TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"ብቻዬን ብቀር እንኳ #ትግሌን እቀጥላለሁ" ጃል መሮ የኦነግ ጦር አዛዥ
.
.
በመንግሥትና በኦነግ መካከል በሽማግሌዎች አማካይነት የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ በርካታ የግንባሩ አባላት ተሰማርተው ከነበሩባቸው ቦታዎች #በሰላም እየተመለሱ ቢሆንም በምዕራብ ኦሮሚያ የሚንቀሳቀሰው የኦነግ ኃይል አዛዥ ግን ይህንን ለመፈፀም ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።

በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች ተሰማርተው የሚገኙ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ጦር አባላት የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትለው #ትጥቅ_ፈትተው ወደ ጦር ካምፖች ከመግባታቸው በፊት ወደተዘጋጁላቸው ጊዜያዊ ማቆያ ስፍራዎች በዚህ ሳምንት እየገቡ እንደሆነ እየተዘገበ ነው።

ሽምግልናውን የመሩትና ስምምነቱ ከፍጻሜ እንዲደርስ ጥረት እያደረጉ ያሉት አባገዳዎች እና የየአካባቢዎቹ ባለስልጣናት ለውሳኔው ተገዢ በመሆን ወደተዘጋጁላቸው ስፍራዎች ከነትጥቃቸው ሲመጡ አቀባበል እያደረጉላቸው ይገኛል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የአባገዳዎችን ጥሪ ተከትሎ ሁሉም የኦነግ ጦር አባላት እየተመለሱ እንዳልሆነ ከተመለሱት የኦነግ ጦር አባላት ተሰምቷል።

ለዚህም እንደምክንያት የሚጠቀሰው የምዕራብ ኦሮሚያ የኦነግ ጦር አዛዥ የሆነው ኩምሳ ድሪባ ወይም በትግል ስሙ በስፋት የሚታወቀው ጓድ መሮ የአባገዳዎችን ጥሪ አለመቀበሉ ነው።

በምዕራብ ኦሮሚያ የሚገኘው የኦነግ ጦር አዛዥ እንደሆነ በስፋት የሚነገርለት ኩምሳ ድሪባ (መሮ) ወይም መሮን ቢቢሲ ስለዚሁ ጉዳይ በስልክ አነጋግሮታል። እንደተባለውም መሮ ባለው ሁኔታ ስምምነቱን ተቀብሎ ለመግባት ዝግጁ እንዳልሆነ ገልጿል።

የአባገዳዎችን ጥሪ ለመቀበል እና እርቅ ለማውረድ ዝግጁ ስለመሆኑ ሲጠየቅም "የእርቅ የተባለው ኮሚቴ እኔን በአካል አግኝተው ለማነጋገር ፍላጎት የላቸውም። ትኩረት ያደረጉት ጦሩን አንድ በአንድ እጁን እንዲሰጥ ማድረግ ላይ ነው" በማለት እሱም እነሱን ለማግኘት ያደረገው ጥረት አለመሳካቱን ይናገራል።

እንዲያውም "ጦሩን የመበታተን ዓላማ ይዘው ነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት" ሲል ይከሳል።

የኦነግ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ዳውድ ኢብሳ የእርቅ ኮሚቴውን በመደገፍ የኦነግ ጦር ጥሪውን ተቀብሎ ወደተዘጋጀለት ስፍራ እንዲሄድ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል። የጦሩ መሪ መሮ የግንባሩ ሊቀመንበር ተገዢ መሆን አለመሆኑን ተጠይቆ ሲመልስ "ሊቀመንበሩ የእርቅ ኮሚቴውን ያሉት፤ 'የኦነግ ጦር የእናንተው ነው። ሂዱና አወያይታችሁ የሚሉትን ስሟቸው' ነው ያሉት" ብሏል።

ጨምሮም እንደተናገረው "እኔ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እንወያይ ነው ያልኩት እንጂ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ ጥቅም የለውም፤ የኦሮሞ ህዝብ መሰቃየት የለበትም ነው የምለው። እነሱ ግን የጦሩ አባላት የእጅ ስልክ ላይ እየደወሉ አንድ በአንድ ጦሩን የማፍረስ ሥራ ነው እየሰሩ የሚገኙት" ሲል ገልጸወል።

ያለው ችግር ከስር መሰረቱ ምፍትሄ አላገኘም ብሎ የሚያምነው መሮ አሁን እየተደረገ ያለው "በተለያዩ ስፍራዎች የሚገኙ ሰዎችን አንድ በአንድ የማስኮብለል ሥራ ነው። ከዚህ የተለየን ጦር 5 በመቶ እንኳ አይሆንም። 95በመቶ አሁንም እንደታጠቀ ነው የሚገኘው" በማለት ተናግሯል።

"ወደፊት መራራ ትግል ማድረጋችንን እንቀጥላለን" ያለው መሮ "ብቻዬን ብቀር እንኳ #ትግል ማድረጌን እቀጥላለሁ እቅዴም ይሄው ነው" በማለት በትጥቅ ትግሉ እንደሚቀጥል ጠንከር በማለት ተናግሯል።

የቀረበውን የእርቅ ጥሪ ተቀብለው ከገቡት የኦነግ አባላት መካከል አንዱ የሆኑት የግንባሩ ጦር የሞራል እና ፖለቲካ መምህር የ57 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ አቶ #ታፈሰ_ኦላና በመሮ በኩል ያሉት ወታደሮች እየተመለሱ እንዳልሆነ አረጋግጠዋል።

ጨምረውም "መሮ መመለስ አይፈልግም፤ ስልክ እየደወለ #ጸያፍ_ቃል እየተናገረን ነው። 'እጃችሁን ለአባገዳዎች እየሰጣችሁ ሰዎች ከትግላችን ዓላማ ውጪ የሆነ ተግባር እየፈጸማችሁ ነው። ታሪክ ይፋረዳችኋል' እያለ ያስጠነቅቀናል።"

አቶ ታፈሰ እንደሚሉት አሁንም በምዕራብ ኦሮሚያ ትዕዛዝ የሚሰጠው መሮ መሆኑንና "የኦሮሞን ምድር የጦር አውድማ ማድረግ ነው የሚፈልገው። ህዝብ ሰላም እየፈለገ እሱ ግን አሁንም ደም ማፍሰስ የሚፈልግ ከሆነ ተሳስቷል" ብለዋል።

የኦነግ የምዕራብ ኦሮሚያ ጦር አዛዥ መሮ በአባ ገዳዎች የቀረበውን ጥሪ ተቀብለው ወደተዘጋጀላቸው ስፍራ የሄዱ የጦሩ አባላት ላይ ይሰነዝራል ስለተባለው ማስፈራሪያን በተመለከተ "የምን ማስፈራራት ነው። መሳሪያ ይዘን እያየናቸው እኮ ነው እየሄዱ ያሉት። ምርጫቸው ነው። ማንም ማንንም አላስፈራራም" ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

መሮ ችግሩን ለመፍታትም እንደቅድመ ሁኔታ የሚጠይቀው "በደቡብ ኢትዮጵያ እና በተለያዩ ዞኖች ከሚገኙ አባላቶቻችን ጋር በቅድመ ሁኔታዎች ላይ #ውይይት ማድረግ አለብን" በማለት የሽምግልና ኮሚቴውም እንዲያወያያቸውና "አንድ በአንድ የጦሩን አባላት ማስኮብለል" ያለውን ድርጊት ማስቆም እንዳለባቸው ተናግሯል።

የእርቅ ኮሚቴው ጸኃፊ የሆነውን #ጀዋር_መሐመድ በበኩሉ የኮሚቴው አባላት በተንቀሳቀሱባቸው ስፍራዎች ሁሉ የኦነግ የጦር አመራሮችን ለማግኘት ያደረጉት ጥረት የጦሩ አመራሮች ፍቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው ሳይሳካ እንደቀረ ይናገራል።

ጃዋር ''ወደ ምዕራብ ኦሮሚያ የተጓዙት አቶ በቀለ ገርባ እና አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ ያደረጉት ሙከራ #አልተሳካላቸውም። ወደ ደቡብ ኦሮሚያ የሄድኩት ደግሞ እኔ ነበርኩኝ። የኦነግ የምዕራብ ዞን የጦር ኃላፊ ሊያገኘን ፍቃደኛ #አልነበረም።'' ሲል ተናግሯል።

ምንጭ፦ BBC አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያን እንፈልጋታለን‼️

ምስኪኑ ዜጋ ሲፈናቀል፣ ሲሰቃይ፣ ሲቸገር፣ ተበደልኩ ሲል፣ ፍትህ ተነፍጊያለሁ ብሎ ሲጮህ፣ መንግስት በድሎኛል ብሎ ሮሮውን ሲያሰማ ለርካሽ #የፖለቲካ_ትርፍ እና #ሀገር_ለማትራመስ የምትሯሯጡ ጨካኝ አረመኔ ሰዎች ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ሰብስቡልን።

ሰዎች ሰውነታቸውን ክደው #ሀዘናቸውን እንኳን #ብሄር ለይተው እንዲገልፁ የምትገፋፉ ሰውነታችሁን የከዳችሁ ሁሉ #ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ከሀገራችን ላይ አንሱ።

በደንብ ስሙኝ...🔥

ህዝቡን በብሄር ከፋፍላችሁ #ወደጦርነት ለመክተት ፌስቡክ ላይ #ተዘፍዝፋችሁ የምትውሉ ሰዎች--የምትወዱትን ማጣት ስትጀምሩ፣ ምስኪን ህፃናት እንደቅጠል ሲረግፉ ማየት ስትጀምሩ፣ ሚሊዮኖች ሰላም ፍለጋ መሰደድ ሲጀምሩ ስታዩ ደም እምባ እያለቀሳችሁ እያንዳንዷን ፌስቡክ ላይ የዋላችሁበትን ቀን #ትረግሟታላችሁ
.
.
መንግስት በአስቸኳይ #ፍትህ እንፈልጋለን ብለው የሚጮሁ ዜጎች ካሉ ያዳምጥ፤ ምላሽ ይስጥ፤ በምስኪን ዜጎች ህይወት ላይ #ቁማር የሚጫወቱ የፖለቲካ ነጋዴዎችንም አደብ ያስገዛ!

#FACEBOOK ከብዶናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
etv Live! "ጉዞ ሉሲ ለሰላምና ለፍቅር" በአፋር ሰመራ የአቀበባል ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በኢትዮጵያ ለአራተኛ ጊዜ የሚካሄደው የህዝብና ቤት ቆጠራ መጋቢት 19 ቀን 2011 ዓ.ም #በመላው አገሪቷ ይጀመራል። በየአስር ዓመቱ ለሚካሄደው ለዚህ ስራ 152 ሺህ የቆጠራ ቦታዎች፣ 182 ሺህ ቆጣሪዎችና 38 ሺህ ተቆጣጣሪዎች እንደዚሁም ለቆጠራው የሚያመቹ የቆጠራ ቦታ ካርታዎች መዘገጀታቻዉን የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎች ዘግቧል፡፡ ህዝቡ ትክክለኛውን መረጃ በመስጠት ለስኬቱ የበኩሉን ሚና መጫወት እንዳለበት ነው በኤጀንሲው የኦሮሚያ የህዝብና ቤት ቆጠራ ኮሚሽን ፀሃፊ አቶ ሼኮ ጉሩ አሳስበዋል። የቆጠራው በትክክልና በጥራት መካሄድ የአገሪቱን ሁለንተናዊ ተጨባጭ ሁኔታ በማመላከት ከአገር ባሻገር ዓለም አቀፍ ፋይዳም ያለው በመሆኑ መረጃው በትክከል መሰብሰብ እንዳለበት ፀሃፊው ገልጸዋል። በጎዳና ላይ የሚኖሩና ተፈናቅለው ወደየቄያቸው ያልተመለሱ የህብረተሰብ ክፍሎችን በያሉበት #ለመቁጠር የሚያስችል የአሰራር ስርዓት መዘጋጀቱንም አስታውቀዋል። አራተኛው የህዝብና ቤት ቆጠራ የሚካሄደው #በዲጂታል_ሳተላይት ስርዓት በመታገዝ ነው ያሉት አቶ ሼኮ፤ የአፋር ስምጥ ሸለቆን ጨምሮ ለዲጂታል ስርዓቱ አመቺ ባልሆኑ አንዳንድ የአገሪቱ ክፍሎች ቆጠራው የሚካሄደው ከዚህ በፊት በነበረው አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።

ምንጭ፡- ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvaethethiopia
#update የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የሚፈፀሙ የጥላቻ ንግግሮችን #ለመቀነስ እርምጃዎችን እንደሚወስዱ አስታወቁ፡፡ አጥፊዎችን #ተጠያቂ የሚያደርጉ #የህግ ማዕቀፎች ተግባራዊ ይደረጋሉም ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አልጀዚራ
@tsegabwolde @tikvahethiopi
#update ፍርድ ቤቱ በአቶ #በረከት_ስምዖንና በአቶ #ታደሰ_ካሳ ተጨማሪ ቀጠሮ ላይ ለመወሰን ለሰኞ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በጥረት ኮርፖሬት የመሪነት ዘመናቸው በሀብት ብክነትና ምዝበራ የተጠረጠሩት አቶ በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ ዛሬ በቀጠሯቸው መሠረት በባሕር ዳርና አካባቢዋ ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡ ዐቃቤ ሕግ ምስክሮች ስላልመጡና መረጃዎች በበቂ #ስላልተጠናቀቁ ተጨማሪ የ14 ቀን ቀጠሮ ጠይቋል፡፡ በዚህ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለሰኞ የካቲት 18 ቀን 2011ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ በአሁኑ ሰዓት ከአፋር፣ ከሶማሌ፣ ከሐረሪ፣ ከቤንሻንጉል ጉምዝና ከጋምቤላ ክልል አጋር ፓርቲዎች የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ጋር #ውይይት እያካሄዱ ነው።

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዜግነትና የብሄር ፖለቲካ ተቃርኖ መዳረሻ...

በኢትዮጵያ ማንኛውም ዓይነት የፖለቲካ አቋምን ማራመድ መብት ቢሆንም፤ ልቀው የወጡት የዜግነትና የብሄር የፖለቲካ አስተሳሰቦች ግን በተቃርኖ የተሞሉ በመሆናቸው፤በተለይ ከዜግነት ይልቅ የብሄር ፖለቲካ የበላይነትን እያገኘ በመምጣቱ የተቃርኗቸው መዳረሻ አሳሳቢ ሆኗል። #በአርባ_ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምርት ቤት ኃላፊ አቶ ደርሶልኝ የኔአባት እንደሚሉት፤ የዜግነት ፖለቲካ በአብዛኛው በሰለጠኑት በምዕራባውያን አገራት የሚቀነቀን ሲሆን፤ በግለሰቦች ነጻነትና በዜጎች እኩልነት ላይ የተመሠረተ ነው። የሰለጠነ የፖለቲካ አስተሳሰብ ተደርጎም ይወሰዳል። ሰው #ሰው በመሆኑ ብቻ በየትኛውም የፖለቲካ ተሳትፎ ተጠቃሚ የሚሆንበት እንዲሁም ከየት መጣ፣ የትኛው ብሄር ነው የሚለውን ግንዛቤ ውስጥ የማያስገባ ነው።

ተጨማሪ ለማንበብ👇

https://telegra.ph/የዜግነትና-የብሄር-ፖለቲካ-ተቃርኖ-መዳረሻ-02-22-3
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ🔝

ከወርሃ ጥር ጀምሮ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርና አስተዳደደር ሃላፊዎች #ሹመትን አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ ተከትሎ የፕሬዝዳንት አፈላላጊ ኮሚቴ በመሰየም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የፕሬዝዳንት አፈላላጊ ኮሚቴም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርና አስተዳደደር ሃላፊዎችን ምርጫና ሹመት/ምደባ አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ ቁጥር 002/2011 ተግባራዊ በማደረግ ሃላፊነቱን በብቃት ሲወጣ ቆይቷል፡፡

በምልመላ እና መረጣ ሂደት ውስጥ በመስፈርትነት የተቀመጡ የትምህርት ዝግጅት፣ የአመራር ልምድ፣ በማስተማር እና በምርምር የተገኘ ልምድን መሰረት በማድረግ ከቀረቡ አሰር ዕጩዎች ተገቢውን መስፈርት የሚያሟሉ ስምንት ተወዳዳሪዎችን ለስትራቴጂክ ዕቅድ ገለጻ ኮሚቴው በመምረጥ ለውድድር አቅርቧል፡፡

ዕጩ ተወዳዳሪዎቹም የቦርድ አመራሮች፣ የሴኔት መማክርት አባላት፣የማኔጅመንት ሃላፊዎች፣በተቋሙ ከሚገኙ ከሁሉም የአካዳሚክ ዘርፎች እና የአስተዳዳር ክፍሎች የተወጣጡ የስራ ሃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ስትራቴጂክ እቅዳቸውን ማቅረብ ችለዋል፡፡

በተሰጣቸው አስራ አምስት ደቂቃ ስትራቴጅክ ዕቅዳቸውን በማቅረብ፣ ከተሳታፊ ለሚነሳላቸው ጥያቄ ለአስራ አመስት ተጨማሪ ደቂቃ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተደርጎ በሚስጥራዊ የድምጽ አሰጣጥ ሂደት ዕጩ #ተወዳዳሪዎች ድምጽ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡

በምርጫው ሂደት ከተሳተፉ ስምንት ዕጩዎች አምስቱ ተለይተው ለቀጣዩ ሂደት ለዩኒቨርሲቲው ቦርድ የቀረቡ ሲሆን፤መስፈርቱን በማሟላት ከአንድ እስከ አምስት የወጡ ጩዎች ይፋ ተደርገዋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

1. ዶ/ር ታከለ ታደሰ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) 88.33 በማምጣት 1ኛ
2. ዶ/ር አብርሃም አላኖ(ተባባሪ ፕሮፌሰር) 77.7 በማምጣት 2ኛ
3. ዶ/ር ሰለሞን ለማ (ተባባሪ ፕሮፌሰር) 72.94 በማምጣት 3ኛ
4. ዶ/ር ወንድሙ ወልዴ( ረዳት ፕሮፌሰር) 70.37 በማምጣት 4ኛ
5. ዶ/ር መስፍን ቢቢሶ(ተባባሪ ፕሮፌሰር) 66.78 በማምጣት 5ኛ ደረጃን የያዙ ሲሆን በአሰራሩ መሰረት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአመራርና አስተዳደደር #ሃላፊዎች ሹመትን አስመልክቶ የወጣውን መመሪያ በሚደነግገው መሰረት #የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ከሚቀርቡለት አምስት ዕጩዎች ሶስቱን ለይቶ ለትምህርት ሚኒስቴር እንሚልክ ተጠቁሟል፡፡

የውድድር ሂደቱ ፍጹም #ሠላማዊ እንደነበር እና መመሪያና ደንቡ በሚፈቅደው ልክ ግልጽ አሰራርን ተከትሎ ተግባራዊ መደረጉን የዩኒቨርሲቲው ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር #ቶላ_በሪሶ ገልጸዋል ሲል የዘገበው የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮሚኒዩኬሽንና ዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ነው፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥቆማ‼️

ስብስቤ ዋሻ-#ባሌ_ዲንሾ_ፓርክ አቅራቢያ ወይም ወደ ዲንሾ በሚወስደው መንገድ ከፍታ ቦታ ላይ #እሳት እንድተነሳ ጥቆማ ደርሶናል። የሚመለከተው አካል ጉዳዩን ይመልከተው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል መንግስት‼️

የአማራ ክልል መንግሥት በማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች #የተፈናቀሉ ዜጎችን በሁለት ወራት ውስጥ ወደ ቀያቸው ለመመለሥ እየሠራ መሆኑን የክልሉ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ #አሰማኸኝ_አስረስ ተናገሩ፡፡

አቶ አሰማኸኝ እንዳሉት በክልሉ ያሉት አጠቃላይ ተፈናቃዮች ቁጥር 90 ሺህ 736 ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ 60 ከመቶ አካባቢው ተፈናቃዮች ደግሞ ከማዕከላዊ እና ምዕራብ ጎንደር የተፈናቀሉ ናቸው፡፡

ተፈናቃዮችን በሁለት ወራት ውስጥ መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሆነም አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡

በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር የተቃጠሉ ቤቶችን ለመገንባት ከሚፈለገው የቤት ክዳን ቆርቆሮ 50 ከመቶውን መንግሥት መግዛቱን ያስታወቁት አቶ አሰማኸኝ ቀሪውን መንግሥት ከለጋሽ አካላት እየጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በማዕከላዊ ጎንደር 4 ሺህ 361 ቤቶች እና በምዕራብ ጎንደር 1 ሺህ 500 ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡

በመሆኑም የክልሉ መንግሥት 5 ሺህ 861 ቤቶችን ገንብቶና መንደር መሥርቶ ዜጎችን ሊያቋቁም መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡

የሚገነቡት ቤቶች እንደ ቤተሰብ ብዛት የሚለያዩ ናቸው፤ አራትና ከዚያ በታች አባላት ላሉት ቤተሰብ ባለ 40 ቆርቆሮ፣ ከአራት በላይ የቤተሰብ አባላት ላሏቸው ደግሞ ባለ 60 ቆርቆሮ ቤት እንደሚገነባ ነው የተናገሩት፡፡

#የመከላከያ_ሠራዊትና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች ኃላፊነቱን ወስደው በዞኖቹ እየሠሩ እንደሆነ አስታውቀው ‹‹ከዚህ በኋላ ወንጀለኞችን ለአንድም ደቂቃ ቢሆን አንታገስም›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በአማራ ክልል ከሚገኙ 90 ሺህ 736 ተፈናቃዮች 25 ከመቶው በመጠለያ ይገኛሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ በዘመድ ወዳጅ ተጠግተዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ናቸው፡፡

ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው #ለመመለስም እየተሰራ መሆኑን አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡ ለዚህም ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጋር ውጤታማ #ምክክር እየተደረገ ነው ብለዋል። አፈጻጸሙም የተፈናቀሉት ወገኖች ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ የሚተገበር ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ለገጣፎ ለገዳዲ‼️

በለገጣፎ ለገዳዲ ከተማ አስተዳደር ሕገወጥ ናቸው ተብለው የፈረሱ ቤቶች ጉዳይ የሰሞኑ መነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከኦሮሚያ ክልል የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው እስከ ትናንት ምሽት ድረስ 3,800 ቤቶች ፈርሰዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ቤቶቹ #በሕገወጥ መንገድ የተሰሩ በመሆናቸው የወሰድኩት #እርምጃ ሕግን የማስከበር ሥራ ነው ብሏል፡፡

ነዋሪዎች በበኩላቸው ከ10 እስከ 19 ዓመት ቤት ገንብተው መኖራቸውን የአፈር ግብር ለመንግሥት እንደሚከፍሉና ውሃና መብራትን ጨምሮ መሰረተ ልማት የከተማ አስተዳደሩ እንዳሟላላቸው ለተለያዩ መገናኛ ብዙሃን መናገራቸው ይታወቃል፡፡ ነዋሪዎች ቤታችን በመፍረሱ ጎዳና ላይ ወድቀናል የሚል #እሮሮ እያሰሙ ነው፡፡

የኦሮሚያ ክልል የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ቢሮ ሃላፊውን ዶክተር #ሚልኬሳ_ሚደግሳ ሸገር 102.1 ራድዮ በጉዳዩ ዙሪየ አነጋግሯቸዋል።

Via Sheger FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia