TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"አልሞትኩም!" ፕሬዘዳንት ሙሀመድ ቡሀሪ‼️

ሞቱ የተባሉትና በአንድ እርሳቸውን በሚመስሉ ሱዳናዊ የተተኩት የናይጄሪያው ፕሬዚዳንት #ሙሐሙደ_ቡሃሪ «አልሞትኩም» አሉ።

ቡሃሪ ትናንት ዕሁድ ኢንተርኔት ላይ የተሰራጨውን ተባራሪ ወሬ ያስተባበሉት፣ ፖላንደ ካቶዊስ ውስጥ በሚካሄደው የተመድ የአየር ንብረት ጉባዔ ለመካፈል በሄዱበት ወቅት፣ እዚያ ከሚገኙ የናይጄዊያ ዳያስፖራ ጋር በተገናኙበት ወቅት ነው።

«በእኔ ይሁንባችሁ፣ እኔ እራሴ ነኝ፣ አታዩም?» ያሉት ቡሃሪ፣ «በቅርቡ 76ኛ የልደት በዐሌን አከብራለሁ፣ እናም የበለጠ ጠንካራ እሆናለሁ» ማለታቸው ተሰምቷል።

ከቃል አቀባያችው ቢሮ ይፋ በሆነ መግለጫ መሠረት፣ ብዙ ሰዎች ወደ ምክትሉ እየሄዱ፣ ለምክትልነት አመልክተዋል፤ እኔ ሞቻለኋ!! ሃ! ሃ! የፈጠራ ወሬው የተናፈሰው፣ ቡሃሪ በህመም ምክንያት ያለፈውን 2017 ዓ.ም አብዛኛውን ጊዜ ሎንዶን በህክምና በማሳለፋቸው እንደሆነም ታውቋል።

«ማይሞችና ሃይማኖት የሌላቸው ናቸው የፈጠራ ወሬውን ያሰራጩት» ብለዋል።

ምንጭ፦ VOA አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia