ኦነግ እና ODP‼️
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ODP) እና የኦነግ አመራሮች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ በሁለቱ መካከል ያለውን ስምምነት በማጠናከርና ችግሮችን በመፍታት #አብረው ለመስራት #ተስማምተዋል፡፡
የODP ምክትል ሊቀመንበር አቶ #ለማ_መገርሳ ከዚህ በኋላ ከኦነግ ጋር በመደማመጥ ለአገር እድገት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
አቶ ለማ ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጋር አብሮ ለመስራትና የኦነግ ሰራዊት የመንግስት አካል ሆኖ ተጨማሪ አቅም እንዲሆን በአስመራ ስምምነት መደረሱን ገልጸዋል፡፡
በዚህ ስምምነት መሰረት ኦነግ ወደ አገር ገብቶ ስራ መጀመሩን የገለጹት አቶ ለማ፣ አለመረጋጋት የተፈጠረው ስምምነቱ ፈርሶ ሳይሆን ካለመረዳዳት የመነጫ ነው ብለዋል፡፡
ከእንግዲህ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር ሁለቱ ፓርቲዎች መስማማታቸውን አቶ ለማ ተናግረው፣ የODP አባላትና የጸጥታ ኃይሎች ይህንን ስምምነት ተረድተው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል፡፡
ወደ ትናንትናው ላለመመለስ በጋራ ቃል ተገባብተው አብረው ለመስራት እንደተስማሙም አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡
የኦነግ ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ በበኩላቸው፣ በአስመራ የተደረሰውን ስምምነት በመተግበር ከODP ጋር አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን ገልጸዋል፡፡
አቶ ዳውድ ኢብሳ ከODP አብረው ለመስራት መስማማታቸውንና የኦነግ አባላትና ደጋፊዎች ለዚህ ስምምነት የበኩላቸውን አስተዋዕኦ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ:- OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ODP) እና የኦነግ አመራሮች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ በሁለቱ መካከል ያለውን ስምምነት በማጠናከርና ችግሮችን በመፍታት #አብረው ለመስራት #ተስማምተዋል፡፡
የODP ምክትል ሊቀመንበር አቶ #ለማ_መገርሳ ከዚህ በኋላ ከኦነግ ጋር በመደማመጥ ለአገር እድገት በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
አቶ ለማ ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጋር አብሮ ለመስራትና የኦነግ ሰራዊት የመንግስት አካል ሆኖ ተጨማሪ አቅም እንዲሆን በአስመራ ስምምነት መደረሱን ገልጸዋል፡፡
በዚህ ስምምነት መሰረት ኦነግ ወደ አገር ገብቶ ስራ መጀመሩን የገለጹት አቶ ለማ፣ አለመረጋጋት የተፈጠረው ስምምነቱ ፈርሶ ሳይሆን ካለመረዳዳት የመነጫ ነው ብለዋል፡፡
ከእንግዲህ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር ሁለቱ ፓርቲዎች መስማማታቸውን አቶ ለማ ተናግረው፣ የODP አባላትና የጸጥታ ኃይሎች ይህንን ስምምነት ተረድተው መንቀሳቀስ አለባቸው ብለዋል፡፡
ወደ ትናንትናው ላለመመለስ በጋራ ቃል ተገባብተው አብረው ለመስራት እንደተስማሙም አቶ ለማ ተናግረዋል፡፡
የኦነግ ሊቀመንበር አቶ #ዳውድ_ኢብሳ በበኩላቸው፣ በአስመራ የተደረሰውን ስምምነት በመተግበር ከODP ጋር አብሮ ለመስራት መስማማታቸውን ገልጸዋል፡፡
አቶ ዳውድ ኢብሳ ከODP አብረው ለመስራት መስማማታቸውንና የኦነግ አባላትና ደጋፊዎች ለዚህ ስምምነት የበኩላቸውን አስተዋዕኦ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ:- OBN
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክርቤት ኤርትራ ላይ ጥሎት የነበረውን #ማዕቀብ አንስቷል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ማዕቀቡ በመነሳቱ ለመላው የኤርትራ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ማዕቀቡ በመነሳቱ ለመላው የኤርትራ ህዝብ እንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የቀድሞውን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀኔራል አቶ #ያሬድ_ዘሪሁንን አስመልጠዋል በሚል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ። ዛሬ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ የወንጀል ችሎት አቶ ያሬድን አስመልጠዋል የተባሉት የነብስ አባቱ አባ ሃይለማርያም ሃይለሚካኤል እና ሾፌራቸው አሸናፊ ታደለ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። መርማሪ ፖሊስ ተጠርጣሪውን ለመያዝ በሚል ችሎቱን የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል። ችሎቱም መርማሪ ፖሊስ ያቀረበው ሃሳብ ተቀባይነት የለውም በሚል ፖሊስ በ10 ቀን ውስጥ #አጣርቶ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሚመለክተው አካል‼️
በሞያሌ አካባቢ ችግር እንዳለ የTIKVAH-ETH ተከታዮች እያሳወቁን ይገኛሉ። መንግስት ችግሩ ሳይከፋ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እና የተፈጠረውን ችግር እንዲፈታ ተጠይቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሞያሌ አካባቢ ችግር እንዳለ የTIKVAH-ETH ተከታዮች እያሳወቁን ይገኛሉ። መንግስት ችግሩ ሳይከፋ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ እና የተፈጠረውን ችግር እንዲፈታ ተጠይቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የረድዔት ድርጅቶች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጸጥታ ችግሩ ባለመሻሻሉ በካማሺ እና ኦዳ ዞኖች ላሉ ተፈናቃዮች ዕርዳታ ለማድረስ ተቸግረዋል፡፡ የተመድ አስቸኳይ ጊዜ ዕርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) በድረ ገጹ እንደገለጸው ላንድ ጊዜ ዕርዳታ ብቻ ለተፈናቃዮች የደረሱት በወታደር የታጀቡ የመንግሥት ባለሥልጣናት ብቻ ናቸው፡፡ ከሳምንታት በፊት በተከሰቱ ማንነትን መሠረት ባደረጉ ግጭቶች በካማሺ ዞን 42 ሺህ፣ በኦዳ ዞን ደሞ 15 ሺህ ተፈናቃዮች አስቸኳይ ዕርዳታ ይፈልጋሉ፡፡
©wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
©wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትግራይ ክልል‼️
የትግራይ ህዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት በሃገሪቱ የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር መሆኑን የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ።
የክልሉ መንግስት ዛሬ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው መንግስት አሁን የጀመረው የህግ የበላይነትን የማስከበር ሂደት በተገቢው ጥንቃቄ ሊከናወን የሚገባው ነው።
ሰብአዊ ጥሰትና ሙስና በፈጸሙ ሰዎች ላይ በመንግስት ሰሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ የህግ ልዕልና ሳይሸራረፍ ከተጽዕኖ በጸዳ መልኩ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት መግለጫው አመልክቷል።
የትግራይ ህዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ እንዲያተኩር ጠቁሟል።
በሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የሙስና ችግርና ህገ-መንግስታዊ ጥሰት ውስጥ እጃቸው ያለ አመራሮችና ተቋማት ስለመኖራቸው ቀደም ሲል በተካሔዱ የኢህአዴግ መድረኮች ውይይት መደረጉንም አመልክቷል።
ችግሩ በእኩል እንዲስተናገድ ከማድረግ ባለፈ እርቅና ይቅር ባይነትን መሰረት አድርጎ የተጀመረው ሂደት ወደ ኋላ እንዳይመለስ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቅሷል።
“የህግ የበላይነትም ሳይሸራረፍ እንዲተገበር ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥናት የሚጠይቅ መሆኑንም የክልሉ መንግስት ያምናል” ብሏል መግለጫው፡፡
የትግራይ ክልል ህዝብ ከሌሎች ብሔሮችና ብሔረሰቦች ጋር በመሆን የከፈለው መስዋዕትነት የዜጎች እኩልነትና ሰብአዊ መብት እንዲከበር እንጂ በማንም አካል እንዲጣስ እንዳልሆነ መግለጫው አመልክቷል።
ባለፉት ዓመታት ይታዩ የነበሩት የፍትህና የዲሞክራሲ መጓደሎች እንዲስተካከሉ ህዝቡ በፅናት እየታገለ መምጣቱንም መግለጫው አስታውሶ በጥልቅ ተሀድሶ ወቅት ህዝቡ ያሳየው ተሳትፎ አንዱ ማሳያ መሆኑን አስረድቷል።
ከሰብአዊ መብት አያያዝና ከሙስና ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እየታየ ላለው ሁኔታ ተጠያቂዎቹ እጃቸው ያለበት አመራሮችና ተቋማት መሆናቸውንም መግለጫው አመልክቷል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትግራይ ህዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት በሃገሪቱ የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር መሆኑን የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ።
የክልሉ መንግስት ዛሬ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው መንግስት አሁን የጀመረው የህግ የበላይነትን የማስከበር ሂደት በተገቢው ጥንቃቄ ሊከናወን የሚገባው ነው።
ሰብአዊ ጥሰትና ሙስና በፈጸሙ ሰዎች ላይ በመንግስት ሰሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ የህግ ልዕልና ሳይሸራረፍ ከተጽዕኖ በጸዳ መልኩ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት መግለጫው አመልክቷል።
የትግራይ ህዝብ ለዓመታት የከፈለው መስዋዕትነት የህግ የበላይነት እንዲከበርና በማንኛውም ወቅት ተጠያቂነት እንዲኖር ለማድረግ መሆኑን ያመለከተው መግለጫው መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ እንዲያተኩር ጠቁሟል።
በሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የሙስና ችግርና ህገ-መንግስታዊ ጥሰት ውስጥ እጃቸው ያለ አመራሮችና ተቋማት ስለመኖራቸው ቀደም ሲል በተካሔዱ የኢህአዴግ መድረኮች ውይይት መደረጉንም አመልክቷል።
ችግሩ በእኩል እንዲስተናገድ ከማድረግ ባለፈ እርቅና ይቅር ባይነትን መሰረት አድርጎ የተጀመረው ሂደት ወደ ኋላ እንዳይመለስ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቅሷል።
“የህግ የበላይነትም ሳይሸራረፍ እንዲተገበር ከፍተኛ ጥንቃቄና ጥናት የሚጠይቅ መሆኑንም የክልሉ መንግስት ያምናል” ብሏል መግለጫው፡፡
የትግራይ ክልል ህዝብ ከሌሎች ብሔሮችና ብሔረሰቦች ጋር በመሆን የከፈለው መስዋዕትነት የዜጎች እኩልነትና ሰብአዊ መብት እንዲከበር እንጂ በማንም አካል እንዲጣስ እንዳልሆነ መግለጫው አመልክቷል።
ባለፉት ዓመታት ይታዩ የነበሩት የፍትህና የዲሞክራሲ መጓደሎች እንዲስተካከሉ ህዝቡ በፅናት እየታገለ መምጣቱንም መግለጫው አስታውሶ በጥልቅ ተሀድሶ ወቅት ህዝቡ ያሳየው ተሳትፎ አንዱ ማሳያ መሆኑን አስረድቷል።
ከሰብአዊ መብት አያያዝና ከሙስና ጉዳዮች ጋር በተያያዘ እየታየ ላለው ሁኔታ ተጠያቂዎቹ እጃቸው ያለበት አመራሮችና ተቋማት መሆናቸውንም መግለጫው አመልክቷል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥቆማ ለኢትዮጵያ መንግስት‼️
የደቡብ ክልል መንግስት እና የፌደራሉ መንግስት በጉራጌ ዞን ያለውን ሁኔታ አጣርቶ የመፍትሄ እርምጃ እንዲወስድ እና ችግሩን እንዲፈታ ጥሪ እናቀርባለን።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የደቡብ ክልል መንግስት እና የፌደራሉ መንግስት በጉራጌ ዞን ያለውን ሁኔታ አጣርቶ የመፍትሄ እርምጃ እንዲወስድ እና ችግሩን እንዲፈታ ጥሪ እናቀርባለን።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፍፁም የሺጥላ🔝የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ #ፍጹም_የሽጥላ ከሜቴክ ጋር በተያያዘ #በሙስና ወንጀል ተጠርጥራ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርባለች። በችሎቱ የተከላካይ ጠበቃ ልታገኝ ባለመቻሏ ፍርድ ቤቱ ለነገ ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA via @like
እንኳን ደስ አለን💥💫የTIKVAH-ETH የሞባይል መተግበሪያ ነገ ለህዝብ ይደርሳል!
የTIKVAH-ETH የሞባይል መተግበሪያን (application) ለመቀበል ዝግጁ ናችሁ??✅
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የTIKVAH-ETH የሞባይል መተግበሪያን (application) ለመቀበል ዝግጁ ናችሁ??✅
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንኳን ደስ አለን💥💫የTIKVAH-ETH የሞባይል መተግበሪያ(application) ነገ ምሽት 2:00 እናተ ጋር ይደርሳል!!
.የተመረጡ ሀገር ውስጥ እና የውጭ ዜናዎች
.ስፖርት
.ቢዝነስ
.መዝናኛ
Apk. 4.1 mb (ነገ ምሽት እናሰራጨዋለን) ለአድሮይድ!
➕ለአይፎን(ios) ተጠቃሚዎች በሚቀጥለው ወር ይቀርባል።
መተግበሪያው፦ የቻናላችንን ተደራሽነት ለመጨመር በማሰብ የተዘጋጀ ነው። የቴሌግራም ቻናላችን #ተጠናክሮ ይቀጥላል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.የተመረጡ ሀገር ውስጥ እና የውጭ ዜናዎች
.ስፖርት
.ቢዝነስ
.መዝናኛ
Apk. 4.1 mb (ነገ ምሽት እናሰራጨዋለን) ለአድሮይድ!
➕ለአይፎን(ios) ተጠቃሚዎች በሚቀጥለው ወር ይቀርባል።
መተግበሪያው፦ የቻናላችንን ተደራሽነት ለመጨመር በማሰብ የተዘጋጀ ነው። የቴሌግራም ቻናላችን #ተጠናክሮ ይቀጥላል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ታዋቂ እና አነጋጋሪ መፅሃፍት በገበያ ላይ ዋሉ‼️መፅሀፍቱን በሁሉም መፅሀፍት ቤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ያገኛሉ። ተጨማሪ በዚህ ስልክ በመደወል መፅሀፍቱን ማግኘት ይቻላል፦ +251911650882