#ዶክተር_ፈቀደ_አግዋር🙏
'' በርካታ የልብ ታማሚዎች ወረፋ ሳይደርሳቸው ህይወታቸውን ያጣሉ '' - ዶክተር ፈቀደ አግዋር
በኢትዮጵያ የልብ ህክምና በተሟላ ሁኔታ እየተሰጠ የሚገኘው አዲስ አበባ ከተማ በመሆኑ ወረፋ ሳይደርሳቸው ህይወታቸው የሚያልፉ የልብ ታማሚዎች መኖራቸው ይነገራል።
ዶክተር ፈቀደ አግዋር በኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል '' የልብ ቀዶ ህክምና '' ሀኪም ናቸው። 800 የልብ ቀዶ ህክምና አድርገዋል።
በሂሊንግ ቫልቭስ ኢትዮጵያ ደግሞ (HVE) 25 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ነፃ የልብ ቀዶ ህክምና ለ30 ታዳጊዎች ሰርተዋል። በተጨማሪም " የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ " የተሰኘ መጽሐፍም ለአንባቢ አበርክተዋል።
ዶ/ር ፈቀደ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሀራ በርሀ በታች ባሉ ሀገሮች ላይ በአሁኑ ሰዓት በተደጋጋሚ በሚከሰት ቶንሲል ምክንያት የሚፈጠር የልብ ህመም ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ድረስ በከፍተኛ ሁኔታ ለልብ ህመም መፈጠር ምክንያት እንደሆነ ይናገራሉ።
በቅርቡ በሂሊንግ ቫልቭስ ኢትዮጵያ (HVE) የነጻ ህክምና ተጠቃሚዋ መሆን የቻለችው የ18 አመቷ ታዳጊም የልብ ህመሟ በቶንሲል ምክንያት የተከሰተ ሲሆን 4 ሰዓታት በፈጀው አንድ የግራ ልብ በር ቀዶ ህክምና በቶንሲል ምክንያት ክፋኛ የተጎዳው የታዳጊዋ የልብ በር በመቀየር የተሳካ ህክምና አድርጋለች።
የልብ ቀዶ ህክምና የሚሰጠው ደረት ተከፍቶ፣ ልብና ሳንባ ቁሞ፣ የደም ዝውውር ለማሽን ተሰጥቶ በመጨረሻም ልብ ተከፍቶ ህክምናው እንደሚሰጥና በዚህም ብዙ የህክምና ሂደቶችን እንደሚያልፍ ዶ/ር ፈቀደ አግዋር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዳሉ።
የልብ ህመም በተፈጥሮ ሊከሰት የሚችል ሲሆን በዓለም ላይ '' ከ1 ሺ ሰው 10 ሰው '' በተፈጥሮ የልብ ችግር ይኖርበታል ተብሎ ይታሰባል።
በሌላ በኩል ደግሞ በደም ግፊት፣ በስኳር በሽታ ምክንያትም የልብ ህመም እንደሚከሰት የልብ ሀኪሙ ዶክተር ፈቀደ ገልፀዋል።
አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የልብ ህክምና በተሟላ ሁኔታ የሚሰጠው በአዲስ አበባ በመሆኑ ለታማሚዎች ፈተና እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
" በሽዎች እሚቆጠሩ ሰዎች ወረፋ ይጠብቃሉ፣ወረፋ ሳይደርሳቸው በርካቶችም ህይወታቸውን ያጣሉ '' ብለዋል።
በመጨረሻም ተሳክቶላቸው ወረፋ ሲደርሳቸው በጣም ያረፈዱና የተወሳሰቡ ህክምና እንድንሰጥ እንገደዳለን ሲሉ ዶ/ር ፈቀደ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።
" ለአንድ የልብ ህመምተኛ ህክምና ለመስጠት በርካታ ባለሙያዎች፣ ብዙ ማሽን ጥቅም ላይ ይውላላል ከዚህ አንፃር በአሁኑ ሰአት በኛ ሀገር የልብ ህክምና ገና ጅማሮ ላይ ነው ማለት እንችላለን " ብለዋል።
እንደ መፍትሔ . . .
በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ሁሉንም ነገር ያሟላ የልብ ህክምና የሚሰጠው ተቋም የኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል እንደሆነ ዶ/ር ፈቀደ አግዋር ይናገራሉ።
ይህን ማዕከል አሳድጎ ትምህርት ቤት በማድረግ ብዙ የልብ ህክምና ባለሙያዎችን በማፍራት በየከተማው፣ በየክልሉ እንዲሄዱ በማድረግ ችግሩን መፍታት የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ሲሉ ኃሳባቸውን ያቀርባሉ።
በተጨማሪም አሁን ላይ ማዕከሉ ያለውን አቅም አሳድጎ ብዙ የልብ ቀዶ ህክምናዎችንም እንዲሰራ ቢደረግ ለበርካቶች መድረስ እንደሚቻልም ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ህክምና እና በደም ስር ገብቶ የሚሰራ የልብ ህክምና የሚሰጡት ቅዱስ ጳውሎስ፣ ጥቁር አንበሳና ኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል መሆናቸውን ከኢትዮጵያ የልብ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ThikvahEthiopia
Via @tikvahethmagazine
'' በርካታ የልብ ታማሚዎች ወረፋ ሳይደርሳቸው ህይወታቸውን ያጣሉ '' - ዶክተር ፈቀደ አግዋር
በኢትዮጵያ የልብ ህክምና በተሟላ ሁኔታ እየተሰጠ የሚገኘው አዲስ አበባ ከተማ በመሆኑ ወረፋ ሳይደርሳቸው ህይወታቸው የሚያልፉ የልብ ታማሚዎች መኖራቸው ይነገራል።
ዶክተር ፈቀደ አግዋር በኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል '' የልብ ቀዶ ህክምና '' ሀኪም ናቸው። 800 የልብ ቀዶ ህክምና አድርገዋል።
በሂሊንግ ቫልቭስ ኢትዮጵያ ደግሞ (HVE) 25 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ነፃ የልብ ቀዶ ህክምና ለ30 ታዳጊዎች ሰርተዋል። በተጨማሪም " የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ " የተሰኘ መጽሐፍም ለአንባቢ አበርክተዋል።
ዶ/ር ፈቀደ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሰሀራ በርሀ በታች ባሉ ሀገሮች ላይ በአሁኑ ሰዓት በተደጋጋሚ በሚከሰት ቶንሲል ምክንያት የሚፈጠር የልብ ህመም ከህፃናት እስከ አዋቂዎች ድረስ በከፍተኛ ሁኔታ ለልብ ህመም መፈጠር ምክንያት እንደሆነ ይናገራሉ።
በቅርቡ በሂሊንግ ቫልቭስ ኢትዮጵያ (HVE) የነጻ ህክምና ተጠቃሚዋ መሆን የቻለችው የ18 አመቷ ታዳጊም የልብ ህመሟ በቶንሲል ምክንያት የተከሰተ ሲሆን 4 ሰዓታት በፈጀው አንድ የግራ ልብ በር ቀዶ ህክምና በቶንሲል ምክንያት ክፋኛ የተጎዳው የታዳጊዋ የልብ በር በመቀየር የተሳካ ህክምና አድርጋለች።
የልብ ቀዶ ህክምና የሚሰጠው ደረት ተከፍቶ፣ ልብና ሳንባ ቁሞ፣ የደም ዝውውር ለማሽን ተሰጥቶ በመጨረሻም ልብ ተከፍቶ ህክምናው እንደሚሰጥና በዚህም ብዙ የህክምና ሂደቶችን እንደሚያልፍ ዶ/ር ፈቀደ አግዋር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስረዳሉ።
የልብ ህመም በተፈጥሮ ሊከሰት የሚችል ሲሆን በዓለም ላይ '' ከ1 ሺ ሰው 10 ሰው '' በተፈጥሮ የልብ ችግር ይኖርበታል ተብሎ ይታሰባል።
በሌላ በኩል ደግሞ በደም ግፊት፣ በስኳር በሽታ ምክንያትም የልብ ህመም እንደሚከሰት የልብ ሀኪሙ ዶክተር ፈቀደ ገልፀዋል።
አሁን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ የልብ ህክምና በተሟላ ሁኔታ የሚሰጠው በአዲስ አበባ በመሆኑ ለታማሚዎች ፈተና እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።
" በሽዎች እሚቆጠሩ ሰዎች ወረፋ ይጠብቃሉ፣ወረፋ ሳይደርሳቸው በርካቶችም ህይወታቸውን ያጣሉ '' ብለዋል።
በመጨረሻም ተሳክቶላቸው ወረፋ ሲደርሳቸው በጣም ያረፈዱና የተወሳሰቡ ህክምና እንድንሰጥ እንገደዳለን ሲሉ ዶ/ር ፈቀደ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል።
" ለአንድ የልብ ህመምተኛ ህክምና ለመስጠት በርካታ ባለሙያዎች፣ ብዙ ማሽን ጥቅም ላይ ይውላላል ከዚህ አንፃር በአሁኑ ሰአት በኛ ሀገር የልብ ህክምና ገና ጅማሮ ላይ ነው ማለት እንችላለን " ብለዋል።
እንደ መፍትሔ . . .
በኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ሁሉንም ነገር ያሟላ የልብ ህክምና የሚሰጠው ተቋም የኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል እንደሆነ ዶ/ር ፈቀደ አግዋር ይናገራሉ።
ይህን ማዕከል አሳድጎ ትምህርት ቤት በማድረግ ብዙ የልብ ህክምና ባለሙያዎችን በማፍራት በየከተማው፣ በየክልሉ እንዲሄዱ በማድረግ ችግሩን መፍታት የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ሲሉ ኃሳባቸውን ያቀርባሉ።
በተጨማሪም አሁን ላይ ማዕከሉ ያለውን አቅም አሳድጎ ብዙ የልብ ቀዶ ህክምናዎችንም እንዲሰራ ቢደረግ ለበርካቶች መድረስ እንደሚቻልም ገልፀዋል።
በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ህክምና እና በደም ስር ገብቶ የሚሰራ የልብ ህክምና የሚሰጡት ቅዱስ ጳውሎስ፣ ጥቁር አንበሳና ኢትዮጵያ የልብ ህክምና ማዕከል መሆናቸውን ከኢትዮጵያ የልብ ህክምና ባለሙያዎች ማህበር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ThikvahEthiopia
Via @tikvahethmagazine
THIKVAH-ETHIOPIA
#NBE : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ማክሰኞ የካቲት 18 ቀን 2017 እንደሚያካሂድ አሳውቋል። ለጨረታ የሚቀርበው የውጭ ምንዛሪ መጠን 60 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፣ ጨረታው ለሁሉም ባንኮች ክፍት እነደሚሆን ገልጿል። @thikvahethiopia
#NBE : ብሔራዊ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ 135 ብር ዋጋ መሸጡን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት መሰረት፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደረገ።
በዚህ ጨረታ 27 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ መኖሩን ገልጿል።
ባንኩ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።
ይህ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የገንዘብ ገበያውን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሪ ተገኝነትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተጠቁሟል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ትግበራ ከገባ ካለፈው ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አንስቶ የአሁን የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጨረታ ሲወጣ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል ።
በዚህም በመጀመሪያዉ ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን እና 27 ባንኮች በጨረታው ላይ መሳተፋቸውን ገልፆ ነበር። #Capital
@thikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባካሄደው ልዩ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ውጤት መሰረት፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 135 ነጥብ 6185 ብር መሆኑን ይፋ አደረገ።
በዚህ ጨረታ 27 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን፣ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተሳትፎ መኖሩን ገልጿል።
ባንኩ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝና ከዋጋና ከውጭ ምንዛሪ መረጋጋት ጋር በሚስማማ መልኩ ተጨማሪ ጨረታዎችን እንደሚያካሂድ አስታውቋል።
ይህ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ የገንዘብ ገበያውን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሪ ተገኝነትን ለማሻሻል የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑ ተጠቁሟል።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ወደ ትግበራ ከገባ ካለፈው ሐምሌ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አንስቶ የአሁን የውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጨረታ ሲወጣ ለ2ኛ ጊዜ መሆኑ ይታወቃል ።
በዚህም በመጀመሪያዉ ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ፣ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ107 ነጥብ 9 ብር ዋጋ መሸጡን እና 27 ባንኮች በጨረታው ላይ መሳተፋቸውን ገልፆ ነበር። #Capital
@thikvahethiopia
Jasiri Africa
ለጀማሪ ሴት ስራ ፈጣሪዎች የተዘጋጀው እደል እንዳያመልጥሽ
- ባለሽበት የስራ መስክ በቂ የሆነ ችሎታ ካለሽ፣ አዲስ እና በፍጥነት የማደግ አቅም ያለው ተቋም የመመስረት ፍላጎት ካለሽ፣ እንዲሁም ችግር የመፍታትና ተጽዕኖ የመፍጠር ብቃት ካለሽ ይህ ዕድል ላንቺ ነው፤
- ሙሉ ወጪሽ ተሸፍኖ በሩዋንዳ የ 3 ወር ስልጠና፤ የቢዝነስ መነሻ እንዲሁም ቢዝነሱ እስኪቋቋም ለተወሰኑ ወራት የሚያቆይ የኪስ ገንዘብ የሚታገኚበት፤
- ክህሎት ያላቸው ብቁ አለም አቀፍ አማካሪዎችን ጨምሮ ስልጠናሽን ጨርሰሽ ወደ ኢትዮጵያ ስትመለሺ ለተወሰነ ግዜ የምትጠቀሚበት የጋራ ቢሮ (co-working space) ተመቻችቷል።
- ኬንያ፣ ሩዋንዳ ወይም እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢዝነስ መጀመር ምርጫሽ ከሆነም በየሀገሩ ተመሳሳይ ድጋፍ ይደረግልሻል።
8ኛው ዙር ለመቀላቀል፣ ዛሬውኑ ተመዝገቢ!
👉 https://bit.ly/40Ai4oR
ለበለጠ መረጃ @jasiri4Africa
ለጀማሪ ሴት ስራ ፈጣሪዎች የተዘጋጀው እደል እንዳያመልጥሽ
- ባለሽበት የስራ መስክ በቂ የሆነ ችሎታ ካለሽ፣ አዲስ እና በፍጥነት የማደግ አቅም ያለው ተቋም የመመስረት ፍላጎት ካለሽ፣ እንዲሁም ችግር የመፍታትና ተጽዕኖ የመፍጠር ብቃት ካለሽ ይህ ዕድል ላንቺ ነው፤
- ሙሉ ወጪሽ ተሸፍኖ በሩዋንዳ የ 3 ወር ስልጠና፤ የቢዝነስ መነሻ እንዲሁም ቢዝነሱ እስኪቋቋም ለተወሰኑ ወራት የሚያቆይ የኪስ ገንዘብ የሚታገኚበት፤
- ክህሎት ያላቸው ብቁ አለም አቀፍ አማካሪዎችን ጨምሮ ስልጠናሽን ጨርሰሽ ወደ ኢትዮጵያ ስትመለሺ ለተወሰነ ግዜ የምትጠቀሚበት የጋራ ቢሮ (co-working space) ተመቻችቷል።
- ኬንያ፣ ሩዋንዳ ወይም እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ቢዝነስ መጀመር ምርጫሽ ከሆነም በየሀገሩ ተመሳሳይ ድጋፍ ይደረግልሻል።
8ኛው ዙር ለመቀላቀል፣ ዛሬውኑ ተመዝገቢ!
👉 https://bit.ly/40Ai4oR
ለበለጠ መረጃ @jasiri4Africa
#Ethiotelecom
🪪 የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የካርድ ኅትመት አገልግሎት በበርካታ የክልል ከተሞች እየተሰጠ ይገኛል!!
በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ‘’NID (Fayda) Printing’’ መተግበሪያ ተጠቅመው የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ!
👉 እንደምርጫዎ በ6 የሥራ ሰዓታት፣ በ2 ቀናት ወይም በ7 ቀናት ውስጥ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ይረከቡ፡፡
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
🪪 የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የካርድ ኅትመት አገልግሎት በበርካታ የክልል ከተሞች እየተሰጠ ይገኛል!!
በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ‘’NID (Fayda) Printing’’ መተግበሪያ ተጠቅመው የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ!
👉 እንደምርጫዎ በ6 የሥራ ሰዓታት፣ በ2 ቀናት ወይም በ7 ቀናት ውስጥ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ይረከቡ፡፡
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
THIKVAH-ETHIOPIA
#ፋይዳ #NationalID " ከፍርድ ቤት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጥያቄው ከዛ እስካልመጣ [የግል መረጃ] ለመንግስት የሥራ አስፈጻሚ አይሰጥም " - አቶ ዮዳሄ አርአያሥላሴ ኢትዮጵያ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምን በይፋ ካስተዋወቀችበት ጀምሮ እስከ አሁን 12 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበዋል፤ እስካሁንም ይህንን አገልግሎት ከ50 በላይ ከሆኑ አገልግሎቶች ጋር የማስተሳሰር ሥራም ተሰርቷል። ይህ ፕሮጀክት…
#ፋይዳ #NationalID
" የትምህርት እና የጤና መረጃን በፋይዳ ለማረጋገጥ የሚያስችል የዋሌት ሥርዓት እየሰራን ነው " - ራሄል አብርሃም የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ
° " በምዝገባ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ተቋማት በቅርቡ ይቀላቀላሉ ! "
ስለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በተሰበሰቡ ጥያቄዎች ላይ የተቋሙ ምክትል አስተባባሪ ራሄል ምላሽ ሰጥተዋል። በዋናነትም ከትግበራና አፈጻጸም ላይ ተያይዞ ያሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።
ምክትል አስተባባሪዋ፥ በዚህ ወቅት ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት በቀጣዮቹ አምስት ወራት ወደ 30 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ መታቀዱን ጠቁመዋል።
ለዚህም አሁን ላይ በአጋርነት ከሚሰሩት ኢትዮ ፖስት እና ኢትዮ ቴሌኮም በተጨማሪ፥ የግል ተቋማትን ወደ ምዝገባ ሥርዓቱ ለማስገባት ጨረታ መውጣቱን ገልጸው፤ ለዚሁ የሚያስፈልጉ የቁሳቁሶች ግዢም በሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ በቅርቡ ዜጎች የተለያዩ አገልግሎት የሚያገኙበትን የራሱን የሞባይል መተግበሪያ በ Android እንዲሁም IOS አስተዋውቋል። እንደ ም/አስተባባሪዋ ከሆነ በቅርቡ የዋሌት ሥርዓትም እንደሚዘረጋ ጠቁመዋል።
የአዲሱ የፋይዳ የዋሌት ሥርዓት ምንድን ነው ?
አዲሱ የዋሌት ሥርዓት "የትምህርት እና የጤና መረጃህን ከፋይዳ ጋር በማገናኘትና በማረጋገጥ በስልክህ ይዘህ እንድትንቀሳቀስ ያስችልኃል" ሲሉ ገልጸዋል።
"ስኮላርሺፕ የሚጠቀሙ ተማሪዎች አንድን የትምህርት ዶክመንት ለማረጋገጥ በተማሩበት ትምህርት ቤት ተገኝተው በመኃተም ወይም ትምህርት ቤታቸው ለሚያመለክቱበት ት/ቤት ማስላክ ነበር። ይህንን አላስፈላጊ መጉላላት የሚያስቀር ዋሌት እየሰራን ነው።" ራሄል አብርሃም
የዋሌት ሥርዓቱ አላስፈላጊ መረጃ እንዳይሰጥ ጭምር ያግዛል ያሉት ምክትል አስተባባሪዋ "አላስፈላጊ መረጃም እንዳይሰጥ ይጠቅማል፤ እድሜህን ብቻ የሚፈልግ ተቋም እድሜህን ብቻ በፋይዳ በኩል Verifiable Credentials (VCs) በመፍጠር ለዛ ተቋም መላክ ትችላለህ፥ ያም ተቋም ያንን አይቶ አገልግሎት የሚሰጥበትን እየሰራን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
"ፋይዳ ላይ ያለው ፎቶዬ ተበላሽቷል እንዴት መቀየር እችላለሁ?"
ይህ ጥያቄ ከበርካታ ቤተሰቦቻችን የተነሳ ጥያቄ ሆኖ አግኝተነዋል። ይህንንም አስመልክቶ የፋይዳ መታወቂያ ላይ ያሉ መረጃዎችን እንዴት መቀየር እንችላለን ብለን ለምክትል አስተባባሪዋ ጥያቄውን አቅርበንላቸዋል።
በምዝገባ ወቅት የሚፈጠሩ የቃላት ግድፈት፤ የዶክመንት አለመገናኘት እና መሰል ስህተቶች በፋይዳ ዌብሳይት ላይ በመግባት እና ማስተካከያ በመጠየቅ እንዲስተካከል የሚያስችል አሰራር አሁን ላይ መኖሩን ገልጸዋል።
ሆኖም የፎቶ እንዲሁም ማንነት ላይ ለውጥ የሚያመጡ የባዮሜትሪክ መረጃዎች ለውጥ በተመለከተ የህግ ማዕቀፎች መዘጋጀታቸውንና አሁን ላይ በምዝገባ ላይ ላሉ አጋር ተቋማት የሥልጠና ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የፎቶ ቅያሬን በተመለከተም በአጭር ጊዜ ውስጥ ዜጎች በምዝገባ ተቋማት በመሄድ ፎቶ መቀየር እንዲችሉ የሚያስችላቸውን ሥርዓት በመዘርጋት ላይ እንገኛለን ብለዋል።
- የፋይዳ ካርድ በድጋሜ ማሳተም ይቻላል?
- የጣትና የአይን አሻራ የሌላቸው ዜጎች መመዝገብ ይችላሉ ?
- የጥሪ ማዕከላችሁ ይሰራል ? እና መሰል ከቲክቫህ ቤተሰቦች የተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
📱 የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ ራሄል አብርሃም ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች ይመልከቱ https://youtu.be/7cYEVy3sDd8
@thikvahethiopia
" የትምህርት እና የጤና መረጃን በፋይዳ ለማረጋገጥ የሚያስችል የዋሌት ሥርዓት እየሰራን ነው " - ራሄል አብርሃም የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ
° " በምዝገባ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ተቋማት በቅርቡ ይቀላቀላሉ ! "
ስለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች በተሰበሰቡ ጥያቄዎች ላይ የተቋሙ ምክትል አስተባባሪ ራሄል ምላሽ ሰጥተዋል። በዋናነትም ከትግበራና አፈጻጸም ላይ ተያይዞ ያሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።
ምክትል አስተባባሪዋ፥ በዚህ ወቅት ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት በቀጣዮቹ አምስት ወራት ወደ 30 ሚሊዮን ዜጎችን ለመመዝገብ መታቀዱን ጠቁመዋል።
ለዚህም አሁን ላይ በአጋርነት ከሚሰሩት ኢትዮ ፖስት እና ኢትዮ ቴሌኮም በተጨማሪ፥ የግል ተቋማትን ወደ ምዝገባ ሥርዓቱ ለማስገባት ጨረታ መውጣቱን ገልጸው፤ ለዚሁ የሚያስፈልጉ የቁሳቁሶች ግዢም በሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ በቅርቡ ዜጎች የተለያዩ አገልግሎት የሚያገኙበትን የራሱን የሞባይል መተግበሪያ በ Android እንዲሁም IOS አስተዋውቋል። እንደ ም/አስተባባሪዋ ከሆነ በቅርቡ የዋሌት ሥርዓትም እንደሚዘረጋ ጠቁመዋል።
የአዲሱ የፋይዳ የዋሌት ሥርዓት ምንድን ነው ?
አዲሱ የዋሌት ሥርዓት "የትምህርት እና የጤና መረጃህን ከፋይዳ ጋር በማገናኘትና በማረጋገጥ በስልክህ ይዘህ እንድትንቀሳቀስ ያስችልኃል" ሲሉ ገልጸዋል።
"ስኮላርሺፕ የሚጠቀሙ ተማሪዎች አንድን የትምህርት ዶክመንት ለማረጋገጥ በተማሩበት ትምህርት ቤት ተገኝተው በመኃተም ወይም ትምህርት ቤታቸው ለሚያመለክቱበት ት/ቤት ማስላክ ነበር። ይህንን አላስፈላጊ መጉላላት የሚያስቀር ዋሌት እየሰራን ነው።" ራሄል አብርሃም
የዋሌት ሥርዓቱ አላስፈላጊ መረጃ እንዳይሰጥ ጭምር ያግዛል ያሉት ምክትል አስተባባሪዋ "አላስፈላጊ መረጃም እንዳይሰጥ ይጠቅማል፤ እድሜህን ብቻ የሚፈልግ ተቋም እድሜህን ብቻ በፋይዳ በኩል Verifiable Credentials (VCs) በመፍጠር ለዛ ተቋም መላክ ትችላለህ፥ ያም ተቋም ያንን አይቶ አገልግሎት የሚሰጥበትን እየሰራን ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
"ፋይዳ ላይ ያለው ፎቶዬ ተበላሽቷል እንዴት መቀየር እችላለሁ?"
ይህ ጥያቄ ከበርካታ ቤተሰቦቻችን የተነሳ ጥያቄ ሆኖ አግኝተነዋል። ይህንንም አስመልክቶ የፋይዳ መታወቂያ ላይ ያሉ መረጃዎችን እንዴት መቀየር እንችላለን ብለን ለምክትል አስተባባሪዋ ጥያቄውን አቅርበንላቸዋል።
በምዝገባ ወቅት የሚፈጠሩ የቃላት ግድፈት፤ የዶክመንት አለመገናኘት እና መሰል ስህተቶች በፋይዳ ዌብሳይት ላይ በመግባት እና ማስተካከያ በመጠየቅ እንዲስተካከል የሚያስችል አሰራር አሁን ላይ መኖሩን ገልጸዋል።
ሆኖም የፎቶ እንዲሁም ማንነት ላይ ለውጥ የሚያመጡ የባዮሜትሪክ መረጃዎች ለውጥ በተመለከተ የህግ ማዕቀፎች መዘጋጀታቸውንና አሁን ላይ በምዝገባ ላይ ላሉ አጋር ተቋማት የሥልጠና ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የፎቶ ቅያሬን በተመለከተም በአጭር ጊዜ ውስጥ ዜጎች በምዝገባ ተቋማት በመሄድ ፎቶ መቀየር እንዲችሉ የሚያስችላቸውን ሥርዓት በመዘርጋት ላይ እንገኛለን ብለዋል።
- የፋይዳ ካርድ በድጋሜ ማሳተም ይቻላል?
- የጣትና የአይን አሻራ የሌላቸው ዜጎች መመዝገብ ይችላሉ ?
- የጥሪ ማዕከላችሁ ይሰራል ? እና መሰል ከቲክቫህ ቤተሰቦች የተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
📱 የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ምክትል አስተባባሪ ራሄል አብርሃም ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡትን ምላሾች ይመልከቱ https://youtu.be/7cYEVy3sDd8
@thikvahethiopia
" ይህ ተግባር ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " - የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በላከው መግላጫ ፤ " ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ ችያለሁ " ሲል ገለጸ።
" ይኽን የመንግሥት ተግባር ይበልጥ አስከፊ የሚያደርገው እነዚህ ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች የት እንደሚገኙ አለመታወቅና ቤተሰቦቻቸውም በመንግሥት አካል የተያዘ ግለሰብ ሊገኙባቸው ይችላሉ የሚሏቸውን ቦታዎች ቢያስሱም ለማግኘት አለመቻላቸው ነው " ብሏል።
" በተጨማሪ አንዳንዶቹ ከተወሰኑ ቀናት መሰወር በኋላ በድንገት የት እንደነበሩ እንኳ መናገር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደቤታቸው መመለሳቸው ነው " ሲል ገልጿል።
ፓርቲው " ይሕ ሕጋዊ መንገድን ያልተከተለ የመንግሥትን ተግባር በሕግ ተጠያቂ መሆን ያለበትን አካል በቁጥጥር ሥር ማዋል ሳይሆን በወንበዴ የሚፈፀም አይነት አፈና እንደሆነ እና ይኽም ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " ብሏል።
አሁንም በዚህ አይነት አፈና ውስጥ ያሉ ወጣቶች እንዳሉ ፓርቲው ማረጋገጡን ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ እንደቻለ አመልክቷል።
ፓርቲው በዚሁ መግለጫው " መንግሥት አፍኖ የያዛቸውን ወጣቶች የት እንደሚገኙ ይፋ እንዲያደርግ " ሲል ጠይቋል።
" መንግሥት አፍኗቸው ያሉ ወጣቶች የወንጀል ተጠያቂነት አለባቸው ካለ ክሱን በግልጽ መሥርቶ እራሣቸውን የመከላከል መብታቸው እንዲያከብር አልያም በቶሎ እንዲፈታቸው " ብሏል።
" ያፈናቸውን ወጣቶች ቤተሰብ እንዲጎበኛቸው፣ የሕግ ጠበቃ እንዲቀርብላቸው እና አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግላቸው "ም ብሏል።
ፓርቲው " ሕገወጥ ተግባሩን የፈፀሙ የመንግሥት አካላትን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች የመንግሥት አካላትን በማሳተፍ ተጠያቂነት እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን እንዲያደርግ እንጠይቃለን " ብሏል።
" ይህን አለማድረግ ግን ሥርዓት አልበኝነትን መጋበዝ፣ ለሕገወጥ ተግባራት ሽፋን መስጠት ብሎም ድጋፍ በማድረግ ቡራኬ እንደመስጠት እንቆጥራለን " ሲል ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ተመልክቶ የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ እንዲያደርግም ፓርቲው በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@thikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) በላከው መግላጫ ፤ " ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ላይ ወጣቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየታፈኑ የት እንደገቡ ሳይታወቅ መሰወራቸውን ከቤተሰቦቻቸው እና ከተለያዩ አካላት ለመገንዘብ ችያለሁ " ሲል ገለጸ።
" ይኽን የመንግሥት ተግባር ይበልጥ አስከፊ የሚያደርገው እነዚህ ታፍነው የተወሰዱ ወጣቶች የት እንደሚገኙ አለመታወቅና ቤተሰቦቻቸውም በመንግሥት አካል የተያዘ ግለሰብ ሊገኙባቸው ይችላሉ የሚሏቸውን ቦታዎች ቢያስሱም ለማግኘት አለመቻላቸው ነው " ብሏል።
" በተጨማሪ አንዳንዶቹ ከተወሰኑ ቀናት መሰወር በኋላ በድንገት የት እንደነበሩ እንኳ መናገር በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ወደቤታቸው መመለሳቸው ነው " ሲል ገልጿል።
ፓርቲው " ይሕ ሕጋዊ መንገድን ያልተከተለ የመንግሥትን ተግባር በሕግ ተጠያቂ መሆን ያለበትን አካል በቁጥጥር ሥር ማዋል ሳይሆን በወንበዴ የሚፈፀም አይነት አፈና እንደሆነ እና ይኽም ሕዝብን ለማስተዳደር ሥልጣን ላይ ካለ አካል የማይጠበቅ አስፀያፊ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን " ብሏል።
አሁንም በዚህ አይነት አፈና ውስጥ ያሉ ወጣቶች እንዳሉ ፓርቲው ማረጋገጡን ቤተሰቦቻቸውም በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንዳሉ ለማወቅ እንደቻለ አመልክቷል።
ፓርቲው በዚሁ መግለጫው " መንግሥት አፍኖ የያዛቸውን ወጣቶች የት እንደሚገኙ ይፋ እንዲያደርግ " ሲል ጠይቋል።
" መንግሥት አፍኗቸው ያሉ ወጣቶች የወንጀል ተጠያቂነት አለባቸው ካለ ክሱን በግልጽ መሥርቶ እራሣቸውን የመከላከል መብታቸው እንዲያከብር አልያም በቶሎ እንዲፈታቸው " ብሏል።
" ያፈናቸውን ወጣቶች ቤተሰብ እንዲጎበኛቸው፣ የሕግ ጠበቃ እንዲቀርብላቸው እና አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግላቸው "ም ብሏል።
ፓርቲው " ሕገወጥ ተግባሩን የፈፀሙ የመንግሥት አካላትን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች የመንግሥት አካላትን በማሳተፍ ተጠያቂነት እና የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን እንዲያደርግ እንጠይቃለን " ብሏል።
" ይህን አለማድረግ ግን ሥርዓት አልበኝነትን መጋበዝ፣ ለሕገወጥ ተግባራት ሽፋን መስጠት ብሎም ድጋፍ በማድረግ ቡራኬ እንደመስጠት እንቆጥራለን " ሲል ገልጿል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጉዳዩን ተመልክቶ የሚመለከተውን አካል ተጠያቂ እንዲያደርግም ፓርቲው በመግለጫው ጥሪ አቅርቧል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@thikvahethiopia
THIKVAH-ETHIOPIA
“የባለስልጣናት ያልተገሩ ንግግሮችና የመንግስትም ተቀዳሚ ተግባሩን ፍጹም መርሳት ሕዝብን ለእልቂት እየዳረገ ነው”- ፓርቲው እናት ፓርቲ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ባወጣውና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ፣ “መልኩንና ቦታውን እየቀያየረ መላ ኢትዮጵያውያንን የደኅንነት ዋስትና ያሳጣው ሀገራዊ እልቂት አሁን አሁን ወደ ሀገራዊ ቀውስነት እያደገ ነው ለማለት ያስደፍራል” ሲል ተችቷል። አክሎ፣ “ለዚህ…
#Update
በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ በተፈጠረው ችግር የተፈናቀሉና ቤት ንብረታቸው ለተቃጠለባቸው ሰዎች ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ፣ በጥቃቱ የተሳተፉት አካላትም ለሕግ እንዲቀርቡ እናት ፓርቲ አሳሰበ።
ወደ 10 ሺሕ ወገኖችን የከፋ ዞን በቀናነት ተቀብሎ እንዳስጠለለና የተወሰኑት ወደ ቄያቸው እየተመለሱ እንደሆነ መገንዘቡን፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለሱን ተግባር በመልካሙ እንደተረዳው፣ ይሁን እንጂ አሁንም ትኩረት የሚሹ ወገኖች እንዳሉ በላከንልን መግለጫ ገልጿል።
“ በአንጻሩ ቤት፣ ንብረት የተቃጠለባቸው በትምህርት ቤቶች ተጠልለው ስለሚገኙ፣ አሁንም አላስፈላጊ ወከባዎችና ‘ያላስረከባችሁት መሣሪያ አለ አምጡ’ በሚል ማንነት ተኮር ማሳደድ እየደረሰ እንደሚገኝ” አስረድቷል።
“እንዲያውም የተወሰኑ ሰዎች ተመልሰው ለመፈናቀል እየተዳረጉ መሆኑን፣ በግድያና ማቃጠል የተሳተፉ በውል ተጣርቶ ለፍርድ አለመቅረባቸውና ፍትህ አለመስፈኑ ችግር እንደፈጠረ፣ ሕዝቡ ሀብትና ንብረቱን ስላጣ ለረሃብ እንደተጋለጠ ለመረዳት ችለናል” ነው ያለው።
“ ስለሆነም አሁንም በአቅራቢያ የሚገኘው የመከላከያ ኃይል የማረጋጋቱን ሥራ ወስዶ እንዲሰራና ቤታቸው ተቃጥሎ በድንኳንና ትምህርት ቤት የተጠለሉ ወገኖቻችን በአፋጣኝ የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች በአጽንዖት እንጠይቃለን ” ሲል አሳስቧል።
የተፈጠረውን “ሞትና ከፍተኛ የንብረት ውድመት” ያስከተለ፣ “እጅግ አስከፊ ማንነት ተኮር ጥቃት” በማውገዝ የመከላከያ ኃይል ቦታውን እንዲቆጣጠረው፣ ተፈናቃዮች ወደ የቄያቸው እንዲመለሱ፣ “ወደ እልቂት የሚመሩ የባለስልጣናት ያልተገሩ ንግግሮች እንዲታረሙ” ከዚህ ቀደም ማሳሰቡን ፓርቲው አስታውሷል።
(የፓርቲው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@thikvahethiopia
በጅማ ዞን ጌራ ወረዳ በተፈጠረው ችግር የተፈናቀሉና ቤት ንብረታቸው ለተቃጠለባቸው ሰዎች ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ፣ በጥቃቱ የተሳተፉት አካላትም ለሕግ እንዲቀርቡ እናት ፓርቲ አሳሰበ።
ወደ 10 ሺሕ ወገኖችን የከፋ ዞን በቀናነት ተቀብሎ እንዳስጠለለና የተወሰኑት ወደ ቄያቸው እየተመለሱ እንደሆነ መገንዘቡን፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለሱን ተግባር በመልካሙ እንደተረዳው፣ ይሁን እንጂ አሁንም ትኩረት የሚሹ ወገኖች እንዳሉ በላከንልን መግለጫ ገልጿል።
“ በአንጻሩ ቤት፣ ንብረት የተቃጠለባቸው በትምህርት ቤቶች ተጠልለው ስለሚገኙ፣ አሁንም አላስፈላጊ ወከባዎችና ‘ያላስረከባችሁት መሣሪያ አለ አምጡ’ በሚል ማንነት ተኮር ማሳደድ እየደረሰ እንደሚገኝ” አስረድቷል።
“እንዲያውም የተወሰኑ ሰዎች ተመልሰው ለመፈናቀል እየተዳረጉ መሆኑን፣ በግድያና ማቃጠል የተሳተፉ በውል ተጣርቶ ለፍርድ አለመቅረባቸውና ፍትህ አለመስፈኑ ችግር እንደፈጠረ፣ ሕዝቡ ሀብትና ንብረቱን ስላጣ ለረሃብ እንደተጋለጠ ለመረዳት ችለናል” ነው ያለው።
“ ስለሆነም አሁንም በአቅራቢያ የሚገኘው የመከላከያ ኃይል የማረጋጋቱን ሥራ ወስዶ እንዲሰራና ቤታቸው ተቃጥሎ በድንኳንና ትምህርት ቤት የተጠለሉ ወገኖቻችን በአፋጣኝ የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች በአጽንዖት እንጠይቃለን ” ሲል አሳስቧል።
የተፈጠረውን “ሞትና ከፍተኛ የንብረት ውድመት” ያስከተለ፣ “እጅግ አስከፊ ማንነት ተኮር ጥቃት” በማውገዝ የመከላከያ ኃይል ቦታውን እንዲቆጣጠረው፣ ተፈናቃዮች ወደ የቄያቸው እንዲመለሱ፣ “ወደ እልቂት የሚመሩ የባለስልጣናት ያልተገሩ ንግግሮች እንዲታረሙ” ከዚህ ቀደም ማሳሰቡን ፓርቲው አስታውሷል።
(የፓርቲው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@thikvahethiopia
#MPESASafaricom
🪄 ዳታው በርክቷል! ወርሃዊ የዳታ ጥቅሎችን እየገዛን እስከ 25% የበለጠ ዳታ አግኝተን በየሄድንበት በፈጣኑ ኢንተርኔት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
🪄 ዳታው በርክቷል! ወርሃዊ የዳታ ጥቅሎችን እየገዛን እስከ 25% የበለጠ ዳታ አግኝተን በየሄድንበት በፈጣኑ ኢንተርኔት ፈታ እንበል! 🥳
M-PESA ላይ ስንገዛ ሁሉም ቅናሽ አላቸው!
በልዩ ልዩ አማራጮች የቀረበልንን የሳፋሪኮም የኢንተርኔት ጥቅል የM-PESA Appን በመጠቀም አሁኑኑ እንግዛ! በአስተማማኙ ኔትወርክ ዳታ እንንበሽበሽ!
#1wedefit
#Furtheraheadtogether
THIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው " - የወላጆች ኮሚቴ ሰርተው ለመለወጥ በሚል ከኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች በማይናማር በአጋቾች የከፋ ስቃይ እያሳለፉ በመሆኑ መንግስት ከስቃይ እንዲታደጋቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ አይዘነጋም። የወላጆች ኮሚቴ፣ ኢትዮጵያዊያኑ በታገቱበት የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ አጋቾች ልጆቹን ዶላር ማጭበርበር…
#Update
🔴 “ መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ ከእገታው የወጡት ኢትዮጵያዊያንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል ” - ቤተሰብ
🔵 “ እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም? ” - ኢትዮጵያዊ በታይላንድ
➡️ “ ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው ” - የወላጆች ኮሚቴ
ሰርተው ለመለወጥ ሲሉ ተታለው ወደ ታይላንድ የተሰደዱና በታጣቂዎች በማይናማር ታግተው ቆይተው የወጡና አሁንም በእገታ ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስት እንዲደርስላቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል።
በሺዎች ከሚቆጠሩት ኢትዮጵያዊያን ታጋቾች ውስጥ 13ዐ የሚሆኑት ከሳምንታት በፊት ከእገታ እንደተለቀቁ፣ ሌሎች በርካቶች ደግሞ ገና ከእገታው እንዳልወጡ፣ የወጡትም ሆኑ ያልወጡት የመንግስትን ድጋፍ እየተጠባበቁ መሆኑን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።
በታይላንድ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ አሁንስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ ከመግደል ያላነሰ ድብድባ ነው የሚካሄደውኮ። እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታይላንድ በረራ እንዳለው እያየን ነው። እሺ ገበያውም አይዘጋበት ቢያንስ ሰው ይዞ ወደ ታይላንድ መጥቶ ሲመለስ የተወሰኑ ሰዎችን እየቀላቀለ ቢመልሰን ማቃለል አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኛ አይደለም እንዴ ? ለሥራ ብለን ነው የመጣነዎኮ ስለተቸገርን ገንዘብ ለማግኘት። ገንዘብ ይዘን ደግሞ ወደ ሀገራችን ለመመለስ።
‘መንግስት አላችሁ?’ ተብለን እስከምንጠየቅ መድረሳችን በጣም ያሳፍራል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሌላ አገር ‘ገንዘብ ረዳሁ’ ብሎ ከሚያወራ እዚህ ያሉትን ዜጓቹን አያስወጣም እንዴ ?
እኛስ መቼም ምግብ ባይቀርብልም ከነበርንበት ሁኔታ አንጻር ምንም አይመስለንም። ትኩረት የሚሹት በማይናማር ከእገታ ያልወጡት እኛ ባለን መረጃ ብቻ እንኳ ከ400 በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያዊያን ነው። እነርሱ የሚወጡት ደግሞ እኛ ቦታውን ስንለቅላቸው ነው።
እኛ ማይናማር ቦርደር ላይ ነው ያለነው። ሞኤ የሚባል ወንዝ እንደተሻገን። በጣም ሐበሻዎች አሉ። ከአንድ ካምፓኒ ብቻ እስከ 500 የሚደርሱ ሐበሻዎች አሉ።
አብዛኛው ኢትዮጵያ ያለበት አንዱ ካምፓኒ ‘ወደ ሌላ ቦታ እንስዳችኋለሁ’ እያለን ነው። ሌላ ቦታ የሚወስደን ሁሉንም ነገሮች ቁጥጥሩ ለማድረግ ነው። አሁን ያለንበት ቦታ ላይ ደኀንነታችን የተጠበቀ ነው።
ማይናማር ግን ብዙ ሰው እየተጎዳ፣ እየተሰቃዬ ያለበት ፎረይን ፓሊሶች የሌሉበት አካባቢ ነው። ያለንበትን ካምፓኒ አቋርጠን ለመውጣት 2,500 ዶላር ይከፈላል። ያለንበት ግቢ እስከ 25 ካምፓኒዎች አሉ። ወደ ሌላ ግቢ ላለመሄድ ነው ጥረት እያደረግን ያለነው።
ሐበሾችን እየጠበቅን ነው ገና ከእገታ ያልወጡ ስላሉ። አመት ድረስ የቆዩ አሉ። በራሳችን ፈቃድ ስለማያስወጡን።
እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ ያልመጣንበት ዋነኛው ምክንያት ሙሉ ወጪ መሸፈን ስላማይችል ነው።
ምክንያቱም ወደ ኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልከው ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኙ ነው መረጃ የሰጡን። የታይላንድ መንግስት ለኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልኳል። ግን እስከ ሳምንት ምላሽ አልተሰጠም።
ካለንበት ካምፕ ወጥተን ወደ ታይላንድ/ሜኢሶት ኤርፓርት ነው መሄድ ያለብን። ከታይላንድ መንግስት ጋር በመነጋገር ወንዝ ያሻግሩናል። ፓስፓርት የሌለው አንድ ወር መቆየት እንደሚችል ነው የተነገረው።
የተጎዱ ሀበሿች፣ ጀርባቸው ላይ ለምጥ ያለ፣ የታመሙ፣ የተደበደቡ በሙሉ ካምፕ ነው ያሉት። እኛን ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ነው ያልጠየቁን እንጂ ህንዶችን፣ ቻይናዎችን ‘አለንላችሁ’ የሚሉ አሉ።
ምን እያደረጉ እንደሆነ የምናውቀው ነገር የለም። የምናውቀው ዘገባ እያደረጉና ዜግነታችንን ለይተው ብዙ ነገር እየጠየቁ እንደሆነ ነው።
የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው የቀሩት። ከኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ ስላላገኙ። ምላሽ ቢያገኙ ይወጡ ነበር የሚቆዩበት ምክንያት የለም። ለኛም ስጋት የሆነው እነርሱ ባለመሄዳቸው የተነሳ ምናልባት የታይላንድ መንግስት ላይቀበለን ይችላል ” ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያዊያኑ ቤተሰቦችስ በሰጡን ቃል ምን አሉ ?
“ ከእገታው ያልወጡ ኢትዮጵያዋያን ስቃይ ላይ ናቸው። ከእገታ ከወጡት 261 ዜጎች 138 ኢትዮጵያዊያ ናቸው። ከማይናማር ተነስተው ታክ በሚባል ካምፕ ነው ያሉት፤ ከቦርደሩ 82፣ ለባንኮክ 377 ኪሎ ሜትር ርቀት።
ቦታው አሁን ለደኀንነታቸው አስተማማኝ እየሆነ አይደለም። ምክንያቱም ከወጡት 261 የ18 ሀገራት ዜጎች በስምንት ቀናት ሁሉም ወደ ሀገራቸው ሂደዋል። የቀሩት የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው።
ከእገታው እንደወጡ ኢንተርቪው ተደገው ነበር በዛው አካባቢው አካላት፣ የደረሰባቸውን ስቃይ ተናግረው ነበር። ቃለመጠይቁን የሰሙ የታይላንድ ፓሊሶችም መልሰው ወስደዋቸዋል። መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ የወጡት ኢትዮጵያዊንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል። የተመለሰ የለም።
የሌሎቹ ሀገሪት ዜጎችም ኢንተርቪው ተደርገው የነበር፤ ነገር ግን ኤምባሲዎች ሂደው በቀናት ውስጥ ነው የወሰዷቸው። 138ቱ ኢትዮጵያዊን ከእገታው ቢወጡም ወደ ኢትዮጵያ ስላልወጡ አደጋ ላይ ናቸው።
በታይላንድ ካምፕ ላይ ያሉት 138፣ በሌላ ጉዳይ ምክንያት በታይላንድ ፓሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ፣ ገና ቦርደር ላይ እየጠበበቁ ያሉ 100 በአጠቃላይ 259 ኢትዮጵያዊያን ስም ዝርዝራቸው እንደተላከለት ውጪ ጉዳይ ነግሮናል።
በስም ዝርዝራቸው መሠረት መረጃዎችን እያደራጀ እንደሆነ ቢገልጽልንም እስካሁን ድረስ ግን ምንም አይነት ተጨባጭ የሆነ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የተሰራ ነገር የለም።
የወጡት ኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ መንግስት የሚጠብቁት ምን እንደሆነ፥ የአገልግሎት ጊዜው ያለቀ ፓርፓርት ያላቸው ልጆች ስላሉ ማንንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ወደ ታይላንድ መንግስት እንዲልክላቸው፣ የበረራ ትኬቶች እንዲስተካክልላቸው ነው” ብለዋል።
የወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ ፦
“ የታይላንድ መንግስት ‘ዜጎቻችሁን ውሰዱ’ ካለ በኋላ ብዙ ሀገራት ልጆቻቸውን አስወጥተዋል። የኢትዮጵያ ልጆች ግን እየተሰቃዩ ነው ያሉት።
የተወሰኑት አምልጠው ሲወጡ ተከትለው ለወጣት የምከሩ ኢትዮጵያዊያን ማይናማር በወታደሮች ካምፕ ታጉረዋል። ከእገታ የወጡት ወደ ሀገቸው ስላልመጡ ሌሎች ያልወጡት ታጋቾችም እየተሰቃዩ ነው።
አሁንም ወታደራዊ ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ ብቻ ናቸው። ምግብም እየተሰጣቸው አይደለም። ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው። ልጆቹ ያልወጡበት ምክንያት ያገራችን መንግስት ባለመቀበሉ ብቻ ነው” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን ከእገታ የማጡት ኢትዮጵያዊንን በአፋጣኝ ማምጣትና የታገቱትን ወገኖች ለማስለቀቅ ለምን እንዳልተቻለ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥያቄ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አላገኘም።
#ThikvahEthiopiaFamilyAA
@thikvahethiopia
🔴 “ መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ ከእገታው የወጡት ኢትዮጵያዊያንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል ” - ቤተሰብ
🔵 “ እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም? ” - ኢትዮጵያዊ በታይላንድ
➡️ “ ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው ” - የወላጆች ኮሚቴ
ሰርተው ለመለወጥ ሲሉ ተታለው ወደ ታይላንድ የተሰደዱና በታጣቂዎች በማይናማር ታግተው ቆይተው የወጡና አሁንም በእገታ ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስት እንዲደርስላቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል።
በሺዎች ከሚቆጠሩት ኢትዮጵያዊያን ታጋቾች ውስጥ 13ዐ የሚሆኑት ከሳምንታት በፊት ከእገታ እንደተለቀቁ፣ ሌሎች በርካቶች ደግሞ ገና ከእገታው እንዳልወጡ፣ የወጡትም ሆኑ ያልወጡት የመንግስትን ድጋፍ እየተጠባበቁ መሆኑን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።
በታይላንድ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ አሁንስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ ከመግደል ያላነሰ ድብድባ ነው የሚካሄደውኮ። እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታይላንድ በረራ እንዳለው እያየን ነው። እሺ ገበያውም አይዘጋበት ቢያንስ ሰው ይዞ ወደ ታይላንድ መጥቶ ሲመለስ የተወሰኑ ሰዎችን እየቀላቀለ ቢመልሰን ማቃለል አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኛ አይደለም እንዴ ? ለሥራ ብለን ነው የመጣነዎኮ ስለተቸገርን ገንዘብ ለማግኘት። ገንዘብ ይዘን ደግሞ ወደ ሀገራችን ለመመለስ።
‘መንግስት አላችሁ?’ ተብለን እስከምንጠየቅ መድረሳችን በጣም ያሳፍራል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሌላ አገር ‘ገንዘብ ረዳሁ’ ብሎ ከሚያወራ እዚህ ያሉትን ዜጓቹን አያስወጣም እንዴ ?
እኛስ መቼም ምግብ ባይቀርብልም ከነበርንበት ሁኔታ አንጻር ምንም አይመስለንም። ትኩረት የሚሹት በማይናማር ከእገታ ያልወጡት እኛ ባለን መረጃ ብቻ እንኳ ከ400 በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያዊያን ነው። እነርሱ የሚወጡት ደግሞ እኛ ቦታውን ስንለቅላቸው ነው።
እኛ ማይናማር ቦርደር ላይ ነው ያለነው። ሞኤ የሚባል ወንዝ እንደተሻገን። በጣም ሐበሻዎች አሉ። ከአንድ ካምፓኒ ብቻ እስከ 500 የሚደርሱ ሐበሻዎች አሉ።
አብዛኛው ኢትዮጵያ ያለበት አንዱ ካምፓኒ ‘ወደ ሌላ ቦታ እንስዳችኋለሁ’ እያለን ነው። ሌላ ቦታ የሚወስደን ሁሉንም ነገሮች ቁጥጥሩ ለማድረግ ነው። አሁን ያለንበት ቦታ ላይ ደኀንነታችን የተጠበቀ ነው።
ማይናማር ግን ብዙ ሰው እየተጎዳ፣ እየተሰቃዬ ያለበት ፎረይን ፓሊሶች የሌሉበት አካባቢ ነው። ያለንበትን ካምፓኒ አቋርጠን ለመውጣት 2,500 ዶላር ይከፈላል። ያለንበት ግቢ እስከ 25 ካምፓኒዎች አሉ። ወደ ሌላ ግቢ ላለመሄድ ነው ጥረት እያደረግን ያለነው።
ሐበሾችን እየጠበቅን ነው ገና ከእገታ ያልወጡ ስላሉ። አመት ድረስ የቆዩ አሉ። በራሳችን ፈቃድ ስለማያስወጡን።
እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ ያልመጣንበት ዋነኛው ምክንያት ሙሉ ወጪ መሸፈን ስላማይችል ነው።
ምክንያቱም ወደ ኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልከው ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኙ ነው መረጃ የሰጡን። የታይላንድ መንግስት ለኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልኳል። ግን እስከ ሳምንት ምላሽ አልተሰጠም።
ካለንበት ካምፕ ወጥተን ወደ ታይላንድ/ሜኢሶት ኤርፓርት ነው መሄድ ያለብን። ከታይላንድ መንግስት ጋር በመነጋገር ወንዝ ያሻግሩናል። ፓስፓርት የሌለው አንድ ወር መቆየት እንደሚችል ነው የተነገረው።
የተጎዱ ሀበሿች፣ ጀርባቸው ላይ ለምጥ ያለ፣ የታመሙ፣ የተደበደቡ በሙሉ ካምፕ ነው ያሉት። እኛን ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ነው ያልጠየቁን እንጂ ህንዶችን፣ ቻይናዎችን ‘አለንላችሁ’ የሚሉ አሉ።
ምን እያደረጉ እንደሆነ የምናውቀው ነገር የለም። የምናውቀው ዘገባ እያደረጉና ዜግነታችንን ለይተው ብዙ ነገር እየጠየቁ እንደሆነ ነው።
የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው የቀሩት። ከኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ ስላላገኙ። ምላሽ ቢያገኙ ይወጡ ነበር የሚቆዩበት ምክንያት የለም። ለኛም ስጋት የሆነው እነርሱ ባለመሄዳቸው የተነሳ ምናልባት የታይላንድ መንግስት ላይቀበለን ይችላል ” ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያዊያኑ ቤተሰቦችስ በሰጡን ቃል ምን አሉ ?
“ ከእገታው ያልወጡ ኢትዮጵያዋያን ስቃይ ላይ ናቸው። ከእገታ ከወጡት 261 ዜጎች 138 ኢትዮጵያዊያ ናቸው። ከማይናማር ተነስተው ታክ በሚባል ካምፕ ነው ያሉት፤ ከቦርደሩ 82፣ ለባንኮክ 377 ኪሎ ሜትር ርቀት።
ቦታው አሁን ለደኀንነታቸው አስተማማኝ እየሆነ አይደለም። ምክንያቱም ከወጡት 261 የ18 ሀገራት ዜጎች በስምንት ቀናት ሁሉም ወደ ሀገራቸው ሂደዋል። የቀሩት የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው።
ከእገታው እንደወጡ ኢንተርቪው ተደገው ነበር በዛው አካባቢው አካላት፣ የደረሰባቸውን ስቃይ ተናግረው ነበር። ቃለመጠይቁን የሰሙ የታይላንድ ፓሊሶችም መልሰው ወስደዋቸዋል። መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ የወጡት ኢትዮጵያዊንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል። የተመለሰ የለም።
የሌሎቹ ሀገሪት ዜጎችም ኢንተርቪው ተደርገው የነበር፤ ነገር ግን ኤምባሲዎች ሂደው በቀናት ውስጥ ነው የወሰዷቸው። 138ቱ ኢትዮጵያዊን ከእገታው ቢወጡም ወደ ኢትዮጵያ ስላልወጡ አደጋ ላይ ናቸው።
በታይላንድ ካምፕ ላይ ያሉት 138፣ በሌላ ጉዳይ ምክንያት በታይላንድ ፓሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ፣ ገና ቦርደር ላይ እየጠበበቁ ያሉ 100 በአጠቃላይ 259 ኢትዮጵያዊያን ስም ዝርዝራቸው እንደተላከለት ውጪ ጉዳይ ነግሮናል።
በስም ዝርዝራቸው መሠረት መረጃዎችን እያደራጀ እንደሆነ ቢገልጽልንም እስካሁን ድረስ ግን ምንም አይነት ተጨባጭ የሆነ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የተሰራ ነገር የለም።
የወጡት ኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ መንግስት የሚጠብቁት ምን እንደሆነ፥ የአገልግሎት ጊዜው ያለቀ ፓርፓርት ያላቸው ልጆች ስላሉ ማንንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ወደ ታይላንድ መንግስት እንዲልክላቸው፣ የበረራ ትኬቶች እንዲስተካክልላቸው ነው” ብለዋል።
የወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ ፦
“ የታይላንድ መንግስት ‘ዜጎቻችሁን ውሰዱ’ ካለ በኋላ ብዙ ሀገራት ልጆቻቸውን አስወጥተዋል። የኢትዮጵያ ልጆች ግን እየተሰቃዩ ነው ያሉት።
የተወሰኑት አምልጠው ሲወጡ ተከትለው ለወጣት የምከሩ ኢትዮጵያዊያን ማይናማር በወታደሮች ካምፕ ታጉረዋል። ከእገታ የወጡት ወደ ሀገቸው ስላልመጡ ሌሎች ያልወጡት ታጋቾችም እየተሰቃዩ ነው።
አሁንም ወታደራዊ ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ ብቻ ናቸው። ምግብም እየተሰጣቸው አይደለም። ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው። ልጆቹ ያልወጡበት ምክንያት ያገራችን መንግስት ባለመቀበሉ ብቻ ነው” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን ከእገታ የማጡት ኢትዮጵያዊንን በአፋጣኝ ማምጣትና የታገቱትን ወገኖች ለማስለቀቅ ለምን እንዳልተቻለ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥያቄ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አላገኘም።
#ThikvahEthiopiaFamilyAA
@thikvahethiopia
" ሞባይል ስልክ ይዞ ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባት በጥብቅ ተከልክሏል " - የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት
አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ መከልከሉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታወቀ።
ሀገረ ስብከቱ የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎችና ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ቄሰ ገበዞች ጋር ውይይት አድርጓል።
ውይይትቱን ተከትሎ ስምምነት ላይ በመደረሱ የተለያዩ መመሪያዎች ተላልፈዋል።
ከመመሪያዎች አንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከተለ መሆኑ ነው።
ይህም ጥብቅ ክልከላ ለሁሉም ገዳማትና አድባራት እንዲያውቁት የመመሪያ ደብዳቤ ተልኳል።
ሀገረ ስብከቱ ፤ " በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት መሠረት ቅዳሴ የሁሉም ጸሎታት ማጠናቀቂያ ፣ ቀራንዮ ላይ ምንገኝበት፣ የበጉ ሠርግ ላይ የምንታደምበት፣ የጌታችንን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በአንድነት ለሓጢአት ሥርየት፣ ለነፍስ ሕይወት፣ ለሃይማኖት ጽንዐትና ለመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ይሆነን ዘንድ የምቀበልበት ታላቅ የጸሎት ሰዓት ነው " ብሏል።
በመሆኑም " አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም ጎልጎታን ከሚያስረሱ ፣በረከትን ከሚያሳጡና ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ ተከልክሏል " ሲል ገልጿል።
መመሪያውን የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ ታዘዋል።
@thikvahethiopia
አገልጋዮች በቅዳሴና ለሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎት ሰዓት ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ መከልከሉን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስታወቀ።
ሀገረ ስብከቱ የዐቢይ ጾምን አስመልክቶ አገልግሎቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት ከሁሉም ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎችና ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ቄሰ ገበዞች ጋር ውይይት አድርጓል።
ውይይትቱን ተከትሎ ስምምነት ላይ በመደረሱ የተለያዩ መመሪያዎች ተላልፈዋል።
ከመመሪያዎች አንዱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚከናወኑ የጸሎተ ቅዳሴና ሌሎች መንፈሳዊ አገልግሎቶች የእጅ ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከተለ መሆኑ ነው።
ይህም ጥብቅ ክልከላ ለሁሉም ገዳማትና አድባራት እንዲያውቁት የመመሪያ ደብዳቤ ተልኳል።
ሀገረ ስብከቱ ፤ " በኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዓት መሠረት ቅዳሴ የሁሉም ጸሎታት ማጠናቀቂያ ፣ ቀራንዮ ላይ ምንገኝበት፣ የበጉ ሠርግ ላይ የምንታደምበት፣ የጌታችንን የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በአንድነት ለሓጢአት ሥርየት፣ ለነፍስ ሕይወት፣ ለሃይማኖት ጽንዐትና ለመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ይሆነን ዘንድ የምቀበልበት ታላቅ የጸሎት ሰዓት ነው " ብሏል።
በመሆኑም " አላስፈላጊ የእጅ ስልክ አጠቃቀም ጎልጎታን ከሚያስረሱ ፣በረከትን ከሚያሳጡና ጸጋን ከሚያስወስዱ ድርጊቶች መካከል አንዱ በመሆኑ ተከልክሏል " ሲል ገልጿል።
መመሪያውን የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉባኤያት ጥብቅ ክትትል በማድረግ እንዲያስፈጽሙ ታዘዋል።
@thikvahethiopia
“ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939 ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር ” - ኮሚሽኑ
ዛሬ አዲስ አበባ ፤ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ወረዳ 2 በተለምዶ ካሬ ቆሬ ብቄላ መናፈሻ አካባቢ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በሰው ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡን ቃል፣ “ እሳቱ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
“ የፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ (ቁርጥራጭ ጨርቅ) የመሳሰሉ ግብዓቶች መጋዘን ላይ ነው የእሳት አደጋው ያጋጠመው ” ያሉት አቶ ንጋቱ፣ የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ ህብረተሰቡ ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ መስጊድና መኖሪያ ቤት ሳይዛመት መቆጣጠር መቻሉን አስረድተዋል።
“ በእሳት አደጋው ሰው ላይ ጉዳት አልደሰም። የቀረው መረጃ በኢኮኖሚ ላይ የደረሰው ጉዳትና የአደጋ መንስኤ ነው። እሱን ከፓሊሶች ጋር ሆነን እያጣራን ነው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የእሳት አደጋ እየተደጋገመ ያለበት ሁኔታ እየተስተዋለ ነው፤ ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ስንል ሳቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ ንጋቱ፣ “ ትክክል ነው እሳት አደጋ የተደጋገመመበት ሁኔታ አለ። አሁን ያለንበት ወቅት ነፋሻማና ደረቅ አየር ነው ” የሚል ምላሽ ስጥተዋል።
“ እሳት እንዲከሰት ከሚያደርጉ ሦስት መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ ሁለቱን አሁን ካለው የአየር ፀባይ እናገኛለንና መዘናጋትና ቸልተኝነት ዋጋ የሚያስከፍልበት ሂደት ስላለ ህብረተሰቡ በመኖሪያ፣ በስራ አካባቢ እሳትና የኤለክትሪክ ኃይል ምንጮችን ሲጠቀም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ አክለዋል።
“ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ያድርግ። ከዚህ አልፎ ለሚያጋጥም አደጋ፥ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939ኝን ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር” ሲሉ አሳስበዋል።
#ThikvahEthiopiaFamilyAA
@thikvahethiopia
ዛሬ አዲስ አበባ ፤ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ወረዳ 2 በተለምዶ ካሬ ቆሬ ብቄላ መናፈሻ አካባቢ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በሰው ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡን ቃል፣ “ እሳቱ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
“ የፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ (ቁርጥራጭ ጨርቅ) የመሳሰሉ ግብዓቶች መጋዘን ላይ ነው የእሳት አደጋው ያጋጠመው ” ያሉት አቶ ንጋቱ፣ የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ ህብረተሰቡ ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ መስጊድና መኖሪያ ቤት ሳይዛመት መቆጣጠር መቻሉን አስረድተዋል።
“ በእሳት አደጋው ሰው ላይ ጉዳት አልደሰም። የቀረው መረጃ በኢኮኖሚ ላይ የደረሰው ጉዳትና የአደጋ መንስኤ ነው። እሱን ከፓሊሶች ጋር ሆነን እያጣራን ነው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የእሳት አደጋ እየተደጋገመ ያለበት ሁኔታ እየተስተዋለ ነው፤ ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ስንል ሳቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ ንጋቱ፣ “ ትክክል ነው እሳት አደጋ የተደጋገመመበት ሁኔታ አለ። አሁን ያለንበት ወቅት ነፋሻማና ደረቅ አየር ነው ” የሚል ምላሽ ስጥተዋል።
“ እሳት እንዲከሰት ከሚያደርጉ ሦስት መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ ሁለቱን አሁን ካለው የአየር ፀባይ እናገኛለንና መዘናጋትና ቸልተኝነት ዋጋ የሚያስከፍልበት ሂደት ስላለ ህብረተሰቡ በመኖሪያ፣ በስራ አካባቢ እሳትና የኤለክትሪክ ኃይል ምንጮችን ሲጠቀም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ አክለዋል።
“ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ያድርግ። ከዚህ አልፎ ለሚያጋጥም አደጋ፥ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939ኝን ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር” ሲሉ አሳስበዋል።
#ThikvahEthiopiaFamilyAA
@thikvahethiopia