This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ-አዲስ አበባ⬆️
የቀድሞው የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #ክንፈ_ዳኛው በቁጥጥር ስር ውለው አዲስ አበባ ሲገቡ።
ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቀድሞው የሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #ክንፈ_ዳኛው በቁጥጥር ስር ውለው አዲስ አበባ ሲገቡ።
ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማረሚያ ገብተዋል‼️በቁጥጥር ስር የዋሉት ሜጀር ጀነራል #ክንፈ_ዳኘው አዲስ አበባ ገብተው ወደ ማረሚያ ቤት አቅንተዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አቶ #ጌታቸው_አሰፋ ተይዘዋል ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው። የቀድሞ የደህንነት ሀላፊ እስካሁኗ ሰዓት ድረስ በፖሊስ ቁጥጥር ስር አልዋሉም።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update 20ኛው የአፍሪካ ህብረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰብ ነገ ይጀምራል። ምክር ቤቱ በመሪዎች ስብሰባ ወቅት ውሳኔ በሚተላለፍባቸው ረቂቅ አጀንዳዎች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል። በስብሰባው ለመሳተፍ የበርካታ የአፍሪካ አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አዲስ አበባ ገብተዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update አዲስ አበባ ከተለያዩ አካባቢዎች ታፍሰው የተወሰዱና በእስር ላይ ያሉ ወጣቶች ፍርድ ቤት አልቀረብንም ሲሉ ለጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንቷ #ቅሬታቸውን አሰሙ፡፡
ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኤርትራ ማዕቀቡ ሊነሳላት ነው‼️
የመንግስታቱ ድርጅት የኤርትራን #ማዕቀብ በነገው ዕለት #ሊያነሳ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ላለፉት 10 ዓመታት ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ለማንሳት ውሳኔዎች እንደሚያስተላልፍ ተገልጿል፡፡
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ያደረገችውን የሰላም ስምምነት እንዲሁም ከጅቡቲ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል ያደረገችውን ጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው ማዕቀቡን ለማንሳት የፀጥታው ምክር ቤት አባላት ተደራድረው የጨረሱት፡፡
ሮይተርስ የድርጅቱን ዲፕሎማቶች ጠቅሶ እንደዘገበው ማዕቀቡን ለማንሳት በእንድሊዝ የቀረበውን ረቂቅ 15 የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላትያለልዩነት እንደሚቀበሉት ይጠበቃል፡፡
ኤርትራ የሶማሊያውን አልሸባብ ለሚባለው ቡድን እገዛ ታደርጋለች በሚል እንደአውሮፓዊያኑ አቆጣተር በ2009 አ.ም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማዕቀቡን እንደጣለባት ይታወሳል፡፡
ምንጭ፦ ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመንግስታቱ ድርጅት የኤርትራን #ማዕቀብ በነገው ዕለት #ሊያነሳ ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ላለፉት 10 ዓመታት ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ለማንሳት ውሳኔዎች እንደሚያስተላልፍ ተገልጿል፡፡
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር ያደረገችውን የሰላም ስምምነት እንዲሁም ከጅቡቲ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማሻሻል ያደረገችውን ጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው ማዕቀቡን ለማንሳት የፀጥታው ምክር ቤት አባላት ተደራድረው የጨረሱት፡፡
ሮይተርስ የድርጅቱን ዲፕሎማቶች ጠቅሶ እንደዘገበው ማዕቀቡን ለማንሳት በእንድሊዝ የቀረበውን ረቂቅ 15 የፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባላትያለልዩነት እንደሚቀበሉት ይጠበቃል፡፡
ኤርትራ የሶማሊያውን አልሸባብ ለሚባለው ቡድን እገዛ ታደርጋለች በሚል እንደአውሮፓዊያኑ አቆጣተር በ2009 አ.ም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ማዕቀቡን እንደጣለባት ይታወሳል፡፡
ምንጭ፦ ሮይተርስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኦነግ‼️
የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦነግ አመራሮች ያደረጉትን #ስምምነት መሰረት በማድረግ ወደ ሃገር ገብተው ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ 1 ሺ154
የኦነግ ጦር አባላት እንደ #የፍላጎታቸው ወደ ስራ ሊሰማሩ ነው።
የኦሮሚያ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ እንዳሳወቀው፤ ስልጠና ሲወስዱ ከነበሩት የኦነግ ጦር አባላት ውስጥ 700ዎቹ በራሳቸው ፍላጎት የኦሮሚያን ፖሊስ እንቀላቀላለን በማለታቸው ግንዛቤ እንዲያገኙ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ እንዲገቡ ተድርገዋል።
የአጭር ጊዜ ስልጠና በመውሰድም የኦሮሚያን ፖሊስ የሚቀላቀሉ ይሆናል። የቀሩትም እንደየፍላጎታቸው በግል ስራ፣ በመንግስት ስራ እና የኦነግ ፖለቲካ አባል በመሆን ወደ ስራ ይገባሉ ተብሏል።
ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦነግ አመራሮች ያደረጉትን #ስምምነት መሰረት በማድረግ ወደ ሃገር ገብተው ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ 1 ሺ154
የኦነግ ጦር አባላት እንደ #የፍላጎታቸው ወደ ስራ ሊሰማሩ ነው።
የኦሮሚያ ፀጥታና አስተዳደር ቢሮ እንዳሳወቀው፤ ስልጠና ሲወስዱ ከነበሩት የኦነግ ጦር አባላት ውስጥ 700ዎቹ በራሳቸው ፍላጎት የኦሮሚያን ፖሊስ እንቀላቀላለን በማለታቸው ግንዛቤ እንዲያገኙ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ እንዲገቡ ተድርገዋል።
የአጭር ጊዜ ስልጠና በመውሰድም የኦሮሚያን ፖሊስ የሚቀላቀሉ ይሆናል። የቀሩትም እንደየፍላጎታቸው በግል ስራ፣ በመንግስት ስራ እና የኦነግ ፖለቲካ አባል በመሆን ወደ ስራ ይገባሉ ተብሏል።
ምንጭ፦ አርትስ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እናት ነበረች ልጇን የገደለችው-ደሴ‼️
‹‹ፖሊስን #በማድከሜ እና ህዝቡን #በተሳሳተ መረጃ በማስቆጣቴም ተጸጽቻለሁ፡፡›› እናት
.
.
.
ባለፈው ሳምንት ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ ላይ አንድ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት መፈጸሙን ተዘግቦ ነበር፡፡ ድርጊቱም አንዲት የ7 ዓመት ህጻን #ከተደፈረች በኋላ እንደተገደለች የሚገልጽ ነበር፡፡
በዕለቱም ተጠርጣሪዉ በፖሊስ መያዛቸውን እና ድርጊቱም ነዋሪዎችን ማስቆጣቱን ነበር የተዘገበው፡፡
አሁን ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ ደግሞ ጥርጣሬው ወደ ሌላ አካል እንዳመራ ያስረዳል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራትም የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደረጃ አሰፋን አነጋግሯል፦ ኮማንደሩም መረጃው ትክክል መሆኑን ነው ያረጋገጡት፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው ጥቅምት 24/2011 ዓ.ም ነበር፡፡ ቦታውም ደሴ ከተማ ነው፡፡ በዕለቱም ወላጅ እናት ‹‹ልጄ ጠፋችብኝ›› ብለው ለፖሊስ መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ፖሊስም የምርመራ መጀመሪያውን እናት በሚሰጡት #ጥቆማ ላይ ያደርጋል፡፡የእናት ጥቆማ ደግሞ የቀድሞ የትዳር አጋራቸው ላይ ያርፋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ ከዚህ በፊት በህጻኗ ላይ ይዝቱ ነበር የሚል ነው፡፡
ፖሊስም ጥቆማውን ተቀብሎ ምርመራውን ይቀጥላል፡፡ ከዚህ ላይ አሳዛኝ ድርጊት ተፈጽሞ ይገኛል፡፡ህጻኗ ተገድላ እና ተጥላ ነበር ፖሊስ ያገኛት፡፡ ፖሊስም ለምርመራ አስከሬኑን ወደ ደሴ እና ጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል ይልካል፡፡
በዕለቱ ደግሞ ተጠርጣሪው በግምት ከምሽቱ 3፡00 አካባቢ በቁጥጥር ሰር ይውላል፡፡ ፖሊስም ምርመራውን ይቀጥላል፡፡ እየተገኙ የነበሩ ቁሳቁሶችና መረጃዎች ግን ፖሊስ ምርመራውን በእናት ላይም ማድረግ እንዳለበት ፍንጭ የሚሰጡ ነበሩ፡፡ በሂደትም ምርመራውን በእናት ላይ ይጀምራል፡፡ የፖሊስን ጥርጣሬ የሚያጎላ መረጃም ያገኛል፡፡አሁን የመጀመሪያው ጥርጣሬ ሚዛን ወደ ሌላ አቅጣጫ ይዞራል፤ እናት የሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ሌላ ገጽታ ነበረውና፡፡
እናት ይነገራሉ ‹‹ልጄን #የገደልኳት እኔ ነኝ፤ ድርጊቱን የፈጸምኩት ግን ልጄን ለመቅጣት እንጂ ለመግደል አስቤ አልነበረም፤ እስካሁን ፖሊስን በማድከሜ እና ህዝቡን በተሳሳተ መረጃ በማስቆጣቴም ተጸጽቻለሁ›› ነበር ያሉት
ይላል የፖሊስ መረጃ፡፡
እናት በሰጡት ቃል እንደተመላከተው ለልጃቸው ልብስ ከገዙላት በኋላ ‹‹ለምን ጫማ አልተገዛልኝም?›› በሚል ጭቅጭቅ ይፈጠራል፡፡ መግባባትም አልቻሉም ነበር፡፡ በዚህም እናት በልጃቸው ላይ አካላዊ ቅጣት ይፈጽማሉ፤ በድንገትም ህጻኗ እስከወዲያኛው ታሸልባለች፡፡
በድረጊቱ የተደናገጡት እናት የልጃቸውን አስክሬን ከአካባቢው ሰውረው ነበር ለፖሊስ ጥቆማውን ያቀረቡት፡፡ እናት ቃላቸውን ለደሴ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤትም ሰጥተዋል፡፡ ተጠርጣሪዋም ለጊዜው በደሴ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ፖሊስ ግን ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት ጠይቋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ከሆስፒታሉ የአስክሬን ምርመራ ውጤቱን እስከሚያገኝ እና መጀመሪያ ተጠርጥረው በተያዙት ሁለተኛ ተከሳሽ ላይም ተጨማሪ ምርመራ ማድረግ ስለፈለገ ነው ብለዋል ኮማንደር ደረጀ አሰፋ፡፡ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ግን ወደ ፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ (አስማማው በቀለ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
‹‹ፖሊስን #በማድከሜ እና ህዝቡን #በተሳሳተ መረጃ በማስቆጣቴም ተጸጽቻለሁ፡፡›› እናት
.
.
.
ባለፈው ሳምንት ደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ ላይ አንድ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት መፈጸሙን ተዘግቦ ነበር፡፡ ድርጊቱም አንዲት የ7 ዓመት ህጻን #ከተደፈረች በኋላ እንደተገደለች የሚገልጽ ነበር፡፡
በዕለቱም ተጠርጣሪዉ በፖሊስ መያዛቸውን እና ድርጊቱም ነዋሪዎችን ማስቆጣቱን ነበር የተዘገበው፡፡
አሁን ከፖሊስ ያገኘነው መረጃ ደግሞ ጥርጣሬው ወደ ሌላ አካል እንዳመራ ያስረዳል፡፡ ጉዳዩን ለማጣራትም የአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደረጃ አሰፋን አነጋግሯል፦ ኮማንደሩም መረጃው ትክክል መሆኑን ነው ያረጋገጡት፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመው ጥቅምት 24/2011 ዓ.ም ነበር፡፡ ቦታውም ደሴ ከተማ ነው፡፡ በዕለቱም ወላጅ እናት ‹‹ልጄ ጠፋችብኝ›› ብለው ለፖሊስ መረጃ ይሰጣሉ፡፡ ፖሊስም የምርመራ መጀመሪያውን እናት በሚሰጡት #ጥቆማ ላይ ያደርጋል፡፡የእናት ጥቆማ ደግሞ የቀድሞ የትዳር አጋራቸው ላይ ያርፋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ ከዚህ በፊት በህጻኗ ላይ ይዝቱ ነበር የሚል ነው፡፡
ፖሊስም ጥቆማውን ተቀብሎ ምርመራውን ይቀጥላል፡፡ ከዚህ ላይ አሳዛኝ ድርጊት ተፈጽሞ ይገኛል፡፡ህጻኗ ተገድላ እና ተጥላ ነበር ፖሊስ ያገኛት፡፡ ፖሊስም ለምርመራ አስከሬኑን ወደ ደሴ እና ጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል ይልካል፡፡
በዕለቱ ደግሞ ተጠርጣሪው በግምት ከምሽቱ 3፡00 አካባቢ በቁጥጥር ሰር ይውላል፡፡ ፖሊስም ምርመራውን ይቀጥላል፡፡ እየተገኙ የነበሩ ቁሳቁሶችና መረጃዎች ግን ፖሊስ ምርመራውን በእናት ላይም ማድረግ እንዳለበት ፍንጭ የሚሰጡ ነበሩ፡፡ በሂደትም ምርመራውን በእናት ላይ ይጀምራል፡፡ የፖሊስን ጥርጣሬ የሚያጎላ መረጃም ያገኛል፡፡አሁን የመጀመሪያው ጥርጣሬ ሚዛን ወደ ሌላ አቅጣጫ ይዞራል፤ እናት የሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ሌላ ገጽታ ነበረውና፡፡
እናት ይነገራሉ ‹‹ልጄን #የገደልኳት እኔ ነኝ፤ ድርጊቱን የፈጸምኩት ግን ልጄን ለመቅጣት እንጂ ለመግደል አስቤ አልነበረም፤ እስካሁን ፖሊስን በማድከሜ እና ህዝቡን በተሳሳተ መረጃ በማስቆጣቴም ተጸጽቻለሁ›› ነበር ያሉት
ይላል የፖሊስ መረጃ፡፡
እናት በሰጡት ቃል እንደተመላከተው ለልጃቸው ልብስ ከገዙላት በኋላ ‹‹ለምን ጫማ አልተገዛልኝም?›› በሚል ጭቅጭቅ ይፈጠራል፡፡ መግባባትም አልቻሉም ነበር፡፡ በዚህም እናት በልጃቸው ላይ አካላዊ ቅጣት ይፈጽማሉ፤ በድንገትም ህጻኗ እስከወዲያኛው ታሸልባለች፡፡
በድረጊቱ የተደናገጡት እናት የልጃቸውን አስክሬን ከአካባቢው ሰውረው ነበር ለፖሊስ ጥቆማውን ያቀረቡት፡፡ እናት ቃላቸውን ለደሴ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤትም ሰጥተዋል፡፡ ተጠርጣሪዋም ለጊዜው በደሴ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ፖሊስ ግን ለተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናት ጠይቋል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ከሆስፒታሉ የአስክሬን ምርመራ ውጤቱን እስከሚያገኝ እና መጀመሪያ ተጠርጥረው በተያዙት ሁለተኛ ተከሳሽ ላይም ተጨማሪ ምርመራ ማድረግ ስለፈለገ ነው ብለዋል ኮማንደር ደረጀ አሰፋ፡፡ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ግን ወደ ፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ (አስማማው በቀለ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update አምነስቲ ኢንተርናሽናል #የሳን_ሱኪን ሽልማት መንጠቁ ተሰማ። የማይናማሯ መሪ አውንግ ሳንሱኪ በሮሂንጊያ ሙስሊሞች ላይ የዘር ጭፍጨፋ ሲፈፀም ዝምታን መምረጣቸው ነው በፈረንጆቹ 2009 የሞራል አምባሳደር ተብለው የተሰጣቸውን ሽልማት ያስነጠቃቸው፡፡
©Arts TV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
©Arts TV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update መቀለ⬇️
የመቀለ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ኢንጅነር #አርአያ_ግርማይ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሸመ።
ተሿሚው ቀደም ሲል የከተማው አስተዳደር ከንቲባ የነበሩት ወደ ሌላ የስራ ኃላፊትን በመሄዳቸው እሳቸው ተክተው እንደሚሰሩ ተገልጿል፡፡
ምክር ቤቱ ትናንት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ኢንጂነር አርአያ ግርማይ የከንቲባ ስራና ኃላፊነት እንዲሰሩ በሙሉ ድምጽ መርጧቸዋል፡፡
ኢንጅነሩ ካላቸው የትምህርት ዝግጅት ሌላ ለረጅም ዓመታት የሱር ኮንስትራክሽን ኃለፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የፕሮጀክት አስኪያጅና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆኖው አገልግለዋል፡፡
ኢንጅነር አርአያ ግርማይ በበኩላቸው “በእኔ ላይ እምነት የጣለው የከተማው ምክር ቤትና ህዝብ በሙሉ ልብ ሌትና ቀን ለማገልገል ዝግጁ ነኝ” ብለዋል፡፡
አንድ ሰው ብቻውን የከተማውን ልማት መቀየር እንደማይቻል ያመለከቱት ኢንጅነሩ በየደረጃው የሚገኝ የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የከተማው አስተዳደር ለዓመታት መፍትሄ ሳያገኝ የቆየውን የመብራትና ውሃ ችግር ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የሲቪል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሃይለየሱስ ግርማይ በሰጠው አስተያየት ተሿሚውን በቅርበት እንደሚያውቃቸው ገልጾ ” በአመራር፣ በሙያ ብቃት ያላቸው በመሆኑ መሾማቸው ለከተማው እድገት መፋጠን ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል” ብለዋል፡፡
የከተማው ነዋሪ አቶ ፍትዊ ባህታ በበኩላቸው ኢንጅነር አርአያ ግርማይ መመረጥ በከተማው ምላሽ ያላገኙ የመልካም አስተዳደርና የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመቀለ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ኢንጅነር #አርአያ_ግርማይ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሸመ።
ተሿሚው ቀደም ሲል የከተማው አስተዳደር ከንቲባ የነበሩት ወደ ሌላ የስራ ኃላፊትን በመሄዳቸው እሳቸው ተክተው እንደሚሰሩ ተገልጿል፡፡
ምክር ቤቱ ትናንት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ ኢንጂነር አርአያ ግርማይ የከንቲባ ስራና ኃላፊነት እንዲሰሩ በሙሉ ድምጽ መርጧቸዋል፡፡
ኢንጅነሩ ካላቸው የትምህርት ዝግጅት ሌላ ለረጅም ዓመታት የሱር ኮንስትራክሽን ኃለፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የፕሮጀክት አስኪያጅና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆኖው አገልግለዋል፡፡
ኢንጅነር አርአያ ግርማይ በበኩላቸው “በእኔ ላይ እምነት የጣለው የከተማው ምክር ቤትና ህዝብ በሙሉ ልብ ሌትና ቀን ለማገልገል ዝግጁ ነኝ” ብለዋል፡፡
አንድ ሰው ብቻውን የከተማውን ልማት መቀየር እንደማይቻል ያመለከቱት ኢንጅነሩ በየደረጃው የሚገኝ የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የከተማው አስተዳደር ለዓመታት መፍትሄ ሳያገኝ የቆየውን የመብራትና ውሃ ችግር ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡
በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የሲቪል ኢንጅነሪንግ ተማሪ ሃይለየሱስ ግርማይ በሰጠው አስተያየት ተሿሚውን በቅርበት እንደሚያውቃቸው ገልጾ ” በአመራር፣ በሙያ ብቃት ያላቸው በመሆኑ መሾማቸው ለከተማው እድገት መፋጠን ትልቅ ሚና ይኖራቸዋል” ብለዋል፡፡
የከተማው ነዋሪ አቶ ፍትዊ ባህታ በበኩላቸው ኢንጅነር አርአያ ግርማይ መመረጥ በከተማው ምላሽ ያላገኙ የመልካም አስተዳደርና የልማት ጥያቄዎች ምላሽ ያገኛሉ ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አምባሳደር ሱሌማን🔝ከ5 አመት በፊት በቅቱ ለነበሩት የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም የጻፉት ደብዳቤ። አምባሳደር ሱሌማን በወቅቱ በጅቡቲ የኢትዮዽያ አምባሳደር ነበሩ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የምስራች!!
ውድ የ“TIKVAH-ETHIOPIA” ቤተሰቦች እንደሚታወቀው ቻናላችን ከአንድ አመት በላይ በቴሌግራም መረጃዎች፣ ዜናዎች፣ እንዲሁም መልዕክቶችን ሲያቀርብላችሁ ቆይቷል።
አሁን ደግሞ ተደራሽነቱን በተሻለ ሁኔታ ለማሳደግ ከ“Golden Gear" ጋር በመተባበር የሞባይል መተግበሪያ(Application) ለእናንተ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ ነው።
በዚህ Application የሃገር ውስጥ እና የሃገር ውጭ ዜናዎች፣ የቢዝነስ ዘገባዎች፣ የስፖርትና የመዝናኛ ወሬዎች በቀላሉ ማግኘት ትችላላችሁ።
🔹መተግበሪያው(APPLICATION) በቀናት ውስጥ ይለቀቃል!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ውድ የ“TIKVAH-ETHIOPIA” ቤተሰቦች እንደሚታወቀው ቻናላችን ከአንድ አመት በላይ በቴሌግራም መረጃዎች፣ ዜናዎች፣ እንዲሁም መልዕክቶችን ሲያቀርብላችሁ ቆይቷል።
አሁን ደግሞ ተደራሽነቱን በተሻለ ሁኔታ ለማሳደግ ከ“Golden Gear" ጋር በመተባበር የሞባይል መተግበሪያ(Application) ለእናንተ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ ነው።
በዚህ Application የሃገር ውስጥ እና የሃገር ውጭ ዜናዎች፣ የቢዝነስ ዘገባዎች፣ የስፖርትና የመዝናኛ ወሬዎች በቀላሉ ማግኘት ትችላላችሁ።
🔹መተግበሪያው(APPLICATION) በቀናት ውስጥ ይለቀቃል!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሜቴክ እና ኢንጂነር ስመኘው‼️
ኢንጂነር #ስመኘው_በቀለ የሕዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅነትን ሙሉ በሙሉ ጠቅለው እንዲይዙ የተደረገው የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንን (ሜቴክ) ጥቅም አይጋፉም በሚል ተስፋ ነበር።
ኢንጂነር ስመኘው ከህልፈተ ህይወታቸው ጥቂት ቀናት አስቀድሞ ስለሚመሩት ፕሮጀክት ዝርዝር ሪፖርት አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ ይታዘዛሉ። በተመሳሳይ ጊዜ የመንግስት የልዑካን ቡድን ወደ ሕዳሴው ግድብ መገናኛ ብዙሀንን ይዞ በመሄድ እንደሚጎበኝ መርሀ ግብር ይወጣል። ኢንጅነር ስመኘው ለመንግስት ለማቅረብ ለተዘጋጁት ሪፖርት ከእናት መስሪያ ቤታቸው የኤሌክትሪክ ሀይል ኮርፖሬሽንና ከተቋራጩ ሜቴክ የፋይናንስ መረጃዎችን ለማስታረቅ ወደላይ ወደታች እያሉ በነበረበት ወቅት ከሜቴክ ቀና ምላሽ አላገኙም። “አለቆች የሉም” ፣ “ለማዘጋጀት ጊዜ ያስፈልገናል” የሚሉ ምክንያቶች ተነግሯው ሲጠባበቁ የሪፖርት ማቅረቢያው ጊዜ ደረሰ።
ሌላው ተቋራጭ ሳሊኒ የራሱን ሪፖርት አስቀድሞ አስረክቦ ነበር። ኢንጂነር ስመኘው በእጃቸው ያለውንና የሚያውቁት የፋይናንስ መረጃ ብቻ አሰናዱ። ሪፖርቱን ለማቅረብ አንድ ቀን ሲቀራቸው በጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ በኩል በርካታ መረጃ መሰባሰቡንና የህዳሴው ግድብ ስራ ከተቋረጠ ከዓመት በላይ ማስቆጠሩ መሰማቱን ደረሱበት። በሜቴክ ላይም የሙስና ምርመራ ይደረጋል ኢንጂነር ስመኘውም ከሀላፊነታቸው እንደሚነሱ ውሳኔ ላይ መደረሱን ስምተዋል። ይልቁንም ለምርመራ የሚያስፈልጉ ቁልፍ መረጃዎችን እንዲሰጡ እንደሚጠበቁ ተነግሯቸዋል። የሜቴክ አመራሮች ኢንጂነር ስመኘው መረጃ እንዳያገኙ ከመከላከል ባለፈ መንግስት ሊያደርገው ባሰበው ምርመራ እንዳይተባበሩ ጫና ለመፍጠርም ሙከራ ሲያደርጉ ነበር። ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ሀምሌ 19 , 2010 አ.ም መስቀል አደባባይ መኪናቸው ውስጥ ህይወታቸው አልፎ ተገኝተው ነበር። አጣብቂኝ ውስጥ የወደቁት ስመኘው ራሳቸውን ማጥፋታቸውን ፖሊስ አደረኩት ባለው ምርመራ ገልጿል።
ሜቴክ ለዓመታት ለፈፀመው ምዝበራ ኢንጂነር ስመኘውን በቀላሉ ማግባባትና ዝም ማሰኘት ችሎ ነበር። ኢንጂነር ስመኘው በተደጋጋሚ ሜቴክ ስራውን መስራት እንደተሳነው ለመስሪያቤታቸው ሪፖርት አድርገዋል። መረጃው ከጥቂት ሀላፊዎች ውጪ እንዳይወጣ ይጠነቀቁ ነበር። የሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት መጀመሪያ ላይ ሁለት ስራ አስኪያጆች ነበሩት። የእሳቸውን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ የግድቡ ስራ አስኪያጅነት በጊዜያዊነት የኢንጂነር ስመኘው ምክትል በነበሩት ኤፍሬም ወልደ ኪዳን ሲመራ ከቆየ በሁዋላ በቅርቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሆራን ማግኘቱ ይታወቃል።
የህዳሴው ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት አቶ ክፍሌ ሆሮ ሜቴክ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራን መስራት የለበትም በማለታቸው ከግድቡ ሀላፊነታቸው ተባረው የነበሩ ናቸው።
አቶ ክፍሌ ሆራ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ሂደት አዲስ አይደሉም ይልቅስ የግድቡን ግንባታ በበላይነት ሲመሩም የነበሩም ናቸው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር በ2003 አ.ም ሲጀመር ኢንጂነር ስመኘው ብቻ አልነበሩም የኘሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ እንዲያውም የግድቡ ፕሮጀክት ሁለት ስራ አስኪያጆች ነበረት።
ኢንጂነር ስመኘው የግድቡን የሲቪል ስራ በስራ አስኪያጅነት አቶ #ክፍሌ_ሆሮ ደግሞ የግድቡን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን በስራ አስኪያጅነት እንዲከታተሉ ተመድበዋል።
አቶ ክፍሌ በስራ አስኪያጅነት ከአንድ አመት በላይ ሰርተዋል። ሆኖም ትንሽ ቆይቶ የህዳሴውን ግድብ የኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሀይድሮ ሜካኒካል ስራዎችን ማን ይስራው የሚለው ጉዳይ ትልቅ አጨቃጫቂ ጉዳይ ሆኖ ብቅ ይላል። ያኔ የሲቪል ስራውን ያከናውን የጀመረው ሳሊኒ ኢምፕሪጂሎ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራው እንዲሰጠው በእጅጉ ቢፈልግም በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ትእዛዝ የተቋቋመው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንም : ሜቴክ : ስራውን ይውሰደው የሚል ሀሳብ ይቀርባል። ህዳሴው ግድብ ሲጀመር ግን ሜቴክ ገና ከተመሰረተ አንድ አመቱ ነው።
የግድቡ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ታድያ ለሜቴክ ኮንትራቱ መሰጠት የለበትም ሲሉ በጽኑ ተቃውመው እንደነበር ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያሳያል። የእሳቸውና ሌሎች ለፕሮጀክቱ የቅርብ የነበሩ የስራ ሀላፊዎችም ልምድና ብቃት ለሌለው ሜቴክ ውሉ ሊሰጠው አይገባም የሚል አቋም ይዘዋል። በአቶ ክፍሌ ሆሮ የከረረ ተቃውሞ ያልተስማሙት አለቆቻቸው የሜቴክን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል ከሀላፊነታቸው እንዲነሱ አድርገዋቸዋል።
ኢንጂነር ስመኘውም ሁለቱንም ስራ ደርበው የህዳሴውን ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅነት ይዘው ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ቀጥለዋል። የሳቸው ህይወት ሲያልፍ ታዲያ አቶ ክፍሌ ሆሮ ከነበሩበት የግል ስራ ተጠርተው የግድቡን ስራ በስራ አስኪያጅነት እንዲመሩ ተደርገዋል። ሜቴክ በአዲስ አለቆቹ እየተመራ ከግድቡ ስራ እየተቀነሰ ሲመጣ አቶ ክፍሌ ሆሮ ደግሞ ወደ ግድቡ ተመልሰዋል።
ምንጭ፦ ዋዜማ ሬዲዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢንጂነር #ስመኘው_በቀለ የሕዳሴ ግድብ ስራ አስኪያጅነትን ሙሉ በሙሉ ጠቅለው እንዲይዙ የተደረገው የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንን (ሜቴክ) ጥቅም አይጋፉም በሚል ተስፋ ነበር።
ኢንጂነር ስመኘው ከህልፈተ ህይወታቸው ጥቂት ቀናት አስቀድሞ ስለሚመሩት ፕሮጀክት ዝርዝር ሪፖርት አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ ይታዘዛሉ። በተመሳሳይ ጊዜ የመንግስት የልዑካን ቡድን ወደ ሕዳሴው ግድብ መገናኛ ብዙሀንን ይዞ በመሄድ እንደሚጎበኝ መርሀ ግብር ይወጣል። ኢንጅነር ስመኘው ለመንግስት ለማቅረብ ለተዘጋጁት ሪፖርት ከእናት መስሪያ ቤታቸው የኤሌክትሪክ ሀይል ኮርፖሬሽንና ከተቋራጩ ሜቴክ የፋይናንስ መረጃዎችን ለማስታረቅ ወደላይ ወደታች እያሉ በነበረበት ወቅት ከሜቴክ ቀና ምላሽ አላገኙም። “አለቆች የሉም” ፣ “ለማዘጋጀት ጊዜ ያስፈልገናል” የሚሉ ምክንያቶች ተነግሯው ሲጠባበቁ የሪፖርት ማቅረቢያው ጊዜ ደረሰ።
ሌላው ተቋራጭ ሳሊኒ የራሱን ሪፖርት አስቀድሞ አስረክቦ ነበር። ኢንጂነር ስመኘው በእጃቸው ያለውንና የሚያውቁት የፋይናንስ መረጃ ብቻ አሰናዱ። ሪፖርቱን ለማቅረብ አንድ ቀን ሲቀራቸው በጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ በኩል በርካታ መረጃ መሰባሰቡንና የህዳሴው ግድብ ስራ ከተቋረጠ ከዓመት በላይ ማስቆጠሩ መሰማቱን ደረሱበት። በሜቴክ ላይም የሙስና ምርመራ ይደረጋል ኢንጂነር ስመኘውም ከሀላፊነታቸው እንደሚነሱ ውሳኔ ላይ መደረሱን ስምተዋል። ይልቁንም ለምርመራ የሚያስፈልጉ ቁልፍ መረጃዎችን እንዲሰጡ እንደሚጠበቁ ተነግሯቸዋል። የሜቴክ አመራሮች ኢንጂነር ስመኘው መረጃ እንዳያገኙ ከመከላከል ባለፈ መንግስት ሊያደርገው ባሰበው ምርመራ እንዳይተባበሩ ጫና ለመፍጠርም ሙከራ ሲያደርጉ ነበር። ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ሀምሌ 19 , 2010 አ.ም መስቀል አደባባይ መኪናቸው ውስጥ ህይወታቸው አልፎ ተገኝተው ነበር። አጣብቂኝ ውስጥ የወደቁት ስመኘው ራሳቸውን ማጥፋታቸውን ፖሊስ አደረኩት ባለው ምርመራ ገልጿል።
ሜቴክ ለዓመታት ለፈፀመው ምዝበራ ኢንጂነር ስመኘውን በቀላሉ ማግባባትና ዝም ማሰኘት ችሎ ነበር። ኢንጂነር ስመኘው በተደጋጋሚ ሜቴክ ስራውን መስራት እንደተሳነው ለመስሪያቤታቸው ሪፖርት አድርገዋል። መረጃው ከጥቂት ሀላፊዎች ውጪ እንዳይወጣ ይጠነቀቁ ነበር። የሕዳሴው ግድብ ፕሮጀክት መጀመሪያ ላይ ሁለት ስራ አስኪያጆች ነበሩት። የእሳቸውን ህልፈተ ህይወት ተከትሎ የግድቡ ስራ አስኪያጅነት በጊዜያዊነት የኢንጂነር ስመኘው ምክትል በነበሩት ኤፍሬም ወልደ ኪዳን ሲመራ ከቆየ በሁዋላ በቅርቡ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሆራን ማግኘቱ ይታወቃል።
የህዳሴው ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት አቶ ክፍሌ ሆሮ ሜቴክ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራን መስራት የለበትም በማለታቸው ከግድቡ ሀላፊነታቸው ተባረው የነበሩ ናቸው።
አቶ ክፍሌ ሆራ ለህዳሴው ግድብ ግንባታ ሂደት አዲስ አይደሉም ይልቅስ የግድቡን ግንባታ በበላይነት ሲመሩም የነበሩም ናቸው። የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር በ2003 አ.ም ሲጀመር ኢንጂነር ስመኘው ብቻ አልነበሩም የኘሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ እንዲያውም የግድቡ ፕሮጀክት ሁለት ስራ አስኪያጆች ነበረት።
ኢንጂነር ስመኘው የግድቡን የሲቪል ስራ በስራ አስኪያጅነት አቶ #ክፍሌ_ሆሮ ደግሞ የግድቡን የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችን በስራ አስኪያጅነት እንዲከታተሉ ተመድበዋል።
አቶ ክፍሌ በስራ አስኪያጅነት ከአንድ አመት በላይ ሰርተዋል። ሆኖም ትንሽ ቆይቶ የህዳሴውን ግድብ የኤሌክትሮ ሜካኒካልና ሀይድሮ ሜካኒካል ስራዎችን ማን ይስራው የሚለው ጉዳይ ትልቅ አጨቃጫቂ ጉዳይ ሆኖ ብቅ ይላል። ያኔ የሲቪል ስራውን ያከናውን የጀመረው ሳሊኒ ኢምፕሪጂሎ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራው እንዲሰጠው በእጅጉ ቢፈልግም በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ትእዛዝ የተቋቋመው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽንም : ሜቴክ : ስራውን ይውሰደው የሚል ሀሳብ ይቀርባል። ህዳሴው ግድብ ሲጀመር ግን ሜቴክ ገና ከተመሰረተ አንድ አመቱ ነው።
የግድቡ ኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ታድያ ለሜቴክ ኮንትራቱ መሰጠት የለበትም ሲሉ በጽኑ ተቃውመው እንደነበር ዋዜማ ያገኘችው መረጃ ያሳያል። የእሳቸውና ሌሎች ለፕሮጀክቱ የቅርብ የነበሩ የስራ ሀላፊዎችም ልምድና ብቃት ለሌለው ሜቴክ ውሉ ሊሰጠው አይገባም የሚል አቋም ይዘዋል። በአቶ ክፍሌ ሆሮ የከረረ ተቃውሞ ያልተስማሙት አለቆቻቸው የሜቴክን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲባል ከሀላፊነታቸው እንዲነሱ አድርገዋቸዋል።
ኢንጂነር ስመኘውም ሁለቱንም ስራ ደርበው የህዳሴውን ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅነት ይዘው ህይወታቸው እስካለፈበት ጊዜ ቀጥለዋል። የሳቸው ህይወት ሲያልፍ ታዲያ አቶ ክፍሌ ሆሮ ከነበሩበት የግል ስራ ተጠርተው የግድቡን ስራ በስራ አስኪያጅነት እንዲመሩ ተደርገዋል። ሜቴክ በአዲስ አለቆቹ እየተመራ ከግድቡ ስራ እየተቀነሰ ሲመጣ አቶ ክፍሌ ሆሮ ደግሞ ወደ ግድቡ ተመልሰዋል።
ምንጭ፦ ዋዜማ ሬዲዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia