አቶ #ሳምሶን_ዋለልኝ ህይወታቸው አልፏል።

እንደወጣን እየቀረን ነው...

•TIKVAH-ETHIOPIA ለወዳጅ፤ ዘመዶች እንዲሁም ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ በሙሉ #መፅናናትን ይመኛል!

#ነብስ_ይማር!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሌላ አሳዛኝ መርዶ...

"ፀግሽ ትላንት ለሊት የኩሪፍቱ አዳማ #ማኔጀር የነበረው #መለሰ_ደጀኔን በመኪና አደጋ ከጎናችን አተነዋል! ቀን ሰርግ ውሎ ማታ ወደ አዳማ እየሄደ ከሲኖትራክ ጋር #ተጋጭቶ በደረሰ አደጋ በመሞት አተነዋል። መለሰ ማለት በጣም መልካም ሰው ነበር፣ ይህ የመኪና አደጋ በዚህ ሳምንት 2ተኛዬ ነው እንጠንቀቅ!"

Via Dagi
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በጎንደር ከተማ በ100 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ዘመናዊ የምግብ ዘይት ፋብሪካ ተመረቀ። ፀሐይ ሁለገብ የገበሬዎች ሕብረት ሥራ ዩኒየን በጎንደር ከተማ በ100 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባውን ዘመናዊ የምግብ ዘይት ማምረቻ ፋብሪካ አስመርቋል። ፋብሪካውን ዛሬ #መርቀው የከፈቱት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የአማራ ክልል ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ መላኩ አለበልና የፌደራል ሕብረት ሥራ ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር አቶ #ኡስማን_ሱሩር ናቸው፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
እባካችሁ ጥንቃቄ አይለየን...‼️

ይህ በፎቶው የምትመለከቱት የመኪና አደጋ የደረሰው ከደቂቃዎች በፊት አዲስ አበባ ጉርድ ሾላ አካባቢ ነው። በቦታው የነበሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት እንደነገሩኝ በአደጋው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"እኔ በእውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ #ዐይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት ግን የሰው #አስተሳሰብ ነው። #የሰው አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ #ይፈርሳል። ጃፓን እና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን #አልምተው ነው"-- መጋቤ ሀዲስ አሸቱ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን #ጅማ_አባ_ጅፋር የእግር ኳስ ክለብን ከማንኛውም ፌዴሬሽኑ ከሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ማገዱን አስታወቀ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለfbc እንዳስታወቀው፥ ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብ ከየካቲት 29 2011 ጀምሮ ፌዴሬሽኑ ከሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ላይ ታግዷል። እንደ ፌዴሬሽኑ ገለጻ፥ ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብ የታገደው አብዱልፈታህ ከማል ለተባለው ተጫዋቹ ተገቢውን ክፍያ ባለመፈፀሙ ነው። አብዱልፈታህ ከማል የተባለው የእግር ኳስ ተጫዋች ከክለቡ ጋር ውል እያለው ከመስከረም ወር 2010 ዓ.ም ጀምሮ ወሉ በክለቡ በመቋረጡ ለፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን ኮሚቴ አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን፥ ኮሚቴውም የተጫዋቹን አቤቱታ በመመልከት ለአመልካች ያልተከፈለው ደመወዝ ታስቦ በአምስት ቀናት ውስጥ እንዲከፈለው የካቲት 12 2010 ዓ.ም ለክለቡ በተፃፈ ደብዳቤ ማሳወቁን ገልጿል። ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብም ይህንን ተግባራዊ ሳያደርግ በመቆየቱ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ሚያዝያ 12 2010 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ በክለቡ ላይ ቀጣይ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀ ቢሆንም ክለቡ ግን ለተጫዋቹ ክፍያውን ሳይከፍል ቆይቷል ብሏል። በመሆኑም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት ጅማ አባ ጅፋር የእግር ኳስ ክለብ ከየካቲት 29 2011 ዓ.ም ጀምሮ ፌዴሬሽኑ ከሚያዘጋጃቸው የእግር ኳስ ውድድሮች የታገደ መሆኑን አስታውቋል።

Via fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጨፌ ኦሮሚያ 9ኛ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው እለት ማካሄድ #ጀምሯል። ጨፌው ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባው የክልሉን መንግስት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም እንደሚገመግም ይጠበቃል። እንዲሁም በክልሉ ያለው #ሰላም#መረጋጋት እና የህግ የበላይነትን ማስከበር ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚመክርም ተገልጿል።

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ወለጋ ዞን በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተገለፀ።

የትራፊክ አደጋው በትናንትናው እለት የደረሰ መሆኑን ከምስራቅ ወለጋ ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

#ከነቀምቴ ከተማ ወደ #ሲቡ_ስሬ ወረዳ 22 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ጪንጊ በተባለች ከተማ አቅራቢያ በመገልበጡ ነው አደጋው የደረሰው።

በትራፊክ አደጋውም በሚኒባስ ተሽከርካሪው ተሳፍረው ሲጓዙ ከነበሩ 22 ሰዎች ውስጥ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉ ነው የተገለፀው።

ምንጭ፦ Fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትላንት ምሽት 5:15 የተላከ...
(እንደወጣን እየቀረን ነው)

"ሀይ ፀጊሽ ዛሬ #ከነቀምት ወደ ሲቡ ሲሬ ሲጓዝ የነበረ #ሀይሩፍ_ተገልብጦ ከ10 ሰው በላይ ሞቷል። በወቅቱ ከባኮ ወደ ነቀምት ስንጓዝ ነበር። በጣም ያሳዝናል ከቀኑ 11:30 ገደማ ነበር አደጋው የተከሰተው።"

Via Yididiya Silshi(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በጎንደር ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ባለው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ-ግብር እስከ 10 ሚሊዮን ብር ቃል እንደተገባ ማረጋገጡን የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴው እንዳሳወቀው ከሁለቱ ዞኖች ለተፈናቀሉ ዜጎች ማቋቋሚያ እስከ 80 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዷል፡፡ የተፈናቃዮቹ ጉዳይ የአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ መሆኑን የገለጸው ኮሚቴው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አስተላልፏል።

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ንግድን የማሳለጥ (Doing Business) መርሐ ግብር የአንድ ወር አፈጻጸም ግምገማ በጠ/ሚር ጽ/ቤት እየተካሄደ ይገኛል። ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ መዋቅራዊ የሥራ አጥነት ችግርን ለመቅረፍ የግል ዘርፉ ንግድን ለመጀመርና ፋይናንስን በቀላሉ ለማግኘት እንዲችል ምቹ ሁኔታ የመፍጠርን አስፈላጊነት አሥምረውበታል። በተለይም ጀማሪ ንግዶች ፋይናንስን በቀላሉ ለማግኘት ያሉባቸውን ማነቆዎች ከመፍታት አኳያ የብድር ሥርዓቱን በመከለስ ተንቀሳቃሽ ንብረትን በመያዣነት ለመበደር የሚያስችል አሠራር በሂደት ላይ መሆኑን ጠ/ሚሩ አስታውቀዋል።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዛሬ በቀን 19/06/2011 ዓ.ም በአብስላ ዋርዳ ቀበሌ አንድ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ #ሞቶ ተገኝቷል። አስክሬኑም #በቲሊሊ ጤና ጣቢያ ምርመራ እየተደረገለት ነው።

Via ጓጉሳ ሽኩዳድ ኮሙኒኬሽን-ቲሊሊ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመሮ ምክትል የሰላም ጥሪውን ተቀበለ‼️

የ'ጓድ' መሮ ምክትል እና 'ዲነራስ' በሚለው የትግል ስም የሚታወቀው ሁንዴ ዴሬሳ ከቀናት በፊት የአባ ገዳዎችን ጥሪ ተከትለው የጦር አባላቱን ይዞ ወደ ተዘጋጀለት ስፍራ ገብቷል።

ሁንዴ ዴሬሳ የአባ ገዳዎችን የሰላም ጥሪ የተቀበለውና ወደ ተዘጋጀው ስፍራ የገባ የመጀመሪያው የኦነግ የጦር አዛዥ ነው ተብሏል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የምዕራብ ኦሮሚያ ዞን ምክትል ጦር አዛዥ የሆነው ሁንዴ ዴሬሳ ወደፊትም ቢሆን በኦሮሞ እና የኦሮሚያ መብትን ለማስከበር መታገላችንን እንቀጥላለን ሲል ለቢቢሲ ተናግሯል።

ቅዳሜ ዕለት በአባ ገዳዎች አቀባበል ተደርጎለት የነበረው የጦር አዛዡ ተከታዮቹ በአምቦ ሰንቀሌ የፖሊስ ማሰልጠኛ ቆይታ ካደረጉ በኋላ ዛሬ ወደ ጦላይ የወታደር ማሰልጠኛ ማዕከል መሄዳቸውን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

የምዕራብ ኦሮሚያ ዞን የጦር አዛዥ የሆነው መሮ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ላይ ''ወደፊት መራራ ትግል ማድረጋችንን እንቀጥላለን። ብቻዬን ብቀር እንኳ ትግል ማድረጌን እቀጥላለሁ እቅዴም ይሄው ነው" ሲል መናገሩ ይታወሳል።

ሁንዴ ዴሬሳ እንዴት የአባ ገዳዎችን ጥሪ ለመቀበል እንደቻለ ሲያብራራ ''ይህ የህዝብ ፍላጎት ነው። ህዝቡ የሚፈልገው ይህን ነው። 'በኦሮሞ ጉዳይ ላይ ኑ አብራን እንሥራ' ብለው ጥሪ ስላቀረቡልን ከሠራዊቱ ጋር ከተወያየን በኋላ ጥያቄያቸውን ተቀብለናል'' ብሏል።

''የኦነግ የምዕራብ ኦሮሚያ ዞን በሁለት ተከፍሎ ነው የሚተዳደረው። ከጊምቢ በታች መሮ ነው ትዕዛዝ የሚሰጠው። ከጊምቢ በላይ እንደ ነቀምቴ፣ ሻምቡ እና ምዕራብ ሸዋ ደግሞ ትዕዛዝ የምሰጠው እኔ ነኝ'' የሚለው ሁንዴ የዕዝ ተዋረዱን ሲያስረዳ ''መሮ ከሊቀመንበሩ [#ዳውድ_ኢብሳ] ትዕዛዝ ይቀበልና ለእኛ ያስተላልፋል'' ብሏል።

የሁንዴ የትግል አጋር እና አዛዥ የሆነው ኩምሳ ዲሪባ ወይም መሮ "የእርቅ የተባለው ኮሚቴ እኔን በአካል አግኝተው ለማነጋገር ፍላጎት የላቸውም። ትኩረት ያደረጉት ጦሩን አንድ በአንድ እጁን እንዲሰጥ ማድረግ ላይ ነው" በሚል እና በሌሎች ምክያቶች ጥሪውን እንደማይቀበል አርብ ዕለት ለቢቢሲ ተናግሮ ነበር።

በዚህ ላይ ሁንዴ አስተያየቱን እንዲሰጥ ተጠይቆ ''ይህን ትግል ህዝቡ የሚፈልግ ከሆነ አንድ መቶ ዓመት እንኳ በትግል ላይ እንቆያለን። የምንታገለው ለህዝቡ እስከሆነ ድረስ ህዝቡ የምፈልገው ሰላማዊ ትግል ነው እስካለ ድረስ የህዝቡን ስሜት ማዳመጥ ይኖርብናል። እሱ [መሮ] የግል አቋሙ ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ ማዳመጥ ያለብን የግል ስሜታችንን ሳይሆን የህዝቡን ፍላጎት ነው'' በማለት ''የአባ ገዳዎችን ጥሪ ከሰማን በኋላ ከመሮ ጋር ተገናኝተን ተነጋግረን ነበር። የእርቅ ጥሪውን ከተቀበልን በኋላ ሃሳቡን ቀየረ'' ሲል የነበረውን ሁኔታ ገልጿል።

የመሮን ውሳኔ በተመለከተም ''ሽንፈት መሰለው፤ ሰው የሚለውን መቀበል ላይ ትንሽ #ድክመት አለበት። #ብቸኝነትም ያጠቃዋል፤ ከዚህ ውጪስ ሌላ ችግር የለበትም" ብሏል።

መሮ ከቀናት በፊት ለቢቢሲ እንደተናገረው ''ከዚህ የተለየን ጦር 5 በመቶ እንኳ አይሆንም። 95 በመቶ አሁንም እንደታጠቀ ነው የሚገኘው" ብሎ ነበር። የመሮ ምክትል የሆነው ሁንዴ እንደሚለው ከሆነ ግን የእርቅ ጥሪውን ተቀብለው የወጡ የኦነግ ወታደሮች በጫካ ከሚገኙት ይበልጣሉ።

''በእኔ ስር የነበሩ የሠራዊት አባላት በሙሉ የእርቅ ጥሪውን በደስታ ተቀብለውታል፤ በጫካ የቀሩት አባላት 'የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ እስኪመለስ እንታገላለን የሚሉት ናቸው'' በማለት ተናግሯል።

በኦነግ ጦር አባላት መካከል የእርቅ ጥሪውን እንቀበል፤ አንቀበል በሚል የሃሳብ ልዩነት ተፈጥሯል ወይ ብለን ለጠየቅነው ጥያቄ፤ ሁንዴ ሲመልስ ''ይህ በደንብ ያለ ነው። እኔ እንደማውቀው እንኳ ሦስት ቦታ ተከስቷል'' ብሏል።

ምንጭ፦ BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia