THIKVAH-ETHIOPIA
3.96K subscribers
6.6K photos
218 videos
39 files
721 links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Peace🏳

ሃማስ እና እስራኤል የተኩስ አቁም ለማድረግ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነገረ።

ሀማስ የስምምነት ፕሮፖዛሉን መቀበሉን በይፋ ሲያሳውቅ የእስራኤልም ይፋ ታደርጋለች ተብሎ እየተጠበቀ ይገኛል።

ሁለቱ አካላት ወደ ስምምነት እንዲመጡ አሜሪካ፣ ኳታር እና ግብፅ ለበርካታ ሳምንታት ሲሰሩ ነበር ተብሏል።

እንደ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ በመጀመሪያው ዙር ለ6 ሳምንታት ይቆያል።

ሃማስ 33 ታጋቾችን ለመልቀቅ እስራኤል ደግሞ 1,000 የሚጠጉ ፍልስጤማውያን ለመልቀቅ መስማማቷ በስፋት እየተነገረ ነው።

' አል አረቢያ ' አንድ ስማቸው ያልተገለጸ የእስራኤል ባለስልጣንን ዋቢ ለማድረግ ሀማስ ለተኩስ አቁም እና ታጋቾችን ለመልቀቅ መስማማቱን ፅፏል።

' አልጀዚራ ' ደግሞ እስራኤል ከስምምነቱ ጋር በተያያዘ አንዳንድ ያልተፈቱና ያላለቁ ጉዳዮች እንዳሉ በመጠቆም የመጨረሻው ማጠቃለያና መፍትሄ በቀጣይ ሰዓታት ውስጥ እንደሚገኝ ዘግቧል።

ስምምነቱን የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ያፀድቁታል ተብሎ ይጠበቃል። የእስራኤል መንግስት ነገ ድምጽ ይሰጣል።

ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ትሩዝ በተባለው የማህበራዊ ሚዲያቸው ላይ " ስምምነት ላይ ተደርሷል ሀማስም ታጋቾችን ለመልቀቅ ተስማምቷል ፤ ታጋቾች በአጭር ጊዜ ነጻ ይሆናሉ " ብለዋል።

የሁለቱ ወገኖች ስምምነት ለ15 ወራት የዘለቀውን እጅግ በጣም አስከፊ ጦርነት ያስቆማል ተብሎ ትልቅ ተስፋ ተጥሏል።

የስምምነቱን መረጃን የሰሙ ፍልስጤማውያን ጋዛ ውስጥ እያነቡ አደባባይ ወጥተው ደስታቸውን እየገለጹ ነው።

ይህ ስምምነት እየተካሄደ በነበረበት ወቅት እስራኤል ጋዛ ቡሬጂ የስደተኞ ካምፕ ላይ በፈጸመችው ጥቃት በርካታ ፍልስጤማውያንን ገድላለች።

ባለፉት 15 ወራት በነበረው እጅግ አስከፊ ጦርነት ከ46 ሺህ በላይ ፍልስጤማውያን ሲገደሉ 1,200 እስራኤላውያን ተገድለዋል 250 ታግተው ተወስደዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከአልጀዚራ፣ አል አረቢያ፣ ፍራንስ 24 ነው ያሰባሰበው።

@thikvahethiopia
THIKVAH-ETHIOPIA
#Peace🏳 ሃማስ እና እስራኤል የተኩስ አቁም ለማድረግ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነገረ። ሀማስ የስምምነት ፕሮፖዛሉን መቀበሉን በይፋ ሲያሳውቅ የእስራኤልም ይፋ ታደርጋለች ተብሎ እየተጠበቀ ይገኛል። ሁለቱ አካላት ወደ ስምምነት እንዲመጡ አሜሪካ፣ ኳታር እና ግብፅ ለበርካታ ሳምንታት ሲሰሩ ነበር ተብሏል። እንደ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱ በመጀመሪያው ዙር ለ6 ሳምንታት ይቆያል።…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ  ፦ #ሀማስ እና #እስራኤል የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማታቸው መነገሩን ተከትሎ ፍልስጤማውያን ደስታቸውን ለመግለፅ በጋዛ አደባባይ ወጥተዋል።

" አላሁ አክበር ! አላሁ አክበር ! " ይህ በስምምነቱ መረጃ የተደሰቱ ፍልስጤማውያን ድምፅ ነው።

በርካቶች የሰላም ወሬ በመንፈሱ በደስታ አልቅሰዋል ፤ አንብተዋል ፤ ፈጣሪ ቀጣዩን ጊዜ ደግሞ የሰላም ያደርግላቸው ዘንድ ተማፅነዋል።

ፍልስጤማውያን ስምምነቱን ተከትሎ እስራኤል የያዘቻቸውን ያሰረቻቸውን ወገኖቻቸውን ትፈታለች ብለው ተስፋ አድርገዋል።

በአስከፊው ጦርነት እጅግ በርካታ ፍልጤማውያን ህጻናት፣ ሴቶች፣ እናቶች ፣ አዛውንቶች አልቀዋል። ላለፉት 15 ወራት የሰቀቀን ህይወት ሲገፉም ነበር።

ስምምነቱ ዘላቂ እና አስተማማኝ ሰላምን ያመጣ ይሆን ? በቀጣይ የሚታይ ይሆናል።

#ሰላም 😭 #Peace 🕊 #سلام

@thikvahethiopia
📱 ወጋገን ኢ-ብር ለምቹ እና ቀልጣፋ ክፍያ !

በወጋገን ኢ-ብር ሞባይል ዋሌት አገልግሎት በመጠቀም የሞባይል አየር ሰዓት መሙላት፣ የበረራ ትኬት መቁረጥ፣ የውሃ አገልግሎት ክፍያ ፣የትምህርት ቤት ክፍያ፣ ትራንስፖርትን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶች ክፍያ በምቾት እና ደህንነቱ በተጠበቀ መንገድ መፈፀም ይችላሉ፡፡

🔶 ወጋገን ኢ-ብር ፈጣን፣ ቀላል እና አስተማማኝ የክፍያ አማራጭ!

የ ኢ-ብር የሞባይል ዋሌት መተግበሪያውን ከፕሌይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር  በማውረድ ወይም ወደ *602# በመደወል እና ወጋገን ባንክን በመምረጥ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡

🔶  የኢ-ብር መተግበሪያ ለማውረድ👇

ፕሌይ ስቶር   🔶   አፕ ስቶር

ለበለጠ መረጃ ወደ ደንበኞች ግንኙነት ማዕከል በ866 ነፃ የስልክ መስመር ይደውሉ! በተጨማሪም ከስር የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን የማህበራዊ ሚዲያዎቻችንን ይቀላቀሉ https://linktr.ee/WegagenBank

#ወጋገን #ኢብር #ፈጣን #አስተማማኝ #ክፍያ
" የሀገር ሀብትና የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉ የቡና ምርት በቀልጣፋ አገልግሎት እጦት ለጥራት ችግር እየተዳረገብን ነዉ " - የቡና አቅራቢዎች

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርመራና ሰርትፊኬሽን ማዕከል በሀገራች ከፍተኛ ቡና አምራች ከሚባሉ ሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ ሻኪሶ ፣ ቡሌሆራ እና አማሮ አከባቢዎች የሚገኙ ምርቶች የጥራት ልኬት እና ሰርትፊኬሽን አግኝተዉ ቡናን ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚቀርቡበት ማዕከል ነው።

በተለይ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሀዋሳ ከተማ ተቋሙ ከሚገኝበት የቀድሞዉ የደቡብ ክልል ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ግቢ ዙሪያ በአራቱም አቅጣጫ ቡና የጫኑ በርካታ ተሸከርካሪዎችን ማየት የተለመደ ሆኗል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምክንያቱን ለማጣራት ክትትል አድርጓል።

የቡና አቅራቢዎች እና አሽከርካሪዎችን ያነጋገርን ሲሆን ፤ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተቋሙ ባለዉ የወረፋ ብዛትና ተያያዥ ችግሮች ላላስፈላጊ ወጪ መዳረጋቸዉንና አልፎም ለሀገር ትልቅ የገቢ ምንጭ በሆነዉ የቡና ምርት ጥራት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግረዋል።

" ቡና በባህሪው እንደ ሙሽራ እንክብካቤ ይፈልጋል " ያሉን አንድ የቡና ላኪ " በቦታዉ ባለዉ ወረፋ መብዛትና ተገቢነት በለሌዉ የተሽከርካሪ አቋቋም ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረግን ነዉ " ብለዋል።

" በማዕከሉ ዙሪያ ተሰልፈን አምስትና ስድስት ቀናትና አለፍ ሲልም ከዛም በላይ አስር ቀን የመቆየት ሁኔታዎች አሉ " ያሉን ሌላኛዉ አስተያየት ሰጪ የቡና አቅራቢ " ቡና ሳይወጋ በሻራ ዉስጥ ታፍኖ ለረጅም ቀናት ስለሚቆይ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በሚናቀርብበት ወቅት የጥራት ደረጃ መዉረድና በከፍተኛ ሁኔታ የኪሎግራም መቀነስ እያጋጠመን ነዉ " ብለዋል።

" ቀልጣፋ አገልግሎት ባለማግኘታችን በእኛና በተሽከርካሪ ባለቤቶች እንዲሁም በቡና አቅራቢዎች እና ጉዳይ አስፈፃሚዎች መካከል አለመተማመኖች እየተፈጠሩ ነዉ " ያሉን አሽከርካሪዎች " ለፓርኪንግ፣ ምግብ ፣ አልጋ መሰል አላስፈላጊ ወጪዎችን እያወጣን ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ቡና በሀገር ደረጃ ባለዉ ከፍተኛ የገቢ ምንጭነት ልክ ትኩረት አልተሰጠውም " የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ " ፈጣን መፍትሔ ካልተበጀለት ጉዳቱ ከኛ አልፎ አምራች አርሶአደሮች፣ ሰፊ የስራ ዕድል በተፈጠረላቸው ወጣቶችና በሀገር የዉጪ ምንዛሪ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ማሳደሩ አይቀርም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ላይ በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ስሜን አነጋግሯል።

እሳቸውም ፤ የዘንድሮ የቡና ምርት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ቀደም ሲል ከነበረዉ የቦታ ጥበትና ተያያዥ ችግሮች ጋር ተዳምሮ ለአገልግሎት አሰጣጡ ቀልጣፋ አለመሆን ዋነኛ ምክንያት መሆናቸዉን ተናግረዋል።

የችግሩን አሳሳብነትና የቡናን ሀገራዊ ጥቅሙን በመግለፅ ለሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ደብዳቤ መፃፋቸዉንና ምላሽም እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ መልኩ የቡና ምርቶች ወደ ማዕከሉ በሚደርሱበት ወቅት አስፈላጊዉ የእርጥበት መጠን ላይ ሳይደርሱ የሚመጡበት አጋጣሚዎች ስላሉ ተገቢዉ የእርጥበት መጠናቸዉ ላይ እስኪደርሱ ድረስ መወጋትም ሆነ የቅምሻ ልኬት ስለማይደረግላቸዉና ለኮንትሮባንድ እንዳይጋለጡ ሲባል ወደ ኋላ ስለማይመለሱ በማዕከሉ እንዲቆዩ ስለሚደረግ የተሽከርካሪዎች ክምችት እንደሚፋጠርም አስታውቀዋል።

ማዕከሉ ለሲዳማ፣ ለደቡብ ኢትዮጵያና ኦሮሚያ ክልል ቡና አምራች አከባቢዎች አገልግሎት የሚሰጥና የሀገራችንን ዋነኛ የኢኮኖሚ አዉታር የሆነዉን ቡና ለማዕከላዊ ገበያ የሚያቀርብ እንደመሆኑ መጠን በተለይም የሲዳማ ክልል መንግስትና ተጠሪ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተዉ መፍትሔ ቢሰጡ ጥሩ ነው ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬን አነጋግሯል።

" ቡና ለሲዳማ ክልል ልዩ ትርጉም ያለዉ የገቢ ምንጭና የክልሉም መለያም ጭምር ነዉ " ያሉ ሲሆን በ2017 ዓ/ም ብቻ ከክልሉ ከ37 ሺ ቶን በላይ ቡና መሰብሰቡን ገልፀዉ በዘንድሮዉ ሀገር አቀፍ የቡና ቅምሻ ወድድር (ካፕ ኦፍ ኤክሰሌንስ) ከ1ኛ እስከ 39ኛ ድረስ የወጡት የክልሉ አምራች አርሶ አደሮች መሆናቸውን አስታዉቀዋል።

በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የሀዋሳ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፊኬሽን ማዕከል ያለበትን ጫና የክልሉ መንግስት መረዳቱንና በአጭር ጊዜ ዉስጥ አፋጣኝ መፍትሔ ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

#ThikvahEthiopiaFamilyHawassa

@thikvahethiopia
THIKVAH-ETHIOPIA
#ሂጃብሂጃብ #አክሱም " ተከሳሾች የሰጡት አስተዳደራዊ ትእዛዝ መዝገቡ እልባት እስኪያገኝ ወይም ተለዋጭ ትእዛዝ እስኪሰጥበት ድረስ #እንዳይተገበር ለጊዜው በእግድ እንዲቆይ ታዟል " - ፍርድ ቤት በአክሱም ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎችን ሂጃብ ለብሰው ትምህርታቸውን እንዳይከታተሉ ክልከላ አድርገዋል በተባሉት አካላት ላይ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ህጋዊ ክስ…
#Update

🧕" የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ በመጣስ አሁንም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች / ልጆቻችን ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ ከልክሏል "  - የተማሪዎች ቤተሰቦች

👉 " የተጣሰ የፍርድ ቤት የእግድ ትእዛዝ የለም ፤ የትምህርት ህግ እና ደንብ ያከበሩ ተማሪዎች ወደ ክፍል ገብተው መማር ጀምረዋል ፤ ቀሪዎቹ እንዲመለሱ ያላሰለሰ ጥረት በማድረግ ላይ ነን " -  የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር

የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም በፃፈው የእግድ ትእዛዝ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው እንዲማሩ ፤ በክልከላ የተሳተፉ አካላት ለጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ቢያዝም ተግባራዊ አልሆነም ብለዋል የተማሪዎች ቤተሰቦች።

የተማሪ ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ (መቐለ) በሰጡት አስተያየት ፤ " የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር በተያያዘ በአክሱም ከተማ ፍርድ  ቤት በኩል በ5 አካላት ላይ የእግድ ደብዳቤ ቢያፅፍም ተግባራዊ አልሆነም ተጥሷል " ብለዋል። 

የእግድ ትእዛዙን ከጣሱት አንዱ የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መሆኑን የጠቀሱት የተማሪ ቤተሰቦች ፤ " ትምህርት ቤቱ የእግድ ትእዛዙን በመጣስ ጥር 7 እና 8/2017 ዓ.ም ተማሪዎቹ ክፍል ገብተው እንዳይማሩ በማድረግ ተደራራቢ ጥፋቶች እየፈፀመ ነው " ሲሉ ከሰዋል። 

አስተያየት ሰጪዎቹ  " ከህግ በላይ መሆን ልክ አይደለም የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና የሃይማኖት መብት ይከበር " ሲሉ ምሬታቸው ገልፀዋል። 

በተማሪዎች ቤተሰቦች በኩል ለቀረበው አስተያየት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ምላሽ የሰጡት የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ርእሰ መምህር ስዩም ካሕሳይ ፥ " ትምህርት ቤታችን ' የፍርድ ቤት እግድ እና ትእዛዝ በመጣስ ተማሪዎቹ እንዳይማሩ ከልክሏል ' የሚባለው ስህተት ነው " ብለዋል።   

" ለተማሪ ሴት ልጆቻችን በቅርብ እና በሩቅ ሆኖው ' እንቆረቆራለን ' ከሚሉት በላይ እናስብላቸዋለን " ያሉት ርእሰ መምህሩ " አሁንም ጉዳዩ ከሚገባው በላይ ማጋነን እና ማቀጣጠል እንዲሁም ለፓለቲካዊ ፍጆታ ማዋል ለአገር እና ህዝብ አይጠቅምም " ሲሉ አብራርተዋል።  

" የትምህርት ቤታችን አስተዳደር የፍርድ ቤት ትእዛዝ እና እግድ ሳይጠብቅ የተፈጠረው አለመግባባት እንዲፈታ ሌት ተቀን በመስራት ላይ እንገኛለን " ሲሉ ገልጸው " የፍርድ ቤቱ ቃል አክብረን የትምህርት ቤቱ መምሪያ እና ደንብ በመጠበቅ ጥቂት የማይባሉ ሴት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው መልሰናል የተቀሩት ለመመለስ ደግሞ በማያቋርጥ ጥረት ላይ እንገኛለን " ብለዋል።

" ከ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ የቀሩት እንዲካተቱ ከሚመለከታቸው አካላት ተከታታይ ስራዎች እየሰራን " ሲሉ አክለዋል።   

ከሂጃብ መልበስ ጋር ተያይዞ ከ2017 የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ እንዲቀሩ  የሆኑት 159 የአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ጉዳይ ክልላዊ እና አገራዊ አጀንዳ ከመሆን በዘለለ በህግ እንዲታይ ወደ ፍርድ አምርቷል።

ከሂጃብ አጠቃቀም ክልከላ ጋር በተያያዘ ተሳታፊ ናቸው በተባሉት በአክሱም ከተማ የሚገኙ 5 አካላት ለጥር 16/2017 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ቃላቸው እንዲሰጡ ፤ ጎን ለጎን ደግሞ ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ ሂጃባቸው ለብሰው ትምህርታቸው እንዲቀጥሉ የአክሱም ከተማ ፍርድ ቤት ጥር 6/2017 ዓ.ም አዟል።  

የትግራይ ትምህርት ቢሮ ዛሬ ጥር 8/2017 ዓ.ም ለሁለተኛ ጊዜ በፃፈው ደብዳቤ ፤ የሂጃብ መልበስ ክልከላው እንዲያነሳ አሳውቋል።

በተያያዘ መረጃ ከሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ጋር ተያይዞ ወደ ትምህርት ገበታ እንዳይገቡ መከልከሉ ለመቃወም የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለዓርብ ጥር 9/2017 ዓ.ም በመቐለ ከተማ እንዲካሄድ የጠራው እና የተፈቀደ ሰላማዊ ሰልፍ የጥምቀት በዓል ዋዜማ በመሆኑ ምክንያት ወደ ጥር 13/2017 ዓ.ም ማዘዋወሩ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ  ከምክር ቤቱ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

#ThikvahEthiopiaFamilyMekelle

@thikvahethiopia
THIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ጉዳዩ ዓለም አቀፍ የወንጀል ገጽታ ያለው ነው " -  የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር

የታገቱት ኢትዮጵያውያን ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው

" በህገወጥ ዓለምአቀፍ ደላሎች ተታለው ወደ ማይናማር ፣ ታይላንድ፣ ቻይና ድንበር አዋሳኝ አካባቢዎች ወደሚገኙ ህገወጥ ካምፓች ተወስደው የሚገኙ ዜጎችን ለማስመለስ በመንግስት የተጀመሩ ጥረቶች ቀጥለዋል።

ጉዳዩ ዓለም አቀፍ የወንጀል ገጽታ ያለው ነው።

እስካሁን በምናደርገው እንቅስቃሴ የ19 ሀገራት ዜጎች ተመሳሳይ በህገወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ተታለውና ታግተው ወደ ማይናማር በመግባት ለከፋ ችግር የተዳረጉ መሆኑን ለመረዳት ችለናል።

ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ በማይናማር 380 የሚል ቁጥር ተጠቅሷል ይሄ የቁጥር የተወሰደው እዚህ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ ዜጎች ልጆቻቸው ታግተው እዚህ መጥተው ካመለከቱት ነው።

በዚህ መሰረት ክትትል ለማድረግ እንዲረዳን ቶኪዮ ለሚገኘው ኤምባሲያችን የተላለፈው ቁጥር ይህ ነው። ትክክለኛው የታጋቾች ቁጥር አይታወቅም።

ቶኪዮ የሚገኘው ኤምባሲያችን ከማይናማር ኤምባሲ ጋር ዜጎቻችንን ለማዳን በትብብር እየሰራ ነው። የ380 ዜጎች ስም ዝርዝር እና ፓስፖርት ኮፒ ቶኪዮ ለሚገኘው የማይናማር ኤምባሲ እንዲደርስ ተደርጓል።

የማይናማር መንግሥት ታጋቾችን ለመልቀቅ ጠረት በማድረግ ላይ ሲሆን ከአጋቾች አምልጠው ለመንግሥት እጅ የሚሰጡ ዜጎች ምህረት በማድረግ በነጻ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ትብብር በማድረግ ላይ ይገኛል።

ፈታኝ የሆነው ዋናው ጉዳይ የታገቱት ዜጎች የሚገኙት በማይናማር እና ታይላንድ መካከል በሚገኙ ከማይናማር መንግሥት ቁጥጥር ውጭ በሆኑ ስፍራዎች መሆኑ ነው። ይህ ስራውን አክብዶታል።

ሌላው ፤ በዚህ ኢሰብዓዊ ወንጀል ኢትዮጵያውያን እና የውጭ ሀገራት ሰው አዘዋዋሪዎች ተቀራርበው እየሰሩ መሆኑ ነው።

እስካሁን መንግሥት ከዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅቶች ጋር ጭምር ባደረገው ጥረት በ6 ወር ውስጥ 34 ዜጎች ከአጋቾች ነጻ ወጥተው ወደ ታይላንድ እና ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ከአጋቾች አምልጠው ህጋዊ ሰነድ ስለሌላቸው በእስር ቤቶች ታስረው የነበሩ 7 ዜጎቻችንም በምህረት እንዲለቀቁ ማድረግ ተችሏል።

ዜጎችን የመታደጉ ስራ ብዙ ጥረትን የሚጠይቅ በመሆኑ ቶኪዮ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ሚስዮን በተጨማሪ በኒዉዴልሂ የሚገኘው ኤምባሲም ተልዕኮ ተሰጥቶት መንቀሳቀስ ጀምሯል " ብለዋል።

NB. አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ወጣቶች ደህንነቱ ወዳልተጠበቀ ስፍራ እየሄዱ ያሉት ከስራ ቅጥር ጋር ተያያዥ በሆኑ የማተለያ ስልቶች በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል። የችግሩን ምንነት እና አስከፊነት ህብረተሰቡ እንዲያውቅ የማድረጉን ስራ ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

@thikvahethiopia
🎁 ጥምቀት የሞባይል ጥቅል!!

እስከ 20% በሚደርስ ቅናሽ ያቀረብናቸውን ልዩ የበዓል ጥቅሎች በ*999#፣ በማይ ኢትዮቴል እና አርዲ ቻትቦት ይግዙ!

👉 ጥቅሎቹን በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ሲገዙ 20% ቅናሽ ከተጨማሪ 20% ስጦታ ጋር ያገኛሉ!

🗓 ከነገ ጥር 10 – 13/2017 ዓ.ም   

መልካም የጥምቀት በዓል!

#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
ሕብር ሙዳይ የቁጠባ ሒሳብ

ሙዳይ ተቀማጭ ሒሳብ በአነስተኛ ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች የሚከፍቱት የቁጠባ ሒሳብ ሲሆን፤ አገልግሎቱ የቁጠባ ባህልን ለማዳበር አነስተኛ ገቢ ያላቸው ቆጣቢዎችን ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ በመሆኑ ደንበኞችን ለማበረታታት በነፃ የገንዘብ ቁጠባ ሣጥኖች የሚሰጥበት የቁጠባ ሒሳብ ነው፡፡

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞  ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች  እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ ? የመንጣቱ ምክንያት ምንድን ነው ?

በአስደናቂነቱ፣ በታሪካዊነቱና በኪነ ህንጻ ጥበቡ ብዙ የተባለለት እና እና በአራት አስርት ዓመታት በፊት በዩኔስኮ የዓለማችን ቅርስ አንዱ ሆኖ የተመዘገበው የፋሲል ግንብ ተሰነጣጥቆ እና አርጅቶ መቆየቱ በርካቶች ሲያነሱት የነበረ ጉዳይ ነው።

በእርጅናም የህልውና ስጋት እንደገጠመውም ሲነገር ነበር።

የጥገና እድሳት እየተከናወለት ያለው ታሪካዊው የፋሲል ግንብ በቅርቡ ይፋ ተደርጓል።

ታሪካዊው ሽሯሟ ቀለም ያለው የፋሲል ግንብ ቀለሙ ነጥቶ መታየቱ ለበርካታ መላምት ክፍት እንዲሆን አድርጎታል።

የታሪካዊው ግንብ ቀለም ለዘመናት ከሚታወቅበት ተለውጦ ለምን ነጣ ? የሚል ጥያቄ እንዲነሳም ምክንያት ሆኗል።

አንዳንዶች " ቅርሱ በአግባቡ አልታደሰም፤ የታወቅበትን ታሪካዊነቱንና ቀለሙንም እንዲያጣ  ተደርጓል " ብለዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ በጥገና እድሳቱ በአማካሪነት እንዲሁም በጥናት የተሳተፉት አንጋፋው አርክቴክት ፋሲል ጊዮርጊስ ምን አሉ ?

" የፋሲል ግንብ ህንጻ ሲገነባ በአነስተኛ ድንጋዮች እና በኖራ ሲሆን፣ ለረጅም ዓመታት ዝናብ፣ በፀሐይ እና በተፈጥሯዊ ሂደቶች ውስጥ ሲያልፍ በርካቶች የሚያውቁትን ይሄንን ' ሽሯማ ' መልክ አምጥቷል።

አሁን እድሳቱ የተደረገበት ኖራ አዲስ በመሆኑ ቀለሙ ነጣ ብሏል።

የእድሳት ሥራው የተከናወነው የፋሲል ግንብ በመጀመሪያ በተገነባበት ማቴሪያል (ቁስ) በዋናነት በኖራ እና በድንጋይ ነው።

የቅርስ አጠባበቅ ሕግን በተከተለ መልክ ነው የተሠራው።

የኖራው አዲስ መሆን ብቻ ይሄንን ነጣ ያለ ቀለም አምጥቷል። የኖራ እና የድንጋይ መልኩ ከተወሰነ ዓመታት በኋላ ወደ ድሮው መልኩ ይመለሳል።

ልዩነቱ አዲስ የመሆን እና የማርጀት ጉዳይ ነው።

የፋሲል ግንብ መጀመሪያ ሲሠራ ኖራው ለብዙ ወራት ወይም ለዓመታት ተቀብሮ የነበረ ነው አሁንም ሲታደስ መነሻውን ተከትሎ ኖራው ለበርካታ ጊዜያት እንዲቀበር ተደርጎ ጥገናው ተካሂዷል።

ቅርሶች በተፈጥሮ፣ በፀሐይ፣ በዝናብ፣ በአቧራ ምክንያት በዓመታት ቀለማቸው እየተቀየረ የሚሄድ ነው ፤ ይሄኛውም ከዓመታት በኋላ የሚታወቀውን ቀለም ይይዛል።

በዓለም አቀፉ የቅርስ ጥገና ሕግ መሠረት ዋነኛው ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ በተሠራበት ቁስ (ማቴሪያል) ታድሷል ወይ ? የሚለው ነው በተሠራበት ድንጋይ እና ኖራ መልሶ መጠገኑ ዋናው ነገር ነው።

ይህንንም በትክክል መሥራቱን አረጋግጠናል።

በአንዳንድ ሁኔታዎች የድሮ ቀለሙን ለማምጣት ለመልክ ሲባል ኬሚካል ይቀላቀላ እነዚህ ግን ኬሚካል ነክ ነገሮች ስለሆኑ ያልታሰበ አደጋ ሊያስከትሉ ይችላሉ።

ቀለሙ እንደ ድሮው ቢመስል እንወድ ነበር፤ ሆኖም ለቀለም ተብለው የሚጨመሩ ነገሮች ያልታሰበ አደጋን በቅርስ ላይ ያመጣሉ።

በዓለም የቅርስ አጠባበቅ ደረጃ ዋነኛው ነገር ቅድሚያ የሚሰጠው የመነሻ ሃሳቡ ነው። ኖራው ትክክለኛ እና አስተማማኝ በመሆኑ የጥንቱ እንደያዘ የጥገና እድሳቱ እየተከናወነ ነው።

መነሻውን ሳይለቅ ጥርሳችንን ነክሰን የሠራንበት ነው።

የቀደመ መልኩ በጊዜ ብዛት ይመጣል የነበረው ገጽታ በጊዜ ሂደት ይመለሳል።

በሽሯሟ መልኩ የሚታወቀው የፋሲል ግንብ መቼ ተመልሶ ይመጣ ይሆን ? የሚለው ዝናብ ሲመታው እና የአየር ሁኔታዎች ሲፈራረቁበት እየተቀየረ ይሄዳል።

ህንጻው ወደ ቀደመ ቀለሙ ለመመለስም ከሦስት እስከ አራት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ ሊወስድ ይችላል።

አንዳንድ ቦታ ላይ በጣም የጠቋቆሩ የግንቡ አናት ላይ አካላት ነበሩ። ድንጋዮቹ ወደ ነበሩበት ለመመለስ እስከ አምስት ዓመት ድረስ የሚደርስ ወይም የግንቡ አናት ላይ ያሉትን ጠቆር ያሉትን የቀደመ ገጽታ ለማምጣት ከዚያ ረዘም ያለ ጊዜ ይወስዳል " ብለዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።

@thikvahethiopia