TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኮምቦልቻ🔝

የጉዞ አድዋ ተጓዦች ኮምቦልቻ ከተማ ቆይታ አድርገዋል። #ኤርሞን_መኮንን ሰላም እንደሆነ እና መጓዝ እንደሚችል ገልጿል። ከደሴ በኃላ ጫማ ተጫምቶ በእግር ይጓዛል የተባለውም ከእውነት የራቀ እንደሆነ ገልፆ፤ ጉዞውን በእግሩ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

©ዮሴፍ አለማየሁ(TIKVAH-ETH ኮምቦልቻ ዩኒቨርሲቲ)
@tikvahethiopia @tsegabwolde
Audio
ሃላሌ!! #ይርጋለም!!

የአገር ሸማግሌዎች፣ የሀይማኖት አባቶችና ወጣቶች የተገኙበት የሰላም ኮንፈረንስ #በይርጋለም ከተማ ተካሂዷል፡፡

ወጣቶች ጥያቄያቸው ምላሽ እስኪያገኝ ድረስ የሲዳማ "ሃላሌ" ባህላዊ ስርዓት ተከትለው በሰላማዊ መንገድ እንዲጠይቁ የሲዳማ አገር ሸማግሌዎች አሳስበዋል፡፡

"ኤጄቶዎች" ወይም የሲዳማ ወጣቶችና አገር ሸማግሌዎች የጋራ የሰላም ኮንፈረንስ ማካሄድ ከጀመሩ በኋላ ለውጥ መታየቱን የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ #ሚሊዮን_ማቲዮስ አስታውቋል፡፡

"ኤጄቶዎች" የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የሚረጋገጥበትን ህዝበ ውሣኔ እንዲያስፈፅም የክልሉ ምክር ቤት ለምርጫ ኮሚሽን ቢስታውቅም ዘግይቷል ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

ምንጭ፦ የአሜሪካ ድምፅ ራድዮ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቴፒ‼️

በደቡብ ክልል በቴፒ ከተማ #ለተቃዉሞ አደባባይ በወጡ ወጣቶች ላይ ፀጥታ አስከባሪዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ አራት ሰዎች ተገደሉ። ሌሎች ሰባት ቆሰሉ። የዐይን ምስክሮች እንዳሉት ከሟቾቹ አንዱ የአስራ ሶስት ዓመት ታዳጊ ወጣት ነዉ ተብሏል። የጀርመን ድምፅ ራድዮ የከተማይቱን ነዋሪዎች ጠቅሶ እንደዘገበዉ ከግጭቱ በኋላ የከተማይቱ የንግድ፣ የትራንስፖርትና የመንግሥት መስሪያቤቶች እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ #ተቋርጧል። ፀጥታ አስከባሪዎች የከተማይቱን ዋና ዋና መንገዶችን በጥብቅ እየተቆጣጠሩ ነዉ። የቴፒና የአካባቢዋ ነዋሪዎች የራስ አስተዳደር ጥያቄ በማንሳት አደባባይ መዉጣት ከጀመሩ ካለፈዉ ጥቅምት ጀምሮ ነዋሪዎችና ፀጥታ አስከባሪዎች በተደጋጋሚ ይጋጫሉ። በየግጭቱ የሰዉ ሕይወት ይጠፋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወሻ🗓ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ በነገው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ። የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ ልዩ ስብሰባ በነገው ዕለት እንደሚያካሂድ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፌደራል ፖሊስ‼️

ባለፉት 6 ወራት በርካታ ሽጉጥ፤ ክላሽ፤ በርካታ ጥይቶች፤ቦንብ እና የቡድን መሳሪያ መትረጊስ በአራቱም አቅጣጫዎች ማለትም በደቡብ ሞያሌ፤ በምስራቅ ቶጎ ውጫሌ፤ በምዕራብ ጋንቤላ ሱዳን አዋሳኝ፤በሰሜን ከሱዳን መተማ ፤ እና በቤንሻጉል ጉምዝ አካባቢ ወደ ሃገር ውስጥ እንደሚገባና ቱርክ ሰራሽ እንደሆነ ተረጋግጧል፡፡

ይህ ህገ ወጥ መሳሪያም በፌደራል ፖለስ ኮሚሽን፤ የሀገር መከላከያ ሚንስቴር፤ የቢሄራዊ መረጃ ደህንነት አገልግሎት እና ከጉምሩክ ኮሚሽን እንዲሁም ከሰፊው ሰላም ወዳድ ህዝብ ጋር በመቀናጀት ከበፊቱ ጋር ሲነጸጸር ቀንሷል፡፡ሌላው ሊቀንስ የቻለበት ምክንያት ደግሞ በማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎትና በተቋሙ ሚዲየሞች አማካኝነት ህብረተሰቡ ስለ ህገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር አስከፊነት በፌደራልና በክልሎች ደረጃ በማስተማር የህዝቡን ተሳትፎ በማሳደግ መቀነስ ተችሏል፡፡

በፍተሻ ኬላዎቹም ጥብቅ ፍተሻ ቢደረግም ከዋናው መንገድ ውጭ ባሉ መንገዶች በጋማ ከብትና በሞተር እያጓጓዙ ወደ አራቱም አቅጣጫዎች እንደሚያስገቡ ተገጸል። ይህን የሃገር ሰላም የሚያናጋ ህገ ወጥ የመሳሪያ ዝውውር ግጭት እንዳይባባስ ህብረተሰቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ተቀናጅቶ እየሰራ ያለውን ተግባር አጠናክሮ በመቀጠል ሰላም የሰፈነባትና #የተረጋጋች ኢትዮጵያን መፍጠር ይኖርበታል፡፡

ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ‼️

በአዲስ አበባ ከተማ በዳቦ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ አግባብነት የሌለውና ህብረተሰቡን ያላማከለ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን አሰሙ፡፡

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ በበኩሉ በዳቦ ዋጋ ላይ አግባብነት የሌለው ጭማሪ ባደረጉ ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል።

ቢሮው በከተማዋ ባሉ ዳቦ ቤቶች ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ምንም አይነት እውቅና ያልተሰጠውና አግባብነት የጎደለው በመሆኑ ይሄንን አድርገው በሚገኙ ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጿል።

የዋጋ ጭማሪውን አስመልክቶ ኢዜአ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ ባደረገው ምልከታ በትክክል የዋጋ ጭማሪ መኖሩን አረጋግጧል።

በዚህም ባለ 100 ግራም ዳቦ በ2 ብር ከ50 ሳንቲም፣ ባለ 200 ግራም ዳቦ በ5 ብር እንዲሁም ባለ 300 ግራም ዳቦ በ7 ብር ከ50 ሳንቲም እየተሸጠ እንደሚገኝ ተመልክቷል።

አስተያየታቸውን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የሰጡ የመዲናዋ ነዋሪዎችም የተደረገው የዋጋ ጭማሪ አግባብነት የሌለውና ህብረተሰቡን ያላማከለ ነው ሲሉም ቅሬታቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።

በመሆኑም መንግስት ይህንን ተግባር በሚፈጽሙ አካላት ላይ አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ እንደሚገባውም አስተያየታቸውን ገለጸዋል።

አቶ አክሊሉ ቢንያ አንድ ብር ከሰላሳ ሳንቲም ይሸጥ የነበረው ዳቦ ዛሬ ሁለት ከአምሳ ገብቷል፡፡ ይህ ደግሞ አግባብ አለመሆኑን ነው የተናገሩትአቶ ጉታ አዱኛ በበኩላቸውየዳቦ ጭማሬው በጣም አስገራሚ እንደሆነ የከተማ አስተዳደሩ አስቸኮይ መፍቴህ ሊሰጠው እንደሚገባ ነው የተናገሩት “የዳቦ ጭማሪው አግባብነት የለውም፤ በአንድ ጊዜ የ1 ብር ከ20 ሳንቲም ጭማሪ እግባብ አይደለም፤ ሁለተኛ ነገር መንግስት ባለበት አገር እንደዚህ አይነት ነገር ሲፈጸም መንግስት ምን እየሰራ ነው? ምንድነው እያደረገ ያለው አፋጣኝ የሆነ እርምጃ ሊሰጠው ይገባል።” ያለው ወጣት ዘላለም ጤናው ነው።

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ አቶ መስፍን አሰፋ በበኩላቸው መንግስት ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በየወሩ 165 ሺህ ኩንታል በድጎማ ያቀርባል።

በዚህም በከተማዋ 1 ሺ 400 ከሚሆኑ ዳቦ ቤቶች ጋር ከ100 ግራም ጀምሮ በ1 ብር ከ30 ሳንቲም እንዲሸጡ የሚያደርግ ትስስር በመፍጠር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

ይሁንና በአሁኑ ወቅት በከተማዋ ዳቦ ቤቶች ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ምንም አይነት እውቅና ያልተሰጠውና አግባብነት የጎደለው መሆኑንም ተናግረዋል።

በዚህም በተተመነላቸው ዋጋ መሰረት የማይሸጡና ከዚህ ዋጋ በላይ ጨምረው በሚሸጡ ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ እንደሚወሰድም ጠቁመዋል።

በዚህም ቢሮው ባደረገው ክትልል በሁለት ቀናት ውስጥ በኮልፌ ክፍለ ከተማ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ አድርገው የተገኙ ሶስት ዳቦ ቤቶች እንዲሁም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አንድ ዳቦ ቤት ላይ እርምጃ መውሰዱን ጠቁመዋል።

ሌሎችም ከዚህ ድርጊት እንዲቆጠቡና ህብረተሰቡን በአግባቡ እንዲያገለግሉና የተጣለባቸውን ሃላፊነት መወጣት እንደሚገባቸውም አሳስበዋል።

ህብረተሰቡም በሸቀጦች ላይ አላስፈላጊ ጭማሪን በሚመለከትበት ጊዜ ለሚያጋጥሙት ህገ-ወጥ ተግባራት በነጻ የስልክ መስመር 8885 ላይ ጥቆማ እንዲያደርግም ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ኢ ዜ አ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቴላቪቭ‼️

በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ። የ24 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ይሁዳ ባይድጋ ከሁለት ሳምንት በፊት ነበር በፖሊስ ተተኩሶበት #የተገደለው#ሰልፈኞቹ የቴላቪቭ ዋና ጎዳናን #በመዝጋት እና በዋና ዋና መንገዶች በማለፍ ባካሄዱት ሰልፍ በእሥራኤል ዘረኝነትን እና ፖሊስ የሚፈጽመውን ከመጠን ያለፈ ጥቃት እና አድልዎ #ተቃውመዋል። በእስራኤል ምክር ቤት የሰብአዊ ሐብት ሎጂስቲክ አስተባባሪ አቶ ዮናታን ታከለ ለጀርመን ድምፅ ራድዮ እንደተናገሩት ኢትዮጵያዊውን የገደለው ፖሊስ አሁንም በስራ ላይ ነው። ይህም ቤተ እስራኤላውያንን በእጅጉ አስቆጥቷል። የዐአእምሮ ህመምተኛው ልጃቸው ይሁዳ ከቤቱ ስለት ይዞ ሲወጣ ፣እንዲደርስላቸው እናቱ ደውለው የነገሩት ፖሊስ ተኩሶ እንደገደለው ተዘግቧል። በእሥራኤል ጦር ውስጥ ማገልገሉ የተነገረውን የይሁዳን አሟሟት የእስራኤል የፍትህ ሚኒስቴር እያጣራሁ ነው ብሏል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአሜሪካ በተከሰተው ከፍተኛ ቅዝቃዜ እስካሁን ቢያንስ ስምንት ሰዎች #መሞታቸው ተገለጸ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ሜድ ዌስት የተከሰተው ቅዝቃዜ በአስር አመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ አደገኛ ነው፡፡ አደገኛና ገዳይ በተባለው ቅዝቃዜ አንድ ተማሪ ከኮሌጅ ውጭ ሞቶ የተገኘ ሲሆን ሌሎች ስድስት ሰዎች መሞታቸው ታውቋል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪ በቅዝቃዜው ክፉኛ የተጎዱ ነዋሪዎች የሚገኙ ሲሆን በሆስፒታሎች እንክብካቤና ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑም ታውቋል፡፡ቅዝቃዜው በተከሰተባቸው የአሜሪካ ግዛቶች ከፍተኛና አደጋ አድራሽ በረዶ በአገሪቱ መጣል መጀመሩም የቢቢሲ ዘገባ አመልክቷል፡፡ በአብዛኛው የአሜሪካ ግዛት ቅዝቃዜው ከዜሮ በታች ሲሆን ዘጠኝ ሚሊዮን የአሜሪካ ነዋሪ ከአስራ ሰባት ሴንቴግሬድ በታች የሆነ ቅዝቃዜ በማስተናገድ ላይ ይገኛል፡፡ እንደ አሜሪካ ሜትሮሎጂ ዘገባ የአሜሪካዋ ሶስተኛ ከተማ ቺካጎ በታሪኳ ከፍተኛ የሆነውም ኔጌቴቭ 32 ቅዝቃዜ ዛሬ እንደምታስተናግድ አመልክቷል፡፡

Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Vote‼️

እጅግ በርካታ ከሚባሉ ከተሞች እንደሚደርሰን ጥቆማ የከተማ ውስጥ ውንብድና እና ዝርፊያ እየከፋ መጥቷል። የፖሊስ ስራ #አጠያያቂም እየሆነ እንደሆነ እየተነገረን ነው። በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች መንግስት የፖሊስ ሀይሉን ሊፈትሽ ይገባል ብለዋል። በሀገራችን ልንዘረፍ፤ አምሽተን ለመስራት ልንሳቀቅ አይገባም ሲሉ ይናገራሉ።
.
.
ውድ የTIKVAH-ETH ቤተሰቦች እናተ በምትኖሩበት አካባቢና ከተማ የህዝብን ፀጥታ ለማስጠበቅ ብሎ መንግስት ያሰማራቸው የአካባቢና የከተማ ፖሊስ ላይ ያላችሁ ምልከታ ምን ይመስላል??

የአካባቢና የከተማ ፖሊስ ላይ #እምነት አላችሁ?

እምነት አለን
እምነት የለንም

🔹የሚመለለታችሁ አካላት ይህ የድምፅ አሰጣጥ ለቀጣይ ስራችሁ ግብአት ይሆናል ብለን እናስባለን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ🔝

ዛሬ በድሬዳዋ ከተማ የፖሊስ መሬት ፖሊስ ጣቢያ አመራርና አባላት #ከራሳቸው መዋጮ በማዋጣት በቀበሌ 09 ለፀጥታና ህግ ማስከበር ስራ ለተመደቡ #የመከላኪያ_ሰራዊት_አባላት ወድማዊ የሆነ ምሳ ግብዣ አድርገዋል።

ምንጭ፦ ድሬዳዋ ፖሊስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኧረ እንንቃ‼️

በዚህች #ድሃ በሆነች ሀገር ላይ እየኖርን #የጎደለንን ለሟሟላት ከመጣር ይልቅ ያለንን #በማጉደል ላይ ተጠምደናል። ምቀኝነት፣ ተንኮል፣ ክፋት፣ መጠላለፍ፣ ማጥላላት፣ መከፋፈል፣ መባላት፣ ለጦርነት መንደርደር፣ ሰው አለማክበር የማንነታችን መገለጫ ሊሆን አይገባም። ያለችን አንድ ሀገር ናት ሰርተን እንቀይራት!! እንዋደድ፤ እንከባበር፤ መጥፎ ስራዎችን እየፀየፍ፤ አንድ የሚያደርገን #ሰውነት ነው።

#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 23/2011 ዓ.ም.

ከትራንስፓርት ሚንስቴርና ከሌሎች ሚንስቴር መስሪያ ቤቶች የተወጣጣው የሉኡካን ቡድን የጅቡቲ ወደብን ጎብኝቷል።
.
.
ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ በምዕራብ እንዲሁም ምሥራቅ ጉጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይልና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች መካከል በታካሄደ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን በርካቶች ከቤታቸው መፈናቀላቸው ተናግረዋል።
.
.
ከአመት በፊት ሳውዲ አረቢያ ጀምራው የነበረውን መጠነ ሰፊ የፀረ-ሙስና ዘመቻ እንዳጠናቀቀች አስታውቃለች፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት 100 ቢሊዮን ዶላር በጥሬ ገንዘብ እና በቁስ መልክ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ሰዎች መሰብሰቡን አስታውቋል።
.
.
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ የፀደቀውን #የስደተኞች_አዋጅ በመቃወም ነገ በጋምቤላ ከተማ ሊደረግ ለታሰበው የተቃውሞ ሰልፍ ፈቃድ #ከልክሏል
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ6 ሺህ ነጋዴዎች ግብር ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ ግብር ስረዛው ከ2003 እስከ 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከፍተኛ የግብር ተመን ተጥሎባቸው አቤቱታ ሲያቀርቡ የቆዩትን ነጋዴዎች ያካትታል፡፡
.
.
4ኛው የህዝብና ቤት ቆጠራ ከመጋቢት 29 ቀን ጀምሮ ይካሄዳል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህግን ተከትለው የሚሰሩ የሪል ስቴት አልሚዎችን እንደሚደግፍ ነገር ግን ህገወጥ የሆኑት ላይ #ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ወረዳ በጫነው አሸዋ ላይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
.
.
በቴፒ ከተማ ከትንላንት ጀምሮ ዳግም #ያገረሸው #አለመረጋጋት ዛሬም ቀጥሏል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጦ ውሏል። ከተማዋ በፀጥታ ሃይሎች በከፍተኛ ደረጃ እየተጠበቀች ነው።
.
.
ዛሬ በስራ ላይ የሚውለውን የነዳጅ ዋጋ መጨመር ተከትሎ ምንም አይነት #የትራንስፖርት_ታሪፍ  ጭማሪ #እንደማይኖር የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገልጿል።
.
.
ጅቡቲ በተካሄደው 15ኛው የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ የተካፈሉ የኢትዮጵያ ልዑካን ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያይተዋል።
.
.
በኦሮሚያ ክልል ለመንግስት ሰራተኞች #አዲስ የስራ ምደባ እየካሄደ መሆኑን የክልሉ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
.
.
#ኮማንድ_ፖስቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 3 ወረዳዎች ላይ በቁጥጥር ስር ካዋላቸዉ 528 ተጠርጣሪዎች 440 የሚሆኑትን በነፃ አሰናብቷል።
.
.
የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ የሆነው ከአዋሽ እስከ ኮምቦልቻ ያለው 270 ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ 97 በመቶ #መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ገልጿል።
.
.
በሱማሌ ክልል ከምሽቱ 4 ሰዓት ጀምሮ ሰዓት ዕላፊ ገደብ ተጥሏል፡፡ የአደባባይ ስብሰባም ተከልክሏል፡፡
.
.
#ቴዎድሮስ_አዲሱ(ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ ቢፈቀድለትም #በሙስና_ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ለሚያልፉ ዐለም ዐቀፍ መንገደኞች #የነጻ ጉብኝት መርሃ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
.
.
የኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ዘርፍ ማህበር እና #የሰላም_ሚኒስቴር በጋራ በመሆን የሰላም ሚዲያ ህብረት ትስሰር ለመፍጠር የሚያስችል ውይይት ዛሬ ማምሻውን አካሂደዋል።
.
.
የሐረሪ ክልል የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ #መሻሻል ማሳየቱን የክልሉ ፍትህና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ  አስታውቋል።
.
.
#ብሄሬን መሰረት ተደርጎ ጥቃት ተፈፅሞብኛል በሚል በሀሰት የሽንት መሽኛ #ብልቱን በፋሻና ፕላስተር በመጠቅለል ግጭት ለመቀስቀስ የሞከረው ግለስብ ድሬ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ በዳቦ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ አግባብነት የሌለውና ህብረተሰቡን ያላማከለ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
.
.
በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።
.
.
በአሜሪካ በተከሰተው ከፍተኛ ቅዝቃዜ እስካሁን ቢያንስ ስምንት ሰዎች #መሞታቸው ተገለጸ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ሜድ ዌስት የተከሰተው ቅዝቃዜ በአስር አመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ አደገኛ ነው፡፡
.
.
ምንጭ፦ etv፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ራድዮ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ bbc፣ VOA፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia