TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዜና እረፍት‼️የኢታብ ሳሙና ፋብሪካ ባለቤት አቶ #እስክንድር_ተስፋዬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጨፌ ኦሮሚያ በዛሬው እለት እያካሄደ ባለው 4ኛ ዓመት 5ኛ የስራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ የተለያዩ #ሹመቶችን አፀደቀ።

በዚህም መሰረት፦

1.ዶክተር ግርማ አመንቴ፦ በምክትል ርእሰ መስተዳደር ማእረግ የግብርና ዘርፍ ሀላፊ

2. አቶ አህመድ ቱሳ፦ በምክትል ርእሰ መስተዳደር ማእረግ የኢኮኖሚ ዘርፍ ሀላፊ

3. ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን፦ በምክትል ርእሰ መስተዳደር ማእረግ የማህበራዊ ዘርፍ ሀላፊ

4. አቶ አሰግድ ጌታቸው፦ የርእሰ መስተዳድር ጽህፈት ቤት ሀላፊ

5. አቶ ዳባ ደበሌ፦ የግብርና እና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ ሀላፊ

6. ዶክተር ኢንጂነር ፍቃዱ ፉፋ፦ የከተማ ልማትና ቤቶች ቢሮ ሀላፊ

7. አቶ ሙላቱ ጽጌ፦ የንግድ ቢሮ ሀላፊ

8. ዶክተር ሚልኬሳ ሚደጋ፦ የመሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ቢሮ ሀላፊ

9. አቶ ገረመው ሁሉቃ፦ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ

10. ወይዘሮ ሙና አህመድ፦ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ቢሮ ሀላፊ

11. አቶ አድማሱ ዳምጠው፦
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሀላፊ

12. አቶ ጥላሁን ወርቁ፦ የኢንተርፕራይዝና ኢንደስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ

13. ወይዘሮ ፈቲያ መሃመድ፦ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ

14. አቶ ኤባ ገርባ፦ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ

15. ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፦ የገቢዎች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

16. አቶ ተሾመ ግርማ ፦ ጠቅላይ አቃቤ ህግ

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጨፌ ኦሮሚያ በዛሬ ውሎው የኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ኦቢኤን) ዋና ዳርዬክተር እና የቦርድ አባላት #ሹመትን አፅድቋል።

በዚህም መሰረት፦

1. ጋዜጠኛ #መሃመድ_አደሞ፦ የኦቢኤን ዋና ዳይሬክተር

2. አቶ ሽመልስ አብዲሳ፦ የኦቢኤን ቦርድ ሰብሳቢ

3. ወይዘሮ ሌሊሴ ነሜ፦ የኦቢኤን የኦርድ አባል

4. ዶክተር ደረጄ ገረፋ፦ የኦቢኤን የኦርድ አባል

5. አቶ አድማሱ ዳምጠው፦ የኦቢኤን የኦርድ አባል

6. ረዳት ፕሮፌሰር ምህረቱ ሻንቆ

7. ኢንጂነር ወርቁ ጋቸና፦ የኦቢኤን የኦርድ አባል

8. ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ፦ የኦቢኤን የኦርድ አባል በመሆን ተሹመዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Forwarded from Kirubel Niguse
በተመጣጣኝ ዋጋ የሚፈልጉትን ነገሮች ለገበያየት 👇
#አልባሳት
#ጫማዎች
#ኤሌክትሮኒክስ
#ሰዐቶች
#ቦርሳዎች.. 👇
@onlinesaleandbuystore
🛑የሌለን የለም ብቻ ነው!
JOIN ብለው ቤተሰብ ይሁኑ ።
👇👇👇
https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEPkyxEP1snCoAkFGw
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
Forwarded from TIKVAH-ETHIOPIA (Tsegab Wolde)
ማስታወቂያ⬆️ኬራዊ ኢንተርናሸናል ሆቴል 🍎🍏🍅🍄 Kerawi International Hotel በአይነቱ ልዩ የሆነ ሆቴል በሀዋሳ ተከፈተ። ምቹና ዘመናዊ አልጋዎች፣ ቪአይፒ መዝናኛ፣ ምርጥ ዘመናዊና ባህላዊ ምግብ፣ ነጻ ኢንተርኔት - Wifi ለምቾትዎ ሊፍት አለልዎ! ከበቂ መኪና ማቆምያ ጋር።

አድራሻ፦ ሀዋሳ ወ/አማኑኤል ዱባሌ ጎዳና ፓትሪዳ ሆቴል ጎን

ጥቅምት 24/2011 ይመረቃል ።
👌🎼🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🤹‍♀🥁💞
Forwarded from Deleted Account
Forwarded from Deleted Account
🔥🔥 NEW OFFER🔥🔥

🚩 ያለን ብዛት ሳያልቅ እንድትገዙ እንመክራለን ።

📌 I7S WIRELESS EARPHONE

🎁 Compatible with ios & android devices

💵💵 Only 300br

አድራሻ :- ከ ልደታ ቤ/ክ ፊት ለፊት ባለዉ ዳሸን ባንክ 200ሜትር ገባ ብለው በግራ በኩል የሚያገኙት , AIA BUSINESS CENTER GROUND FLOOR


JOIN @HABMART @HABMART @HABMART
ፎቶ⬆️የሕዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ ስብሰባ ዛሬ መስከረም 28 ቀን 2011 ዓ.ም. በፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ንግግር ተከፍቷል።

ፎቶ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አለም አቀፉ ጋዜጠኛ የOpride.com መስራች እና ዋና ኤዲተር ጋዜጠኛ #መሀመድ_አደሞ የOBN ዋና ዳይሬክተር ሆኖ ተሹሟል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተመድ ማስጠንቀቂያ‼️የአለም ሀገራት የምድራችን ሙቀት እንዳይጨምር አስፈላጊውን እርምጃ ካልወሰዱ እስከ አውሮፓዊያኑ 2030 ባለው ጊዜ የከፋ የአየር ንብረት ለውጥ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል የተባበሩት መንግስታቱ ድርጅት/ተመድ/ #አስጠነቀቀ፡፡

ድርጅቱ ይሄን ያስታወቀው ከአውሮፓዊያኑ 2030 ወዲህ የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ #ሊጨምር እንደሚችል ከተነበየ በኋላ ነው ተብሏል፡፡

ይሄም ሁኔታ እውን ከሆነ በአለም በሚሊዮን በሚቆጠሩ ሰዎች ላይ የከፋ ድርቅ፣ ሰደድ እሳት፣ ጎርፍ እና የምግብ እጥረት እንደሚከሰት የመንግስታቱ ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ፓናል ገልጿል፡፡

ድርጅቱ እዚህ መደምደሜያ ላይ የደረሰው ለአለም ሙቀት መጨመር ምክንያት የሆነው የሙቀት አማቂ ጋዝ ልቀት አሁን ያለበትን ደረጃ ጥናት በማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

አሁን ላይ የአለም ሙቀት በ1 ዲግሪ ሴልሺየስ እየጨመረ ሲሆን ይህን ሁኔታ እንዳይባባስ በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት የአለም መንግስታት አስፈላጊውን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚገባ ተመልክቷል፡፡

የአለም ሙቀት ከ1 ነጥብ 5 ድግሪ ሴልሺየስ የዘለለ እንዳይሆን እስከ 2030 ባለው ጊዜ ውስጥ የአለም የካርቦን ዳይ ኦክሳይድ ልቀት በ45 በመቶ ሊቀንስ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

ምንጭ፦ ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሰንደቅ አላማ ቀን አከባበር መርሀ ግብር #ተሰረዘ። ከሰንደቅ አላማ ጋር ተያይዞ ያለውን አለመግባባት ታሳቢ በማድረግና አላስፈላጊ #ግጭት ላለማስነሳት የዘንድሮው የሰንደቅ አላማ ቀን አከባበር መሰረዙን የበዓል አዘጋጅ ኮሚቴው ተናግሯል። በዓሉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወስጥ እንግዶች በተገኙበት #ታስቦ ይውላል።

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM