TIKVAH-ETHIOPIA
" 26 ሰዎች ወዲያ ነው ህይወታቸው ያለፈው። ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል " - ፖሊስ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ፤ ጉዳያ ቢላ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ26 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። አደጋው ከሻምቡ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው የተከሰተው፡፡ በደረሰው አደጋ የ26 ወገኖቻችን ሕይወት ወዲያው ሲያልፍ 42 ወገኖቻችን ላይ ደግሞ…
#Update
“ አደጋው በጣም አሰቃቂ ነው። 28 ሰዎች ሞተዋል። 45ቱ ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ” - የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ጉደያ ቢላ ወረዳ ደረሰ በተባለው የትራፊክ አደጋ፣ እስካሁን የሟቾች ቁጥር 28 መድረሱን የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ኮሚሽኑ ስለአደጋው መንስኤ በሰጠን ቃል፣ “የፊት ጎማው በሮ ወጥቶ ነው። በፍጥነት ላይም ነበር። የፍሬን ቴክኒክ ችግር እንዳለም መረጃ አለ” ብሏል።
የሟቾች ቁጥር ከ26 ጨመረ እንዴ? ስንል የጠየቅናቸው የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋና መረጃ ክፍል ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር መሰለ አበራ፣ “እስካሁን ባለው መረጃ የሟቾች ቁጥር 28 ነው” ብለዋል።
“ ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 45 ሰዎች ናቸው። እነርሱም በባኮ ሆስፒታል ህክምና ላይ ናቸው ” ነው ያሉት።
የደረሰባቸው ጉዳት ቀላል ጭምር ነው ወይስ ከባድ ብቻ ነው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ዋና ኢንስፔክተሩ፣ “ 45ቱም ከባድ አደጋ ነው የደረሰባቸው ” ሲሉ መልሰዋል።
“ ከሻምቡ ወደ አዲስ አበባ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ማርሴዲስ ኮድ 3A 12661 መኪና ጉደያ ቢላ ወረዳ ጎንካ ኢጃ ቀበሌ ጅማ ወንዝ የሚባል ልዩ ቦታ ነው የፊት ጎማው በሮ ገደል የገባው ” ሲሉም የአደጋውን መንስኤ ጨምር አስረድተዋል።
አክለው፣ “ የፊት ለፊት ጎማው በሮ ወጥቶ ነው። በፍጥነት ላይም ነበር። የፍሬን ቴክኒክ ችግር እንዳለም መረጃ አለ። ፓሊስ በማጣራት ላይ ይገኛል ” ነው ያሉት።
የተሳፈሩ ሰዎች ስንት ነበሩ ? ጉዳት ሳይደርስባቸው የተረፉ ይኖሩ ይሆን? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “ አሁን ባለው መረጃ 28 ሟች፣ 45 ከባድ ጉዳት አጠቃላይ ሹፌርና ረዳት፣ ተሳፋሪን ጨምሮ ነው። መኪያው ውስጥ የነበሩት እነዚሁ ናቸው ” ብለዋል ዋና ኢንስፔክተሩ።
“ አደጋው የደረሰበት ማርሴዲስ ተሽከርካሪ ስሪቱ በጣም የቆዬ በመሆኑ ለረጅም ርቀት መመደብ አልነበረበትም ” የሚል አስተያዬት ሲሰጥ ተስተውሏል፤ የፓሊስ አስተያዬት ምንድን ነው ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄም አቅርበናል።
ኢንስፔክተሩ፣ “እኛ ይሄ መረጃ አልደረሰንም። መንገድ ትራንስፓርት መረጃውን አይቶ ከመናኸሪያ የሚመድበው ስለሆነ ከትልቁ መናኸሪያ ነው ይሄ ስምሪት የሚሰጠው” ብለዋል።
“የሚመለከተው አካል፣ ፌደራል መንገድ ትራንስፓርት አይቶ ስሞሪት የሚሰጥ ስለሆነ እንደኛ እንዲህ አይነት ችግር ካለ እነርሱም ፍተሻ እንዲያደርጉና እንዲህ አይነት ርቀት ቦታም ባይመደብ ጥሩ ነው” ሲሉም አክለዋል።
የፍጥነትም ሆነ የቴክኒክ ችግር እንዲህ አይነት አደጋዎች እንዳይደገሙ ባስላለፉት መልዕክት፣ “ይሄ አሰቃቂ አደጋ ነው። እንደ ኦሮሚያ የደረሰው ከባድ አደጋ ነው። በድጋሚ እንዳይከሰት ባለ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ሳይሰማሩ በፊት የቲክኒክ ችግር ቢመረምሩ” ሲሉ አሳስበዋል።
ዋና ኢንስፔክሩ በምላሻቸው፣ “የቲክኒክ ችግር በጣም ለአደጋ ስለሚያጋልጥ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ነው መልዕክት የማስተላልፈው” ሲሉም አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ አደጋው በጣም አሰቃቂ ነው። 28 ሰዎች ሞተዋል። 45ቱ ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ” - የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን ጉደያ ቢላ ወረዳ ደረሰ በተባለው የትራፊክ አደጋ፣ እስካሁን የሟቾች ቁጥር 28 መድረሱን የኦሮሚያ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ኮሚሽኑ ስለአደጋው መንስኤ በሰጠን ቃል፣ “የፊት ጎማው በሮ ወጥቶ ነው። በፍጥነት ላይም ነበር። የፍሬን ቴክኒክ ችግር እንዳለም መረጃ አለ” ብሏል።
የሟቾች ቁጥር ከ26 ጨመረ እንዴ? ስንል የጠየቅናቸው የክልሉ ፓሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋና መረጃ ክፍል ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር መሰለ አበራ፣ “እስካሁን ባለው መረጃ የሟቾች ቁጥር 28 ነው” ብለዋል።
“ ከባድ አደጋ የደረሰባቸው 45 ሰዎች ናቸው። እነርሱም በባኮ ሆስፒታል ህክምና ላይ ናቸው ” ነው ያሉት።
የደረሰባቸው ጉዳት ቀላል ጭምር ነው ወይስ ከባድ ብቻ ነው ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ ዋና ኢንስፔክተሩ፣ “ 45ቱም ከባድ አደጋ ነው የደረሰባቸው ” ሲሉ መልሰዋል።
“ ከሻምቡ ወደ አዲስ አበባ ተሳፋሪዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ማርሴዲስ ኮድ 3A 12661 መኪና ጉደያ ቢላ ወረዳ ጎንካ ኢጃ ቀበሌ ጅማ ወንዝ የሚባል ልዩ ቦታ ነው የፊት ጎማው በሮ ገደል የገባው ” ሲሉም የአደጋውን መንስኤ ጨምር አስረድተዋል።
አክለው፣ “ የፊት ለፊት ጎማው በሮ ወጥቶ ነው። በፍጥነት ላይም ነበር። የፍሬን ቴክኒክ ችግር እንዳለም መረጃ አለ። ፓሊስ በማጣራት ላይ ይገኛል ” ነው ያሉት።
የተሳፈሩ ሰዎች ስንት ነበሩ ? ጉዳት ሳይደርስባቸው የተረፉ ይኖሩ ይሆን? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “ አሁን ባለው መረጃ 28 ሟች፣ 45 ከባድ ጉዳት አጠቃላይ ሹፌርና ረዳት፣ ተሳፋሪን ጨምሮ ነው። መኪያው ውስጥ የነበሩት እነዚሁ ናቸው ” ብለዋል ዋና ኢንስፔክተሩ።
“ አደጋው የደረሰበት ማርሴዲስ ተሽከርካሪ ስሪቱ በጣም የቆዬ በመሆኑ ለረጅም ርቀት መመደብ አልነበረበትም ” የሚል አስተያዬት ሲሰጥ ተስተውሏል፤ የፓሊስ አስተያዬት ምንድን ነው ? የሚል ተጨማሪ ጥያቄም አቅርበናል።
ኢንስፔክተሩ፣ “እኛ ይሄ መረጃ አልደረሰንም። መንገድ ትራንስፓርት መረጃውን አይቶ ከመናኸሪያ የሚመድበው ስለሆነ ከትልቁ መናኸሪያ ነው ይሄ ስምሪት የሚሰጠው” ብለዋል።
“የሚመለከተው አካል፣ ፌደራል መንገድ ትራንስፓርት አይቶ ስሞሪት የሚሰጥ ስለሆነ እንደኛ እንዲህ አይነት ችግር ካለ እነርሱም ፍተሻ እንዲያደርጉና እንዲህ አይነት ርቀት ቦታም ባይመደብ ጥሩ ነው” ሲሉም አክለዋል።
የፍጥነትም ሆነ የቴክኒክ ችግር እንዲህ አይነት አደጋዎች እንዳይደገሙ ባስላለፉት መልዕክት፣ “ይሄ አሰቃቂ አደጋ ነው። እንደ ኦሮሚያ የደረሰው ከባድ አደጋ ነው። በድጋሚ እንዳይከሰት ባለ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች ሳይሰማሩ በፊት የቲክኒክ ችግር ቢመረምሩ” ሲሉ አሳስበዋል።
ዋና ኢንስፔክሩ በምላሻቸው፣ “የቲክኒክ ችግር በጣም ለአደጋ ስለሚያጋልጥ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ነው መልዕክት የማስተላልፈው” ሲሉም አስገንዝበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " - ፓርኩ
በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የቆየውና ለቀናት ከቁጥጥር ውጪ ለማድረግ አስቸግሮ የነበረው ቃጠሎ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፓርኩና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ይህን ተከትሎም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በአደጋው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ የጠየቀ ሲሆን፣ እንስሳት መቃጠላቸውንና ከ350 እስከ 400 ሄክታር የሚገመት ሳራማ ቦታ መቃጠሉን ሰምቷል።
የፓርኩ ኃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ ምን አሉ ?
" የካቲት 1/2017 ዓ/ም መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር። ትላንት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር ተደርጓል። ዛሬም ከጠዋቱ 11 ሰዓት ጀምረን ጫካ ነበርን ሙሉ በመሉ መጥፋቱን አረጋግጠናል።
ተራማጅ የሆኑና መሮጥ የሚችሉ የዱር እንስሳት ብዙዎቹ አምልጠዋል። ግን መራመድ የማይችሉ፣ አዲስ የተወለዱ የዱር እንስሳት ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።
እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ግን የጉዳቱን መጠን ሰርቨይ መሰራት አለበት " ብለዋል።
የፓርኩ ምን ያክል ክፍል እንደተቃጠለ ታውቋል? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ " መለካት ያስፈልጋል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
" ደረቃማ ሳር ስላለ በትንሹ ነው የሚቀጣጠለውና በሰው ኃይል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት፣ በሰው ኃይል ከመቆጣጠር በላይ ሆኖ ነው በግሬደርና፣ ከእሳቱ ርቆ በሎደር የማስራብ ሥራ የተሰራው” ሲሉ አስታውሰዋል።
ፖርኩ ወደ 244 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ 42 አጥቢዎችና ሌሎች እንስሳት እንዳሉበት አስረድተው፣ “የተመሰረተው በኬንያና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ትልቁ የሜዳ አህያ ለመጠበቅ ነው” ብለዋል።
ኮቪድ ከመከሰቱ በፊት እስከ 200 ሺሕ፣ ኮቪድ ተከስቶ ከቆዬ በኋላ የቱሪስት ቁጥር በመቀነሱ ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ገቢ የሚገኝበት እጩ ፓርክ መሆኑ ተነግሯል።
ፓርኩ ከአዲስ አበባ በ27ዐ ርቀት ላይ ያለ፣ ኤሪያው 1099 ስኩየር ኪሎሜትር የሆነ፣ ወይራ፣ የሀበሻ ጽድ፣ ዝንባ የመሳሰሉ እፅዋቶች ያሉበት፣ 40 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሜዳ ላይ ያረፈ ሳር ያለበት ነውም ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " - ፓርኩ
በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሔራዊ ፓርክ ተከስቶ የቆየውና ለቀናት ከቁጥጥር ውጪ ለማድረግ አስቸግሮ የነበረው ቃጠሎ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፓርኩና የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ይህን ተከትሎም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በአደጋው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ የጠየቀ ሲሆን፣ እንስሳት መቃጠላቸውንና ከ350 እስከ 400 ሄክታር የሚገመት ሳራማ ቦታ መቃጠሉን ሰምቷል።
የፓርኩ ኃላፊ አቶ አሕመድ እንድሪስ ምን አሉ ?
" የካቲት 1/2017 ዓ/ም መንስኤው ባልታወቀ ምክንያት የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ ነበር። ትላንት 10 ሰዓት በቁጥጥር ስር ተደርጓል። ዛሬም ከጠዋቱ 11 ሰዓት ጀምረን ጫካ ነበርን ሙሉ በመሉ መጥፋቱን አረጋግጠናል።
ተራማጅ የሆኑና መሮጥ የሚችሉ የዱር እንስሳት ብዙዎቹ አምልጠዋል። ግን መራመድ የማይችሉ፣ አዲስ የተወለዱ የዱር እንስሳት ጉዳት ሊያደርስ ችሏል።
እያጠፋን በነበርንበት ወቅት የኤሊና እባብ ዝርያዎች ተቃጥለው አግኝተናል። ግን የጉዳቱን መጠን ሰርቨይ መሰራት አለበት " ብለዋል።
የፓርኩ ምን ያክል ክፍል እንደተቃጠለ ታውቋል? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ " መለካት ያስፈልጋል። ከ350 እስከ 400 ሄክታር ሳራማ ቦታ ተቃጥሏል ብለን እንገምታለን " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
" ደረቃማ ሳር ስላለ በትንሹ ነው የሚቀጣጠለውና በሰው ኃይል ለመቆጣጠር አስቸጋሪ አድርጎት፣ በሰው ኃይል ከመቆጣጠር በላይ ሆኖ ነው በግሬደርና፣ ከእሳቱ ርቆ በሎደር የማስራብ ሥራ የተሰራው” ሲሉ አስታውሰዋል።
ፖርኩ ወደ 244 የአእዋፍ ዝርያዎች፣ 42 አጥቢዎችና ሌሎች እንስሳት እንዳሉበት አስረድተው፣ “የተመሰረተው በኬንያና በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኘውን ትልቁ የሜዳ አህያ ለመጠበቅ ነው” ብለዋል።
ኮቪድ ከመከሰቱ በፊት እስከ 200 ሺሕ፣ ኮቪድ ተከስቶ ከቆዬ በኋላ የቱሪስት ቁጥር በመቀነሱ ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ገቢ የሚገኝበት እጩ ፓርክ መሆኑ ተነግሯል።
ፓርኩ ከአዲስ አበባ በ27ዐ ርቀት ላይ ያለ፣ ኤሪያው 1099 ስኩየር ኪሎሜትር የሆነ፣ ወይራ፣ የሀበሻ ጽድ፣ ዝንባ የመሳሰሉ እፅዋቶች ያሉበት፣ 40 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሜዳ ላይ ያረፈ ሳር ያለበት ነውም ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔊 #የሠራተኞችድምፅ
“ ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው። ወዴት እንጩህ ? ” - ሠራተኞች
በምዕራብ አርሲ ዞን ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎችና ሠራተኞች “አመራሮች ደመወዛችንን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ለምን? ብሎ መጠየቅም አይቻልም” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ምሬታቸውን አሰምተዋል።
“‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ በሚል ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው" ያሉት ስሞታ አቅራቢዎቹ፣ "ወዴት እንጩህ?” ሲሉ ጠይቀዋል።
“ለቀበሌ ቤት መስሪያ" እንዲሁም "ለቡሳ ጎኖፋ” በሚል ደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው እንደሚቆረጥ፣ የዲቲ ክፍያ በወቅቱ እንደማይከፈላቸው፣ አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ክፍያም እንዳልተፈጸመላቸው አስረድተዋል።
“ዝም ብለው ነው የሚቆርጡብን ፈቃዳችንንም እንኳ አይጠይቁንም” ያሉ ሲሆን፣ የኑሮ ውድነቱን ተቋቁመው ቤተሰብ ማስዳደር ስላልቻሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።
ሠራተኞች ስላማረራቸው ጉዳይ ምን አሉ?
“ ከደመወዛችን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ያለ ማንም ፍላጎት ሰሞኑን 100% ከደመወዛችን ቆርጠዋል። ደመወዙ የሚቆረጠው ለፈረሙትም ላልፈረሙትም ነው።
በአመት 100% በደመወዝ ስኬል ነው የሚቆረጠው። ይህ በወር ከ500 እስከ 800 ሊሆን ይችላል። እንደዬ ስኬሉ መጠኑ ይለያያል። በዚህ ወር ደመወዛችን ተቆርጧል።
የዱዩቲ ክፍያም የአሁኑ ዘግይቷል። ሌላው የሦስት ወራት የዱቲ ክፍያ አልተፈጸመልንም ገና እየጠበቅን ነው። ፋይናንስ ነው ያልከፈለን። ፎርሙ ፋይናንስ ጋ ደርሷል።
የሁለት ወራት አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ አልተከፈለንም። ደመወዛችንን አናውቅም የማይቆረጥ የለም። ዝም ብለው ነው የሚቆርጡት ያለምንም ፈቃድ። እኛን አይጠይቁንም። እንደፈለጉ ነው የሚያደርጉን። ሠራተኛም አይጠይቅም።
ገንዘባችን በብዛት እየተቆረጠ ያለው ‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ ተብሎ ነው። ከዚህም በፊት ያለፍላጎታችን ይቆርጡ ነበር። የትም አቤት ቢባል መልስ አይገኝም።
ይህ ድርጊት የሚፈጸመው እኛ ወረዳ ብቻ እንጂ ሌላ ወረዳ ላይ አልሰማንም ደመወዝ እየቆረጡ ያሉት ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቅሬታው ምላሽ ለማካተት ከክልል፣ ዞን እንዲሁም ወረዳ ባለስልጣናት ለቀናት ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ምላሽ አልተገኘም። ሆኖም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኞች ከሆኑ በድጋሚ ጥረት ያደርጋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው። ወዴት እንጩህ ? ” - ሠራተኞች
በምዕራብ አርሲ ዞን ዝዋይ ዱግዳ ወረዳ ያሉ ጤና ባለሙያዎችና ሠራተኞች “አመራሮች ደመወዛችንን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ለምን? ብሎ መጠየቅም አይቻልም” ሲሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ምሬታቸውን አሰምተዋል።
“‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ በሚል ያለፈቃዳችን ከአመት ደመወዛችን 100% እየተቆረጠብን ነው" ያሉት ስሞታ አቅራቢዎቹ፣ "ወዴት እንጩህ?” ሲሉ ጠይቀዋል።
“ለቀበሌ ቤት መስሪያ" እንዲሁም "ለቡሳ ጎኖፋ” በሚል ደመወዛቸው ያለፈቃዳቸው እንደሚቆረጥ፣ የዲቲ ክፍያ በወቅቱ እንደማይከፈላቸው፣ አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ ክፍያም እንዳልተፈጸመላቸው አስረድተዋል።
“ዝም ብለው ነው የሚቆርጡብን ፈቃዳችንንም እንኳ አይጠይቁንም” ያሉ ሲሆን፣ የኑሮ ውድነቱን ተቋቁመው ቤተሰብ ማስዳደር ስላልቻሉ መፍትሄ እንዲሰጣቸው አሳስበዋል።
ሠራተኞች ስላማረራቸው ጉዳይ ምን አሉ?
“ ከደመወዛችን እንደፈለጉ ነው የሚቆርጡት። ያለ ማንም ፍላጎት ሰሞኑን 100% ከደመወዛችን ቆርጠዋል። ደመወዙ የሚቆረጠው ለፈረሙትም ላልፈረሙትም ነው።
በአመት 100% በደመወዝ ስኬል ነው የሚቆረጠው። ይህ በወር ከ500 እስከ 800 ሊሆን ይችላል። እንደዬ ስኬሉ መጠኑ ይለያያል። በዚህ ወር ደመወዛችን ተቆርጧል።
የዱዩቲ ክፍያም የአሁኑ ዘግይቷል። ሌላው የሦስት ወራት የዱቲ ክፍያ አልተፈጸመልንም ገና እየጠበቅን ነው። ፋይናንስ ነው ያልከፈለን። ፎርሙ ፋይናንስ ጋ ደርሷል።
የሁለት ወራት አዲሱ የደመወዝ ጭማሪ አልተከፈለንም። ደመወዛችንን አናውቅም የማይቆረጥ የለም። ዝም ብለው ነው የሚቆርጡት ያለምንም ፈቃድ። እኛን አይጠይቁንም። እንደፈለጉ ነው የሚያደርጉን። ሠራተኛም አይጠይቅም።
ገንዘባችን በብዛት እየተቆረጠ ያለው ‘የቀበሌ ቤት መስሪያ’ ተብሎ ነው። ከዚህም በፊት ያለፍላጎታችን ይቆርጡ ነበር። የትም አቤት ቢባል መልስ አይገኝም።
ይህ ድርጊት የሚፈጸመው እኛ ወረዳ ብቻ እንጂ ሌላ ወረዳ ላይ አልሰማንም ደመወዝ እየቆረጡ ያሉት ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቅሬታው ምላሽ ለማካተት ከክልል፣ ዞን እንዲሁም ወረዳ ባለስልጣናት ለቀናት ሙከራ ቢያደርግም ለጊዜው ምላሽ አልተገኘም። ሆኖም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኞች ከሆኑ በድጋሚ ጥረት ያደርጋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🚨“ በጣም ብዙ ችግር ነው እየደረሰባቸው ያለው። ጣታቸው የተቆረጠ አሉ ” - የወላጆች ኮሚቴ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰጠው መግለጫ በመነሳት፣ “ አንዳንድ ሚዲያዎች መንግስት በማይናማር የታገቱ ዜጎችን አስለቀቀ ” በማለት መዘገባቸው ስህተት መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። የታጋቾቹ ቤተሰቦች በዝርዝር ምን አሉ ? “ አጋቾች ያገቷቸውን ልጆቻችንን…
#Update
" ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው " - የወላጆች ኮሚቴ
ሰርተው ለመለወጥ በሚል ከኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች በማይናማር በአጋቾች የከፋ ስቃይ እያሳለፉ በመሆኑ መንግስት ከስቃይ እንዲታደጋቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ አይዘነጋም።
የወላጆች ኮሚቴ፣ ኢትዮጵያዊያኑ በታገቱበት የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ አጋቾች ልጆቹን ዶላር ማጭበርበር ላይ እንደሚያሰሯቸው በመግለጽ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ደጋግሞ መፍትሄ መጠየቁ ይታወቃል።
አሁንስ ኢትዮጵያዊያኑ ተለቀቁ ?
ለመፍትሄው ቅርብ የሆኑ አካላት ሁሉ መረጃ በመጠየቅ የታጋቾቹን ጉዳይ በጥልቀት የሚከታተሉ አንድ የታጋች ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ " ከሌሎች ዜጎች ጋር ተደምሮ 261 ልጆች ተለቀዋል። ከ261 ውስጥ ከ126 እስከ 138 ይደርሳል የወጡት የኢትዮጵያዊያኑ ቁጥር " ሲሉ ገልጸዋል።
የታጋቾቹ ወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እንዳልተለቀቁ፣ ነገር ግን የታይላንድ የጸጥታ ኃይሎችና ኤንጂኦዎች ጥረት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ከእገታው እንደወጡ ገልጾልናል።
ኮሚቴው በሰጠን ቃል፣ " ከቀናት በፊት 6ዐ ኢትዮጵያዊያን አጥር ዘለው ጠፍተው ከሌሎች አገር ዜጎች ጋር ወጥተው ፓሊስ በቁጥጥር ስር አውሏቸው ነበር " ብሏል።
" ትላንት ደግሞ ወደ 70 ኢትዮጵያዊያን ከተለያዩ ቦታዎች፣ ከ60ዎቹ ጋር በአጠቃላይ 130 ኢትዮጵያዊያን ወጥተው ወደ ባንኮክ እየተጓዙ ነው " ያለው ኮሚቴው፣ ቀሪዎቹም ልዩ ትኩረት እንደሚሹ ገልጿል።
" እንዲወጡልን ብለን ካመለክትንላቸው ልጆቻችን አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት እንኳ ገና አልወጡም " ብሎ፣ " የኢትዮጵያ መንግስት ልጆቻችንን ችላ ብሎብናል " ሲል ወቅሷል።
" ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በአሁኑ ወቅት ትንሽ ቢንቀሳቀስ በጣም ጥሩ ነው " ሲልም በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አስገንዝቧል።
ወጡ የተባሉ ልጆችን ያወጣቸው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ወይስ ሌላ ? ስንል ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ ኮሚቴው፣ " የኢትዮጵያ መንግስት ምንም እጁ የለበትም። ካሁን በኋላ እጁን ካስገባልን ግን አናውቅም " ሲል መልሷል።
ማነው ያወጣቸው ታዲያ ? ስንል በድጋሚ ላቀረብነው ጥያቄ በምላሹ ፣ " ያወጧቸው ኤንጂኦዎችና የታይላንድ መንግስት ማይናማር ያሉ የጸጥታ አካላት ናቸው " ብሏል።
" ለሚዲያ ከቨሬጅ ብለው እንደሆነም አናውቅም። ከተለያዩ አገራት ያሉ ልጆችን ‘አንተን፣ አንተን’ እያሉ ነው አሉ ያወጡት " ሲልም ስጋቱን ተናግሯል።
ኮሚቴው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል በዝርዝር ምን አለ ?
" ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው። ቀሪዎቹም ብዙ ናቸው። ማንም ካሁን በኋላ ዘወር ብሎ የሚያቸውም አይኖርም።
ያልወጡት ልጆቻችን ላይ አሁንም እዛው ያሉ አጋቾች የከፋ እርምጃ ሊወስዱባቸው የሚችሁሉበት አጋጣሚ ሰፊ ነው እንደወጡት ሁሉ ቶሎ የማውጣት ስራ ካልተቀላጠፈ።
እስቲ እንዲያው መንግስት ይድረስላቸው። የኢትዮጵያ መንግስት እዛው ቆሞ አለሁ ይበላቸው ልጆቻችንን። ታይላንድ ላይም ሰው ይመደብልን።
በእርግጥም የማይናማር አካባቢ የጸጥታ አካላት የእገታውን አካባቢ ተቆጣጥሯል ተብሏል። ስለዚህ ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከማይናማር መንግስት በአስቸኳይ ቀርቦ ልጆቹ የሚወጡበትን መንገድ ይነጋገርልን።
አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ይድረስልን እያልን ነው። የታይላንድ መንግስትና በማይናማር ያሉ አካላት ተባብረው የቻይና መንግስትም እየረዳቸው ነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት።
ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በከስቸኳይ ሰዎች መድቦ እንዲየጋገርና ሁሉም ልጆቻችን እንዲወጡልን አሁንም በድጋሚ መልዕክቴ ነው " ሲል አሳስቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው " - የወላጆች ኮሚቴ
ሰርተው ለመለወጥ በሚል ከኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች በማይናማር በአጋቾች የከፋ ስቃይ እያሳለፉ በመሆኑ መንግስት ከስቃይ እንዲታደጋቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ አይዘነጋም።
የወላጆች ኮሚቴ፣ ኢትዮጵያዊያኑ በታገቱበት የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ አጋቾች ልጆቹን ዶላር ማጭበርበር ላይ እንደሚያሰሯቸው በመግለጽ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ደጋግሞ መፍትሄ መጠየቁ ይታወቃል።
አሁንስ ኢትዮጵያዊያኑ ተለቀቁ ?
ለመፍትሄው ቅርብ የሆኑ አካላት ሁሉ መረጃ በመጠየቅ የታጋቾቹን ጉዳይ በጥልቀት የሚከታተሉ አንድ የታጋች ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ " ከሌሎች ዜጎች ጋር ተደምሮ 261 ልጆች ተለቀዋል። ከ261 ውስጥ ከ126 እስከ 138 ይደርሳል የወጡት የኢትዮጵያዊያኑ ቁጥር " ሲሉ ገልጸዋል።
የታጋቾቹ ወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን እንዳልተለቀቁ፣ ነገር ግን የታይላንድ የጸጥታ ኃይሎችና ኤንጂኦዎች ጥረት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ከእገታው እንደወጡ ገልጾልናል።
ኮሚቴው በሰጠን ቃል፣ " ከቀናት በፊት 6ዐ ኢትዮጵያዊያን አጥር ዘለው ጠፍተው ከሌሎች አገር ዜጎች ጋር ወጥተው ፓሊስ በቁጥጥር ስር አውሏቸው ነበር " ብሏል።
" ትላንት ደግሞ ወደ 70 ኢትዮጵያዊያን ከተለያዩ ቦታዎች፣ ከ60ዎቹ ጋር በአጠቃላይ 130 ኢትዮጵያዊያን ወጥተው ወደ ባንኮክ እየተጓዙ ነው " ያለው ኮሚቴው፣ ቀሪዎቹም ልዩ ትኩረት እንደሚሹ ገልጿል።
" እንዲወጡልን ብለን ካመለክትንላቸው ልጆቻችን አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት እንኳ ገና አልወጡም " ብሎ፣ " የኢትዮጵያ መንግስት ልጆቻችንን ችላ ብሎብናል " ሲል ወቅሷል።
" ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በአሁኑ ወቅት ትንሽ ቢንቀሳቀስ በጣም ጥሩ ነው " ሲልም በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አስገንዝቧል።
ወጡ የተባሉ ልጆችን ያወጣቸው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ወይስ ሌላ ? ስንል ጠይቀነው በሰጠን ምላሽ ኮሚቴው፣ " የኢትዮጵያ መንግስት ምንም እጁ የለበትም። ካሁን በኋላ እጁን ካስገባልን ግን አናውቅም " ሲል መልሷል።
ማነው ያወጣቸው ታዲያ ? ስንል በድጋሚ ላቀረብነው ጥያቄ በምላሹ ፣ " ያወጧቸው ኤንጂኦዎችና የታይላንድ መንግስት ማይናማር ያሉ የጸጥታ አካላት ናቸው " ብሏል።
" ለሚዲያ ከቨሬጅ ብለው እንደሆነም አናውቅም። ከተለያዩ አገራት ያሉ ልጆችን ‘አንተን፣ አንተን’ እያሉ ነው አሉ ያወጡት " ሲልም ስጋቱን ተናግሯል።
ኮሚቴው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል በዝርዝር ምን አለ ?
" ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው። ቀሪዎቹም ብዙ ናቸው። ማንም ካሁን በኋላ ዘወር ብሎ የሚያቸውም አይኖርም።
ያልወጡት ልጆቻችን ላይ አሁንም እዛው ያሉ አጋቾች የከፋ እርምጃ ሊወስዱባቸው የሚችሁሉበት አጋጣሚ ሰፊ ነው እንደወጡት ሁሉ ቶሎ የማውጣት ስራ ካልተቀላጠፈ።
እስቲ እንዲያው መንግስት ይድረስላቸው። የኢትዮጵያ መንግስት እዛው ቆሞ አለሁ ይበላቸው ልጆቻችንን። ታይላንድ ላይም ሰው ይመደብልን።
በእርግጥም የማይናማር አካባቢ የጸጥታ አካላት የእገታውን አካባቢ ተቆጣጥሯል ተብሏል። ስለዚህ ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከማይናማር መንግስት በአስቸኳይ ቀርቦ ልጆቹ የሚወጡበትን መንገድ ይነጋገርልን።
አሁንም ቢሆን የኢትዮጵያ መንግስት ይድረስልን እያልን ነው። የታይላንድ መንግስትና በማይናማር ያሉ አካላት ተባብረው የቻይና መንግስትም እየረዳቸው ነው እየተንቀሳቀሱ ያሉት።
ቶኪዮ ያለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በከስቸኳይ ሰዎች መድቦ እንዲየጋገርና ሁሉም ልጆቻችን እንዲወጡልን አሁንም በድጋሚ መልዕክቴ ነው " ሲል አሳስቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ExitExamResult ➡" የፈተናው ውጤት ተለቆ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል " - የትምህርት ሚኒስቴር አመራር 🔴" የፈተና ውጤት ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ጋር መጥቷል " - የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት የሀገር አቀፍ መውጫ ፈተና ውጤት ለዩኒቨርሲቲዎች መላኩን የትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት አጭር ቃል ፥ " ፈተናው…
#UPDATE #ExitExamResult
“ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል። ከዚህኛው ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተንና እንቅፋታቸው ትልልቅ የሆኑም እስከነጨረሻውም የሚይፈተኑበት ጊዜ ሊኖር ይችላል ” - ትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሃገር አቀፉን የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት ከሰዓታት በፊት መለቀቁን ትምትርት ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸውን ነግረናችኋል።
በወቅቱም የፈተናው ውጤት የሚታይበት ሊንክ ስንጠይቅ “ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል ” በመባሉ የተለዬ መመልከቻ ካለ እንደምናጋራችሁ ቃል ገብተንላችሁ ነበር።
በዚህም፣ የውጤት መመልከቻው ሊንክ የትኛው ነው ? ስንል የጠየቅናቸው አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር በሰጡን ቃል፣ “ ውጤት የሚታይበት ሊንክ ኖርማሊ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል። ከተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ውጪ ሁሉም ማዬት እንዲችሉ ተነግሯቸዋል ” የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።
“ ሊንኩ፦ ባለፈው ኦንላይን ሳፓርቲንግ የምንጠቀምበት ፔጅ ነበረ፤ እዛ ፔጅ ላይ ተለቋል። ያውቁታል እነሱ ፤ ከዚህ በፊት የተለቀቀ ሊንክ ነው ለኤግዚት ኤግዛም የተመዘገቡበት ሊንክ ላይ ውጤት ማየት ይችላሉ ” ሲሉ አስረድተዋል።
ስንት ተማሪዎች እንዳለፉና እንደወደቁ ጠይቀናቸው ገና እንዳልታወቀ በገለጹበት አውድ፣ “ አናላይስሱ አልተሰራም። አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ቅዳሜ እለት ስለሚያስመርቁ ለእነሱ ተብሎ ነው በችኮላ የተለቀቀው ” ብለዋል።
በሌላ በኩል፣ የዲሲፒሊን ጉድለት የታየባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የፈተና ውጤት አለመለቀቁንም እኝሁ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
“ የዲሲፒሊን ግድፈት ጎልቶ የታየባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ውጤት አልተለቀቀም፤ ወደ 6 በሚሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች። ከዛ ውጪ ተለቋል። ስለዚህ አናላይሲሱ የ6ቱም ተጨምሮ ሲያልቅ ይሰራል ” ሲሉ ነግረውናል።
ስለዚህ የፈተናው ውጤት በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ነው የተላከው ማለት ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ፣ “ የፈተና ኮራፕሽኑ፤ ስርቆቱ የጎላባቸው 6 ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ላይ ነው እንጂ ያልተለቀቀው ሁሉም ላይ ተለቋል ” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን።
በፈተናው ወቅት የተፈጠረ ችግር ነበር ወይስ በሰላም ተጠናቋል ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የአመራሩ ምላሽ፣ “ በዚህኛው ፈተናችን በሰላም ነው የተጠናቀቀው። የጎላ ቸግር አልነበረም ” የሚል ነው።
አክለው ደግሞ፣ “ የተለመዱ የዲሲፒሊን ችግሮች ናቸው የነበሩት፣ የተማሪዎች ከስርቆት ጋር በተገናኘ ያልተፈቀዱ እንደ ሞባይል ያሉ ኤሌክትሮኒክ ዲቫይሶችን ለመጠቀም ሙከራ ማድረግ፣ ወጣ ያለ ደግሞ ከዚህ በፊት የተፈተኑ ተማሪዎች ገብተው ለመፈተን ሙከራ ማድረግ፣ ናቸው እንጂ በጣም የጎላ ችግር አልታዬም ” ነው ያሉት።
ከዲሲፒሊን ግድፈት ጋር በተያያዘ ስንት ተማሪዎች ተገኝተዋል ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ “ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ እስካሁን ድረስ ወደ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል። የዚህኛው ራውንድ ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተንና እንቅፋታቸው ትልልቅ የሆኑ እስከነጨረሻውም የማይፈተኑበት ጊዜ ሊኖር ይችላል ” ብለዋል።
“ እስካሁን ግን አልተወሰነም። ለጊዜው ግን የዚህኛው ውጤት ዲስኳሊፋይድ እንደሚደረግ ነው 54ዐ ተማሪዎች የተለዩት። ቁጥሩ ሊበልጥ ይችላል፤ ለጊዜው ግን ወደ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል ” ሲሉም አክለዋል።
(ስንት ተፈታኞች እንዳለፉና እንዳላለፉ ውጤቱን ተከታትለን በቀጣይ የምናሳውቃችሁ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል። ከዚህኛው ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተንና እንቅፋታቸው ትልልቅ የሆኑም እስከነጨረሻውም የሚይፈተኑበት ጊዜ ሊኖር ይችላል ” - ትምህርት ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሃገር አቀፉን የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት ከሰዓታት በፊት መለቀቁን ትምትርት ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸውን ነግረናችኋል።
በወቅቱም የፈተናው ውጤት የሚታይበት ሊንክ ስንጠይቅ “ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል ” በመባሉ የተለዬ መመልከቻ ካለ እንደምናጋራችሁ ቃል ገብተንላችሁ ነበር።
በዚህም፣ የውጤት መመልከቻው ሊንክ የትኛው ነው ? ስንል የጠየቅናቸው አንድ የትምህርት ሚኒስቴር አመራር በሰጡን ቃል፣ “ ውጤት የሚታይበት ሊንክ ኖርማሊ ለዩኒቨርሲቲዎች ተልኳል። ከተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ውጪ ሁሉም ማዬት እንዲችሉ ተነግሯቸዋል ” የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።
“ ሊንኩ፦ ባለፈው ኦንላይን ሳፓርቲንግ የምንጠቀምበት ፔጅ ነበረ፤ እዛ ፔጅ ላይ ተለቋል። ያውቁታል እነሱ ፤ ከዚህ በፊት የተለቀቀ ሊንክ ነው ለኤግዚት ኤግዛም የተመዘገቡበት ሊንክ ላይ ውጤት ማየት ይችላሉ ” ሲሉ አስረድተዋል።
ስንት ተማሪዎች እንዳለፉና እንደወደቁ ጠይቀናቸው ገና እንዳልታወቀ በገለጹበት አውድ፣ “ አናላይስሱ አልተሰራም። አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ቅዳሜ እለት ስለሚያስመርቁ ለእነሱ ተብሎ ነው በችኮላ የተለቀቀው ” ብለዋል።
በሌላ በኩል፣ የዲሲፒሊን ጉድለት የታየባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የፈተና ውጤት አለመለቀቁንም እኝሁ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
“ የዲሲፒሊን ግድፈት ጎልቶ የታየባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ውጤት አልተለቀቀም፤ ወደ 6 በሚሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች። ከዛ ውጪ ተለቋል። ስለዚህ አናላይሲሱ የ6ቱም ተጨምሮ ሲያልቅ ይሰራል ” ሲሉ ነግረውናል።
ስለዚህ የፈተናው ውጤት በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ነው የተላከው ማለት ነው ? ስንል ላቀረብንላቸው ጥያቄ ፣ “ የፈተና ኮራፕሽኑ፤ ስርቆቱ የጎላባቸው 6 ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ላይ ነው እንጂ ያልተለቀቀው ሁሉም ላይ ተለቋል ” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን።
በፈተናው ወቅት የተፈጠረ ችግር ነበር ወይስ በሰላም ተጠናቋል ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የአመራሩ ምላሽ፣ “ በዚህኛው ፈተናችን በሰላም ነው የተጠናቀቀው። የጎላ ቸግር አልነበረም ” የሚል ነው።
አክለው ደግሞ፣ “ የተለመዱ የዲሲፒሊን ችግሮች ናቸው የነበሩት፣ የተማሪዎች ከስርቆት ጋር በተገናኘ ያልተፈቀዱ እንደ ሞባይል ያሉ ኤሌክትሮኒክ ዲቫይሶችን ለመጠቀም ሙከራ ማድረግ፣ ወጣ ያለ ደግሞ ከዚህ በፊት የተፈተኑ ተማሪዎች ገብተው ለመፈተን ሙከራ ማድረግ፣ ናቸው እንጂ በጣም የጎላ ችግር አልታዬም ” ነው ያሉት።
ከዲሲፒሊን ግድፈት ጋር በተያያዘ ስንት ተማሪዎች ተገኝተዋል ? ለሚለው ጥያቄ በሰጡን ምላሽ፣ “ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ እስካሁን ድረስ ወደ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል። የዚህኛው ራውንድ ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተንና እንቅፋታቸው ትልልቅ የሆኑ እስከነጨረሻውም የማይፈተኑበት ጊዜ ሊኖር ይችላል ” ብለዋል።
“ እስካሁን ግን አልተወሰነም። ለጊዜው ግን የዚህኛው ውጤት ዲስኳሊፋይድ እንደሚደረግ ነው 54ዐ ተማሪዎች የተለዩት። ቁጥሩ ሊበልጥ ይችላል፤ ለጊዜው ግን ወደ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል ” ሲሉም አክለዋል።
(ስንት ተፈታኞች እንዳለፉና እንዳላለፉ ውጤቱን ተከታትለን በቀጣይ የምናሳውቃችሁ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Breaking : የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል። ሚኒስትሩ አብረዋቸው ለውድድር የቀረቡትን የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው የተመረጡት። @tikvahethiopia
#Update
ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ቦታ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ 6 ዙር ከፈጀው የድምጽ አሰጣጥ በኋላ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው መመረጥ ችለዋል።
የምርጫ ሂደቱ ምን ይመስላል?
በምርጫው የሚያሸንፈው ተመራጭ ድምጽ መስጠት ከሚችሉት 48 አባል ሀገራት ሁለት ሶስተኛውን ድምጽ (33 ድምፅ) ማግኘት ይጠበቅበታል።
በሚደረገው ምርጫ ለማሸነፍ የሚያስፈልገውን 33 ነጥብ ማግኘት ካልተቻለ ተከታታይ ምርጫዎች የሚካሄዱ ሲሆን ዝቅተኛ ድምጽ ያገኘው ከውድድሩ ተሰናብቶ ቀሪ ተወዳዳሪዎች ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ነጥብ እስኪያገኙ ይወዳደራሉ።
በዚህም ለ7ኛ ጊዜ በተደረገው በዚህ ውድድር አሸናፊውን ለመለየት 6 ዙሮች ፈጅቷል።
በመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዙሮች የኬንያው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ መምራት ቢችሉም የማሸነፊያ ነጥብ ሳያገኙ ቀርተዋል።
በስድስተኛው ዙር ድምጽ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ለማሸነፍ የሚያስፈልጋቸውን 33 ነጥብ በማግኘታቸው ምርጫውን አሸንፈዋል።
በዚህም ለቀጣይ 4 ዓመታት የቀድሞውን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂን በመተካት 7ኛው የኅብረቱ ሊቀመንበር በመሆን መመረጥ ችለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከፍተኛ ፉክክር በታየበት የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ቦታ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ 6 ዙር ከፈጀው የድምጽ አሰጣጥ በኋላ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሆነው መመረጥ ችለዋል።
የምርጫ ሂደቱ ምን ይመስላል?
በምርጫው የሚያሸንፈው ተመራጭ ድምጽ መስጠት ከሚችሉት 48 አባል ሀገራት ሁለት ሶስተኛውን ድምጽ (33 ድምፅ) ማግኘት ይጠበቅበታል።
በሚደረገው ምርጫ ለማሸነፍ የሚያስፈልገውን 33 ነጥብ ማግኘት ካልተቻለ ተከታታይ ምርጫዎች የሚካሄዱ ሲሆን ዝቅተኛ ድምጽ ያገኘው ከውድድሩ ተሰናብቶ ቀሪ ተወዳዳሪዎች ለማሸነፍ የሚያስችላቸውን ነጥብ እስኪያገኙ ይወዳደራሉ።
በዚህም ለ7ኛ ጊዜ በተደረገው በዚህ ውድድር አሸናፊውን ለመለየት 6 ዙሮች ፈጅቷል።
በመጀመሪያዎቹ ተከታታይ ዙሮች የኬንያው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ መምራት ቢችሉም የማሸነፊያ ነጥብ ሳያገኙ ቀርተዋል።
በስድስተኛው ዙር ድምጽ የጅቡቲው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ለማሸነፍ የሚያስፈልጋቸውን 33 ነጥብ በማግኘታቸው ምርጫውን አሸንፈዋል።
በዚህም ለቀጣይ 4 ዓመታት የቀድሞውን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂን በመተካት 7ኛው የኅብረቱ ሊቀመንበር በመሆን መመረጥ ችለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia