THIKVAH-ETHIOPIA
3.95K subscribers
6.58K photos
218 videos
39 files
721 links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
THIKVAH-ETHIOPIA
🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ 🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች ➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ”  - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ…
#Update

🔴 “ ወደ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” - ቤተሰቦች

➡️ “ ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የተያዙት ” - ጤና ባለሙያ


የአራት ወራት አዲሱ ደወመዝ ክፍያ ስላልተፈጸመላቸው የሥራ ማቆም አድማ በመምታታቸው ከታሰሩት የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች መካከል አራቱ እንዳልተፈቱ ቤተሰቦቻቸውና የጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

መጀመሪያ የታሰሩት ዘጠኝ እንደነበሩ ሠራተኞቹ ከቀናት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ እስራቱ ቀጥሎ በአጠቃላይ 12 ሰዎች ታስረው እንደነበርና አራቱ እንዳልተፈቱ ነግረውናል።

የታሳሪ ቤተሰቦችና ጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

አንድ ጤና ባለሙያ በሰጡን ቃል፤ “ የተፈቱና ሌሎቹም በሥራ ገበታ ላይ ናቸው። የነዚህ የአራቱ አለመፈታት ግን እስካሁን ምስጢር ሆኖብናል። ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የታሰሩት ” ሲሉ ተናግረዋል።

የታሳሪ ቤተሰቦች በበኩላቸው “ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” ብለዋል።

“ ጥያቄው የሆስፒታሉ አካላት ሁሉ ነው። የፓለቲካ ጉዳይ የሌለበት የደመወዝ ጥያቄም ነው። ከደመወዝ ይከፈለን ውጪ ያነሱት ጥያቄ የለሞ ” ሲሉም ሞግተዋል።

አንዲት የታሳሪ ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ ባለቤታቸው ከታሰሩ ቀናት እንዳስቆጠሩ፣ እስካሁንም እንዳልተፈቱ፣ ያሉበትን ሁኔታም እንደማያውቁ ገልጸዋል።

ሌላኛው የታሳሪዋ የቅርብ ሰው የ10 ወር ጨቅላ ህፃን ያላት ጤና ባለሙያ እንደታሰረች ገልጸው፣ በዋስ እንደትለቀቅ እንኳ ቢሞከር ፈቃደኛ አካል አለመኖሩን ጠቁመዋል።

“ አጥቢ ከመሆኗ አንፃር ቀነ ገደብ ተጠይቆ ነበር። ፍርድ ቤት ዋስትና እንዲሰጣት ውሳኔ ቢያስተላልፍም እንዳትወጣ በፓሊስ ተከልክላለች ” ሲሉ ነው የወቀሱት።

የታሳሪ ቤተሰቦች፣ የታሰሩት የጤና ባለሙያዎች እንደሆኑ፣ ብዙ የህክምና ተገልጋዮች መጉላላታቸውም ከግምት ሊገባ እንደሚገባ አሳስበው፣ በፍጥነት እንዲፈቱ ጠይቀዋል።

የታሰሩት ለምን እንዳልተፈቱ ምላሽ ለማግኘት የጸጥታ አካላትን ለማካተት የተደረገው መከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለሆናቸው ለጊዜው አልተሳካም።

የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ከዚህ ቀደም  ጠይቀነው፣ በሌሎች ሆስፒታሎችም ጭምር ከ2000 በላይ ሠራተኞች ክፍያው እንዳልተፈጸመላቸው፣ የታሰሩትን ለማስፈታትም እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ነበር።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia
THIKVAH-ETHIOPIA
" በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ተፈናቅለዋል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር 🚨" አሁንም ከኬንያ ቱርካና ግዛት በኩል ዛቻዎች ስላሉ ስጋት ዉስጥ ነን ጥበቃና ከለላ ይደረግልን " - አርብቶአደሮች በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር ደቡብ ኦሞ ዳሰነች ወረዳና በኬንያ ቱርካና ግዛት አዋሳኝ አከባቢ ባለፉት ሁለት ቀናት በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች እንደተቀሰቀሰ በተነገረዉ ግጭት የበርካቶች…
" ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እየተመለሱ ነዉ ፤ የአስክሬን ፍለጋዉም ተጠናክሮ ቀጥሏል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ እና በሰሜን ኬንያ ቱርካና የድንበር አከባቢ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት ምክንያት ስየስ ከተባለ የዳሰነች መንደር ተፈናቅለዉ የነበሩ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶአደሮች ወደ ቀያቸዉ መመለስ መጀመራቸዉን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በቀጠናዉ በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባ ስርቆቶች መነሻ እንደተቀሰቀሰ በተገለፀዉ ግጭት ከሁለቱም ሀገሮች ከ30 በላይ አርብቶአደሮች ሕይወት መጥፋቱን መዘገባችን አይዘነጋም።

ግጭቱን ተከትሎም ኬንያን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስናት የቱርካና ሀይቅ ሰሜናዊ ጠረፍ ላለፉት አምስት ቀናት ከእንቅስቃሴ ዉጪ ሲሆን ከዳሰነች ወረዳ ስየስ መንደር በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ አርብቶ አደሮች በአቅራቢያቸዉ ወደሚትገኘዉ ሌላ መንደር ተፈናቅለዉ ነበር።

በትናትዉ ዕለት የዳሰነችና የቱርካና አከባቢ አስተዳደሮች ባሉበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እና የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የተመራ ልዑክ ከኢትዮጵያ በኩል በኬንያ የቱርካና ካውንቲ የፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነርና የአከባበው የፓርላማ ተወካይ የተመራ ልዑክ በሁለቱ ሀገራት የድንበር አከባቢ ተፈጠሮ የነበረዉን ግጭት በፍጥነት ለመፍታትና አከባቢውን ወደነበረበት ሰላም ለመመለስ መነጋገራቸዉን ተከትሎ ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸዉ የመመለስ እየተሰራ እንደሆነ አቶ ታደለ ሀቶ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ከዚሁ ጎን ለጎን በሀይቅ ዉስጥ የጠፉ አስከሬኖች የማፈላለጉ ስራም ተጠናክሮ መቀጠሉን ያነሱት አቶ ታደለ በሁለቱም ወገን የተወሰዱ ንብረቶችን የማስመለስና በአከባቢዉ ጠንካራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ተጠናክረዉ በሚቀጥሉበት ዙሪያ ዉይይት ማድረጋቸዉን አስታዉቀዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyHW

@thikvahethiopia
" ከየካቲት 24 በኋላ የፋይዳ መታወቂያ የሌለው ደንበኛ የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር ትኬት መቁረጥ አይችልም " - የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር

የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ለመንገደኞች የጉዞ ትኬት የሚያገኙበትን መንገድ ከሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ  ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረጉን ገልጿል።

ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረውን በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ ሂደት አገልግሎቱን ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ መደረጉን የኢትዮጵያ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር የኮምዩኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ወ/ሮ እስራኤል ወልደ መስቀል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ወ/ሮ እስራኤል " ማስታወቂያዎችን ስንሰራ የቆየን በመሆኑ የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ ነው ነገር ግን ይሄንን ሳምንት ልዩ በሆነ መንገድ እና ሰውም የአጠቃቀም ጉድለት ስላለ የጉዞ ትኬት እየቆረጥን እንገኛለን ከሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ በኃላ ግን ያለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የባቡሩን ትኬት ማግኘት አይቻልም " ብለዋል።

ክፍያው የሚፈጸመው በቴሌ ብር ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች የፋይዳ የምዝገባ ቁጥራቸውን ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ደግሞ ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል።

ባለሞያዋ በትኬት ዋጋ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ አለመኖሩን አንስተው በነባሩ ዋጋ ዲጂታላይዝ ብቻ መደረጉን ጠቁመዋል።

ከዚህ ቀደም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ፉሪ የሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎች አሰራሩ ዲጂታላይዝ ስለሆነ የመንገደኞችን የአገልግሎት ትኬት የመቁረጥ ስራ እንደማይሰሩ ወ/ሮ እስራኤል ገልጸዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyAA

@thikvahethiopia