TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbeba

ኢ/ር ታከለ ኡማ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ ግብር እድሳት የተደረላቸውን ቤቶች #ለአረጋዊያን እና #አቅመ_ደካሞች በማስረከብ ላይ ይገኛሉ፡፡ በዛሬው ዕለትም ኢ/ር ታከለ ኡማ እራሳቸው እድሳቱን ያስጀመሩትን በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቃኘው ሻለቃ ተብሎ በሚጠራው አደባባይ አከባቢ የሚኖሩ እናት መኖሪያ ቤት ስራው ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ ለባለንብረቷ ቤታቸውን አስረክበዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በክረምት የበጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር 1000 ለሚሆኑ አረጋዊያን ቤት ለማደስ ወደ ስራ የገባ ቢሆንም እስከ አሁን 1,573 ለሚሆኑ በከተማው ውስጥ ለሚገኙ አረጋዊያን የመኖሪያ ቤት እድሳት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ከዚህም ውስጥ 1,111 ቤቶች እድሳት ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ለባለንብረቶቹ ተላልፈዋል፡፡

Via Mayor Office AA
@tsegabwolde @tikvahethiopia