#update በ3 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የርብ መስኖ ግድብ ኘሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አህመድ ዛሬ ተመርቋል፡፡ ኘሮጀክቱ 28 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ላሊበላ⬆️
በአማራ ክላዊ መንግስት በሰሜና ደቡብ ጎንደር ዞኖች ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገፕው: በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ የተመራውና ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ ክቡር የአማራ ብ/ክ/መ ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንድአርጋቸው እና
ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች የሚገኙበት ልዑክ ከስዓት በኃላ ላይ ወደ ላሊ-በላ በማቅናት የላሊ-በላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት ጥበቃና ጥገና የሚገኝበትን ሁኔታ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል፣
በቅድሚያም ቤተ-መድሃኒዓለም ሲጎበኝ በድንገት ለተሰበው የላሊ-በላ ህዝብ ንግግር ያደረጉት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ: "ላሊ-በላን የሚያክል ድንቅ የዓለምና የአፍሪካ ቅርስ: ለእኛ ደግሞ ከዚያም በላይ መኩሪያችንና መመኪያችንን ስለሆነ ደግመን መገንባት ባንችልም እንኳ መጠበቅ ግን ግዴታችን ነው" ብለዋል።
ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አርጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአማራ ክላዊ መንግስት በሰሜና ደቡብ ጎንደር ዞኖች ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገፕው: በክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #አብይ_አህመድ የተመራውና ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ ክቡር የአማራ ብ/ክ/መ ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንድአርጋቸው እና
ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች የሚገኙበት ልዑክ ከስዓት በኃላ ላይ ወደ ላሊ-በላ በማቅናት የላሊ-በላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት ጥበቃና ጥገና የሚገኝበትን ሁኔታ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል፣
በቅድሚያም ቤተ-መድሃኒዓለም ሲጎበኝ በድንገት ለተሰበው የላሊ-በላ ህዝብ ንግግር ያደረጉት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ: "ላሊ-በላን የሚያክል ድንቅ የዓለምና የአፍሪካ ቅርስ: ለእኛ ደግሞ ከዚያም በላይ መኩሪያችንና መመኪያችንን ስለሆነ ደግመን መገንባት ባንችልም እንኳ መጠበቅ ግን ግዴታችን ነው" ብለዋል።
ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አርጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ⬆️
"ዛሬ ማህበረ ቅዱሣን የአቡነ ጎርጎርዮስ ሥልጠና ማዕከል ለ14ተኛ ዙር በበጋው እና በክረምቱ መርኃግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎች በቅድስት ሥላሤ አዳራሽ እያስመረቀ ይገኛል። ተማሪዎቹ የተማሩት
👉በገና
👉ማሲንቆ
👉ከበሮ
👉ልሳነ ግዕዝ ነው።
በመርኃግብሩ ላይ ወደ 1000 የሚጠጋ ሰው ተግኝቷል።"
©B ከሥላሤ ካቴድራል አ·አ(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ዛሬ ማህበረ ቅዱሣን የአቡነ ጎርጎርዮስ ሥልጠና ማዕከል ለ14ተኛ ዙር በበጋው እና በክረምቱ መርኃግብር ያስተማራቸውን ተማሪዎች በቅድስት ሥላሤ አዳራሽ እያስመረቀ ይገኛል። ተማሪዎቹ የተማሩት
👉በገና
👉ማሲንቆ
👉ከበሮ
👉ልሳነ ግዕዝ ነው።
በመርኃግብሩ ላይ ወደ 1000 የሚጠጋ ሰው ተግኝቷል።"
©B ከሥላሤ ካቴድራል አ·አ(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከጀርባ ያለው አካል⁉️
አሁን አሁን በተደጋጋሚ የምንሰማው ለሚደርሱት ችግሮችና ለሚታዩት #ግጭቶች ማንነቱ #የማይታወቅ፣ በጀርባ #ተደብቆ የሚገፋ ሀይል
መኖሩ ነው፡፡ በግጭቶች ሰው ሲሞት፣ ፀጥታ ሲታወክ፣ አደጋ ሲደርስ፣ ከኋላ ሆነው አቀነባብረዋል የሚባሉ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች “አሉ” ይባላል እንጂ ማንነታቸው ይፋ ሆኖ ችግር ፈጣሪው አካል የሚታወቀው መቼ ነው ? ሁልጊዜ የማይታወቅ ተጠያቂ ማበጀት እያደር መተማመንን አያጎድልም ወይ ? በዚህ ዙሪያ የሸገር 102.1 ጋዜጠኛ ከባለሙያ ጋር ያደረገውን ቆይታ ከላይ አድምጡት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሁን አሁን በተደጋጋሚ የምንሰማው ለሚደርሱት ችግሮችና ለሚታዩት #ግጭቶች ማንነቱ #የማይታወቅ፣ በጀርባ #ተደብቆ የሚገፋ ሀይል
መኖሩ ነው፡፡ በግጭቶች ሰው ሲሞት፣ ፀጥታ ሲታወክ፣ አደጋ ሲደርስ፣ ከኋላ ሆነው አቀነባብረዋል የሚባሉ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች “አሉ” ይባላል እንጂ ማንነታቸው ይፋ ሆኖ ችግር ፈጣሪው አካል የሚታወቀው መቼ ነው ? ሁልጊዜ የማይታወቅ ተጠያቂ ማበጀት እያደር መተማመንን አያጎድልም ወይ ? በዚህ ዙሪያ የሸገር 102.1 ጋዜጠኛ ከባለሙያ ጋር ያደረገውን ቆይታ ከላይ አድምጡት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ተገኘ‼️
አደጋ የደረሰበት የነዳጅ ቦቲ ህገ ወጥ መሳሪያ #ተገኘበት። ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ ሲጓዝ የነበረው የነዳጅ ቦቲ በገንዳውሀ ከተማ አስተዳደር በተለምዶ ኢንዱስትሪ መንደር በሚባል አካባቢ በትናትናው ዕለት ጥቅምት 17/2011 ዓ.ም ፍየል አድናለሁ በሚል ምክኒያት #በመገልበጡ አደጋ ደርሷል። በዛሬው ዕለት ጥቅምት 18/2011 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩና የወረዳው የጸጥታ ሀይሎች ባደረጉት ፍተሻ መሰረት 97 ክላሽን ኮፍ 1291 የቱርክ ሽጉጥ እና 3 ብሬን መገኘቱን ከስፍራው ለመዘገብ ተችሏል።
ምንጭ፦ Metema wereda communication affairs office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አደጋ የደረሰበት የነዳጅ ቦቲ ህገ ወጥ መሳሪያ #ተገኘበት። ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ ሲጓዝ የነበረው የነዳጅ ቦቲ በገንዳውሀ ከተማ አስተዳደር በተለምዶ ኢንዱስትሪ መንደር በሚባል አካባቢ በትናትናው ዕለት ጥቅምት 17/2011 ዓ.ም ፍየል አድናለሁ በሚል ምክኒያት #በመገልበጡ አደጋ ደርሷል። በዛሬው ዕለት ጥቅምት 18/2011 ዓ.ም የከተማ አስተዳደሩና የወረዳው የጸጥታ ሀይሎች ባደረጉት ፍተሻ መሰረት 97 ክላሽን ኮፍ 1291 የቱርክ ሽጉጥ እና 3 ብሬን መገኘቱን ከስፍራው ለመዘገብ ተችሏል።
ምንጭ፦ Metema wereda communication affairs office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport ዛሬ በተካሄደው አየርላንድ #ደብሊን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንድም በሴትም ማሸነፍ ችለዋል።
በሴቶች የደብሊኑ ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ መስራ ዱቢሶ 2:33:48 ፈጣኑን ሰዓት አስመዝግባ አሸንፋለች።
በወንዶች ፆታ በአውሮፖውያኑ 2015 ና በ2017 ደብሊን ማራቶንን 3ኛ ሆኖ ያጠናቀቀው አሰፋ በቀለ የዛሬውን ውድድር 2:13:23 በመግባት በቀዳሚነት አጠናቋል።
ምንጭ፦ ፋስት ረኒንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሴቶች የደብሊኑ ማራቶን ኢትዮጵያዊቷ መስራ ዱቢሶ 2:33:48 ፈጣኑን ሰዓት አስመዝግባ አሸንፋለች።
በወንዶች ፆታ በአውሮፖውያኑ 2015 ና በ2017 ደብሊን ማራቶንን 3ኛ ሆኖ ያጠናቀቀው አሰፋ በቀለ የዛሬውን ውድድር 2:13:23 በመግባት በቀዳሚነት አጠናቋል።
ምንጭ፦ ፋስት ረኒንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️
በዲላ ከተማ ልዩ ቦታው ሞላ ጎልጃ ወረድ ብሎ የድሮው ቱቱፈላ ፔንሲዮን አካባቢ የተሰጣ ልብስ በማስገባት ላይ በነበሩ የቤተሰብ አባላት ላይ በደረሰ የኤሌክትሪክ አደጋ፣ አንድ እናት ከሶስት ልጆቿ ጋር #መሞቷ ተሰምቷል። አምስተኛ የቤተሰብ አባል በደረሰበት ከከፍተኛ ቃጠሎ በዲላ ሆስፒታል የህክምና #እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል።
🔹ከሟቾቹ አንዷ በነገው ዕለት ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ልታቀና የተዘጋጀች ነበረች።
©ማስተዋል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዲላ ከተማ ልዩ ቦታው ሞላ ጎልጃ ወረድ ብሎ የድሮው ቱቱፈላ ፔንሲዮን አካባቢ የተሰጣ ልብስ በማስገባት ላይ በነበሩ የቤተሰብ አባላት ላይ በደረሰ የኤሌክትሪክ አደጋ፣ አንድ እናት ከሶስት ልጆቿ ጋር #መሞቷ ተሰምቷል። አምስተኛ የቤተሰብ አባል በደረሰበት ከከፍተኛ ቃጠሎ በዲላ ሆስፒታል የህክምና #እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል።
🔹ከሟቾቹ አንዷ በነገው ዕለት ወደ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ልታቀና የተዘጋጀች ነበረች።
©ማስተዋል
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UpdateSport ባርሴሎና ሪያል ማድሪድን 5 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸነፈ። በጫወታው ሱዋሬዝ 3 ግቦችን አስቆጥሯል። ቪዳል እና ኩቲኒሆ የቀሩትን የባርሴሎና ግቦች ሲያስቆጥሩ ለሪያል ማድሪድ ብቸኛውን ግብ ማርሴሎ አስቆጥሯል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ታላቁ ቤተ መንግስት⬆️
በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤትና #መኖሪያ የሚገኝበትን በአራት ኪሎ አካባቢ የሚገኘው የአፄ ምኒልክ ቤተ መንግሥት በዘመናዊ መንገድ በማደስና በማልማት ወደ #ሙዚየምነት ለመቀየር፣ የፈረንሣይ መንግሥት #ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱ ታወቀ።
የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት ታላቁን የምኒልክ ቤተ መንግሥት በማደስና ተጨማሪ ልማቶችን በማከናወን፣ ለሕዝብና ለጎብኝዎች ክፍት የሚሆን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ዕቅድ ተይዟል፡፡ ይህንንም በፍጥነት በተግባር ለመቀየር የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርትሚኒስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶታል።
ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው በበላይነት እየተከታተሉት እንደሚገኝ ታውቋል። በዚህም መሠረት የተለያዩ አገሮች ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዳሳዩ፣ በዋናነት ግን የፈረንሣይ መንግሥት አስፈላጊውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱን ምንጮች ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ሳምንት የሚያደርጉትን የአውሮፓ ጉብኝት በፈረንሣይ የሚጀምሩ ሲሆን፣ በፈረንሣይ በሚኖራቸው የአንድ ቀን ቆይታ ቤተ መንግሥቱን ወደ ቱሪዝም መዳረሻ ለመቀየር ለተቀረፀው ፕሮጀክት የሚፈለገውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ የተመለከተ ስምምነት ተፈራርመው ይመለሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግንቦት ወር 2010 ዓ.ም. በውጤታማ ሥራ አፈጻጸም ላይ በወቅቱ ለነበሩ የካቢኔ ሚኒስትሮች ባደረጉት ገለጻ፣ የአፄ ምኒልክ ቤተ መንግሥትን የቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ እንደሚገባ መግለጻቸው ይታወሳል።
ቤተ መንግሥቱ ኢትዮጵያ ምን እንደምትመስልና ጥንታዊ ገናናነቷ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መሆን በወቅቱ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ያለፋት የኢትዮጵያ መንግሥታት እያንዳንዳቸው በቅጥር ግቢው ትተው ያለፋትን አሻራ ለማሳየት፣ ለዓመታት የተዘጉ ቤቶችን በማስከፈት የካቢኔ አባሎቻቸውን እያዞሩ ማስጎብኘታቸው አይዘነጋም።
ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤትና #መኖሪያ የሚገኝበትን በአራት ኪሎ አካባቢ የሚገኘው የአፄ ምኒልክ ቤተ መንግሥት በዘመናዊ መንገድ በማደስና በማልማት ወደ #ሙዚየምነት ለመቀየር፣ የፈረንሣይ መንግሥት #ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱ ታወቀ።
የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት ታላቁን የምኒልክ ቤተ መንግሥት በማደስና ተጨማሪ ልማቶችን በማከናወን፣ ለሕዝብና ለጎብኝዎች ክፍት የሚሆን የቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግ ዕቅድ ተይዟል፡፡ ይህንንም በፍጥነት በተግባር ለመቀየር የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርትሚኒስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶታል።
ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ራሳቸው በበላይነት እየተከታተሉት እንደሚገኝ ታውቋል። በዚህም መሠረት የተለያዩ አገሮች ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዳሳዩ፣ በዋናነት ግን የፈረንሣይ መንግሥት አስፈላጊውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱን ምንጮች ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ሳምንት የሚያደርጉትን የአውሮፓ ጉብኝት በፈረንሣይ የሚጀምሩ ሲሆን፣ በፈረንሣይ በሚኖራቸው የአንድ ቀን ቆይታ ቤተ መንግሥቱን ወደ ቱሪዝም መዳረሻ ለመቀየር ለተቀረፀው ፕሮጀክት የሚፈለገውን የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ የተመለከተ ስምምነት ተፈራርመው ይመለሳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ምንጮች ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በግንቦት ወር 2010 ዓ.ም. በውጤታማ ሥራ አፈጻጸም ላይ በወቅቱ ለነበሩ የካቢኔ ሚኒስትሮች ባደረጉት ገለጻ፣ የአፄ ምኒልክ ቤተ መንግሥትን የቱሪዝም መዳረሻ ማድረግ እንደሚገባ መግለጻቸው ይታወሳል።
ቤተ መንግሥቱ ኢትዮጵያ ምን እንደምትመስልና ጥንታዊ ገናናነቷ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ መሆን በወቅቱ መናገራቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ያለፋት የኢትዮጵያ መንግሥታት እያንዳንዳቸው በቅጥር ግቢው ትተው ያለፋትን አሻራ ለማሳየት፣ ለዓመታት የተዘጉ ቤቶችን በማስከፈት የካቢኔ አባሎቻቸውን እያዞሩ ማስጎብኘታቸው አይዘነጋም።
ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia