TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሚሊኒየም አዳራሽ⬆️

"ዛሬ በሚሊንየም አዳራሽ ኤክስፔ ነበር እና ሰራተኛ ፍለጋ የመጡ ድርጅቶች የሰበሰቡትን CV እንዴት ትተው እንደሚሄዱ እየው። ጥንቃቄ እንዲደረግ መልዕክት አስተላልፍልኝ። በነገራችን ላይ ይህ የሆነበት ቦታ የምን ድርጅት እንደሆነም አይታወቅም።"

©Ab
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤ በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የቀረበለትን አዳዲስ የካቢኔ ሹመት አፅድቋል።

በዚህም መሰረት⬇️

1.አቶ ንጋቱ ዳኛቸው - የጥቃቅን እና አነስተኛ ቢሮ ሃላፊ

2. ወ/ሮ አልማዝ አብርሃ - የሴቶችና ህፃናት ቢሮ ሃላፊ

3. ወ/ሮ ፍሬህይወት ተፈራ የፍትህ ቢሮ ሃላፊ

4. አቶ ጀማሉ ጀምበር - የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ሃላፊ

5. አቶ ሺሰማ ገብረስላሴ - የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ

6. ዶ/ር ፍሬህይወት ገብረህይወት - የፐብሊክ ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊ

7.አቶ አሰፋ ዮሃንስ - የቴክኒክና ሙያ ቢሮ ሃላፊ

8.ኢንጂነር ኤርምያስ - የኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ

9.አቶ አብዱልፈታ የሱፍ - የንግድ ቢሮ ሃላፊ

10.አቶ ፎኢኖ ፎላ - የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ

11.ኢንጂነር ዮናስ አያሌው -
የኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ

12.ኢንጂነር ሽመልስ እሸቱ - የመሬት ማኔጅመንት ቢሮ ሃላፊ

13.አቶ ደረጄ ፈቃዱ - የፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር

14.አቶ ዘውዱ ቀፀላ - የሰራተኛና ማህበራዊ ቢሮ

15.ዶ/ር ዮሃንስ ጫላ - የጤና ቢሮ ሃላፊ

16.ኢንጂነር ሰናይት ዳምጠው - የቤቶች አስተዳደር ሃላፊ

17.አቶ ነብዩ ባየ - የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ

18. ዶክተር ታቦር ገብረመድህን - የትምህርት ቢሮ ሃላፊ በመሆን ተሾመዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ላደረግነው ሹመት መስፈርቱ ብቃትና #ኢትዮጵያዊነት ብቻ ነው" የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዛሬው የሚሊኒየም አዳራሽ ኤክስፖ ላይ የነበሩት ወጣቶች ባዩት እና በሆነው ነገር ማዘናቸው ገልፀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሀላባ⬆️

"ፀግሽ የሄዱት ሰዎች ተመልሰዋል ሀላባ ገብተዋል። ከተማዋ በጭፈራ ደምቃለች። ነገር ግን ሁለት አይነት ስሜት ነው ያለው የደስታ እና ለተቃወመው ወገን የንዴት። ህዝቡ በፌስቡክ ወሬ እንዳሸበር መልዕክቴን አስተላልፍልኝ።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳአህ እና የፕሬዘዳንት ኢሳያስ አማካሪ የማነ ገብረአብ የተካተቱበት ልዑክ አዲስ አበባ ገብቷል። ልዑካኑ ከፕሬዘዳንት ኢሳያስ የተላከውን ደብዳቤ ለጠ/ሚ ዶክተር አብይ አህመድ ይሰጣሉ እንዲሁም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደርጋሉ።

@tsegabwolde @tikahethiopia
#update ሶማሌ ክልል⬇️

ከኢፌዴሪ መከላከያ ሃይል ከፌደራል ፖሊስ እና ከሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል የተውጣጣ ኮማንድ ፖስት ተቋቁሟል።

በዛሬው እለት የደቡብ ምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጄኔራል በላይ ስዩም፣ የሶማሌ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር እና ሌሎች የፀጥታ ሃይል አዛዦች በተገኙበት በጂግጂጋ ከተማ ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱም የፌደራልና የክልሉ የፀጥታ ሃይሎች ለክልል ሰላም በትብብር እና በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።

ዋና አዛዡ እንደተናገሩት የፀጥታ ሃይሎቹ ክልሉን ወደ ሰላምና መረጋጋት ለመመለስ በመከላከያ ሰራዊት ዕዝ ስር ሆነው እንዲሰሩ ተወስኗል።

የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ለክልሉ ሰላምና ደህንነት በጋራ የሚሰራ መሆኑንም ዋና አዛዡ ተናግረዋል።

©FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደቡብ ሱዳን መንግስት በሀገሪቱ ለመጣው ሰላም የኢትዮጵያን ህዝብ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #አብይ አህመድን አመሰግኗል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አቶ ተስፋዬ በልጂጌ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በምክትል ከንቲባ መአረግ የህዝብ ግንኙነት ዋና አማካሪ ሆነው ተሹመዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia