TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ደቡብ ክልል ? እስካሁን የክልልን አደረጃጀትን በምክር ቤቶች የፀደቁ እነማን ናቸው ? - ወላይታ - ጋሞ - ጌዴኦ - የም ልዩ ወረዳ - ቡርጂ ልዩ ወረዳ - ኮንሶ - ባስኬቶ ልዩ ወረዳ - ኧሌ ልዩ ወረዳ - ደቡብ ኦሞ - አማሮ ልዩ ወረዳ በአንድ የክልል ስር ለመሆን በየምክር ቤቶቻቸው አፅድቀዋል። - ከምባታ - ሀላባ - ሀዲያ - የም ልዩ ወረዳ ምክር ቤቶች ከጉራጌ እና ስልጤ ዞኖች ጋር በአንድ…
#ስልጤ_ዞን

በዛሬው ዕለት የስልጤ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባዔዉን ማካሄድ ጀምሯል።

ጉባኤው ሁለት ቀናት የሚቆይ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ እንደሚወያይ ተገልጿል።

ምክር ቤቱ ከሚወያይባቸው አጀንዳዎቹ መካከል ቀዳሚው #የክልል_አደረጃጀትን በተመለከተ በቀረበ መነሻ ሀሳብ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

ትላንት የከምባታ፣ ሀላባ ፣ ሀዲያ ዞኖች እና የም ልዩ ወረዳ ምክር ቤቶች ከጉራጌ እና ስልጤ ዞኖች ጋር በአንድ ላይ በመሆን በአንድ ክልል ስር ለመጠቃለል በምክር ቤቶቻቸው መወሰናቸው የሚታወስ ነው።

የክልል አደረጃጀትን በተመለከተ የጉራጌ እና ስልጤ ዞኖች በም/ቤት ገና ውሳኔ እንዳላሳለፉ መነገሩም አይዘነጋም።

ዛሬ የስልጤ ዞን ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።

@tikvahethiopia