TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የ245 ሺህ ብር ሽልማት አሸናፊዎች 👏
ከአሳ ተረፈ ምርት (ከአሳ ቆዳ) በመጠቀም #ሎሽን የሰሩት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የአምና ምሩቃን በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጀው የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ የ245 ሺህ ብር አሸነፊ ከሆኑት መካከል ይጠቀሳሉ።
" ሬይ ኮስሞቲክስ " ከአሳ ቆዳ ሎሽን በማዘጋጀት አንደኛ የአካባቢን ንፅህን በመጠበቅ በሌላ በኩል ለተገልጋዮች አሁን ላይ ገበያ ላይ ካሉት ሎሽኖች ለየት ያሉ ጠቅሞችን የሚያሰጥ እንደሆነ ተገልጾልናል።
እስካሁን ወደ ምርት እንዳልገቡ የተናገሩት የሬይ ኮስሞቲክስ አባላት በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግቢ ስር እዳሉ አሳውቀዋል። ወደ ሽያጭ እና ወደ ምርት ለመግባት ግን ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
የሬይ ኮስሞቲክስ መስራች እና የፕሮዳክሽን ማነጀር ራውላ ኤፍሬም የስራ ፈጠራ ውድድሩ ላይ በመወዳደር የ245 ሺህ ብር አሸናፊዎች መሆን መቻላቸውን ገልፃለች።
ከሶስት ሳምንት በፊት አሸናፊ ቢሆኑም እስካሁን ግን ብሩ እጃቸው ላይ እንዳልደረሰ ጠቁመውናል።
@tikvahethiopia
ከአሳ ተረፈ ምርት (ከአሳ ቆዳ) በመጠቀም #ሎሽን የሰሩት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የአምና ምሩቃን በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጀው የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ የ245 ሺህ ብር አሸነፊ ከሆኑት መካከል ይጠቀሳሉ።
" ሬይ ኮስሞቲክስ " ከአሳ ቆዳ ሎሽን በማዘጋጀት አንደኛ የአካባቢን ንፅህን በመጠበቅ በሌላ በኩል ለተገልጋዮች አሁን ላይ ገበያ ላይ ካሉት ሎሽኖች ለየት ያሉ ጠቅሞችን የሚያሰጥ እንደሆነ ተገልጾልናል።
እስካሁን ወደ ምርት እንዳልገቡ የተናገሩት የሬይ ኮስሞቲክስ አባላት በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ግቢ ስር እዳሉ አሳውቀዋል። ወደ ሽያጭ እና ወደ ምርት ለመግባት ግን ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል።
የሬይ ኮስሞቲክስ መስራች እና የፕሮዳክሽን ማነጀር ራውላ ኤፍሬም የስራ ፈጠራ ውድድሩ ላይ በመወዳደር የ245 ሺህ ብር አሸናፊዎች መሆን መቻላቸውን ገልፃለች።
ከሶስት ሳምንት በፊት አሸናፊ ቢሆኑም እስካሁን ግን ብሩ እጃቸው ላይ እንዳልደረሰ ጠቁመውናል።
@tikvahethiopia
👍416👏60❤18😢13😱12🥰6