TIKVAH-ETHIOPIA
" ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ እንጀምራለን፤ ... የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖችንም ተከራይተናል " - ጠ/ሚር ሪሺ ሱናክ ዩናይትድ ኪንግደም በቁጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ መላክ ትጀምራለች። የዩናይትድ ኪንግደም ፓርላማ ስደተኞች/ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ ለመመለስ የተያዘውን እቅድ መጀመር የሚያስችለውን " የሩዋንዳ እቅድ " የተሰኘውን ረቂቅ…
" ... ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የመላክ እቅዱ ገና ከአሁኑ ተጽእኖ እያሳደረብን ነው " - አይርላንድ
ዩናይትድ ኪንግደም በሕገ-ወጥ መልኩ ወደ አገሯ የሚገቡ ስደተኞችን ወደ #ሩዋንዳ እልካለሁ ማለቷን ተከትሎ ዩኬ የሚገኙ ስደተኞች ወደ ሩዋንዳ ላለመመለስ ሲሉ እንደ #አየርላንድ ያሉ አገራትን አማራጭ መዳረሻቸው እያደረጉ መሆኑ ተነግሯል።
ይህን ተከትሎ የአየርላንድ መንግሥት ከዩናይትድ ኪንግደም የሚመጡ ስደተኞችን ወደ ዩናይትድ ኪንግደም መመለስ የሚያስችለውን ሕጋዊ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ጀምሯል።
የአየርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑት ሲሞን ሃሪስ የአገሪቱ ፍትሕ ሚኒስቴር ስደተኞችን ወደ ዩኬ መመለስ የሚያስችል ሕግ አርቅቆ ለአገሪቱ ካቢኔ እንዲያቀርብ አዘዋል።
የሀገሪቱ ፍትሕ ሚኒስቴር በቅርቡ ወደ አየርላንድ ከተሻገሩ ስደተኞች መካከል 80% የሚሆኑት መነሻቸው ዩኬ መሆኑን ገልጿል።
የዩኬ ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የመላክ እቅድ ገና ከአሁኑ በአየርላንድ ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
ዩናይትድ ኪንግደም በቁጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ መላክ ትጀምራለች።
ለዚህም ፤ የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖች ኪራይ መፈጸሙ እና ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የሚወስዱ ሰራተኞችም መሰልጠናቸው ተነግሯል።
@tikvahethiopia
ዩናይትድ ኪንግደም በሕገ-ወጥ መልኩ ወደ አገሯ የሚገቡ ስደተኞችን ወደ #ሩዋንዳ እልካለሁ ማለቷን ተከትሎ ዩኬ የሚገኙ ስደተኞች ወደ ሩዋንዳ ላለመመለስ ሲሉ እንደ #አየርላንድ ያሉ አገራትን አማራጭ መዳረሻቸው እያደረጉ መሆኑ ተነግሯል።
ይህን ተከትሎ የአየርላንድ መንግሥት ከዩናይትድ ኪንግደም የሚመጡ ስደተኞችን ወደ ዩናይትድ ኪንግደም መመለስ የሚያስችለውን ሕጋዊ ማዕቀፍ ማዘጋጀት ጀምሯል።
የአየርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር የሆኑት ሲሞን ሃሪስ የአገሪቱ ፍትሕ ሚኒስቴር ስደተኞችን ወደ ዩኬ መመለስ የሚያስችል ሕግ አርቅቆ ለአገሪቱ ካቢኔ እንዲያቀርብ አዘዋል።
የሀገሪቱ ፍትሕ ሚኒስቴር በቅርቡ ወደ አየርላንድ ከተሻገሩ ስደተኞች መካከል 80% የሚሆኑት መነሻቸው ዩኬ መሆኑን ገልጿል።
የዩኬ ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የመላክ እቅድ ገና ከአሁኑ በአየርላንድ ላይ ተጽእኖ እያሳደረ ነው መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
ዩናይትድ ኪንግደም በቁጣዮቹ ከ10 እስከ 12 ሳምንታት ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ መላክ ትጀምራለች።
ለዚህም ፤ የንግድ ቻርተር አውሮፕላኖች ኪራይ መፈጸሙ እና ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ የሚወስዱ ሰራተኞችም መሰልጠናቸው ተነግሯል።
@tikvahethiopia
#EU #Visa
የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት የኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ጊዜያዊ ገደብ ጣለ።
የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት በኅብረቱ አባል ሀገራት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ገደብ ማስቀመጡን ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን ቪዛ አመልካቾች ቪዛ ሲፈልጉ ፦
- አስፈላጊ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ እና በአውሮፓ ህብረት ህግ የተቀመጠውን መደበኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ እንደሚገደዱ፤
- አባል ሀገራት ከአሁን በኋላ ከ2 ጊዜ በላይ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ለመግባት የሚያስችለውን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን መስጠት እንደማይችሉ ፤
- የዲፕሎማቲክ ወይም የሰርቪስ ፓስፖርት የያዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ ሲፈልጉ መደበኛ የቪዛ ክፍያ ለመክፈል እንደሚገደዱ ተነግሯል።
በተጨማሪ መደበኛ ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን ተቀይሯል።
ይህ ውሳኔ የተወሰነው የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት ባደረገው ግምገማ መሰረት ኢትዮጵያ በህገ-ወጥ መንገድ በአውሮፓ ህብረት ሀገራት የሚቆዩትን ዜጎቿን በማስመለስ ረገድ የምታደርገው ጥረት በቂ ባለመሆኑ ነው ተብሏል።
ገደቡ እንከመቼ እንደሚቆይ የተባለ ነገር የለም።
https://www.consilium.europa.eu/en/press/press-releases/2024/04/29/ethiopia-council-restricts-visa-provision/
@TikvahethMagazine @tikvahethiopia
የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት የኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ጊዜያዊ ገደብ ጣለ።
የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት በኅብረቱ አባል ሀገራት ውስጥ ለኢትዮጵያውያን ዜጎች ቪዛ አሰጣጥ ላይ ገደብ ማስቀመጡን ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን ቪዛ አመልካቾች ቪዛ ሲፈልጉ ፦
- አስፈላጊ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ እና በአውሮፓ ህብረት ህግ የተቀመጠውን መደበኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ እንደሚገደዱ፤
- አባል ሀገራት ከአሁን በኋላ ከ2 ጊዜ በላይ ወደ ህብረቱ አባል ሀገራት ለመግባት የሚያስችለውን ቪዛ ለኢትዮጵያውያን መስጠት እንደማይችሉ ፤
- የዲፕሎማቲክ ወይም የሰርቪስ ፓስፖርት የያዙ ኢትዮጵያውያን ቪዛ ሲፈልጉ መደበኛ የቪዛ ክፍያ ለመክፈል እንደሚገደዱ ተነግሯል።
በተጨማሪ መደበኛ ቪዛ ለማግኘት የሚጠበቀው የ15 ቀን ጊዜ ወደ 45 ቀን ተቀይሯል።
ይህ ውሳኔ የተወሰነው የአውሮፓ ህብረት ም/ቤት ባደረገው ግምገማ መሰረት ኢትዮጵያ በህገ-ወጥ መንገድ በአውሮፓ ህብረት ሀገራት የሚቆዩትን ዜጎቿን በማስመለስ ረገድ የምታደርገው ጥረት በቂ ባለመሆኑ ነው ተብሏል።
ገደቡ እንከመቼ እንደሚቆይ የተባለ ነገር የለም።
https://www.consilium.europa.eu/en/press/press-releases/2024/04/29/ethiopia-council-restricts-visa-provision/
@TikvahethMagazine @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል። " በሁሉም ክልሎች ያሉ…
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ 9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር
በዓሉን ምክንያት በማድረግ የ25% ቅናሽ የተደረገባቸውን የቤት ዕቃዎቻችንን ገዝተው ቤትዎን ያድምቁ!
የዘመናዊነት ተምሳሌት!
አድራሻችን
1. ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251 995 27 2727 / +251 911 51 6843
2. ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251 957 86 8686
3. ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251 993 82 8282
👉 Telegram: https://t.iss.one/yonatanbt_furniture
👉 Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=100087238034736
👉 TikTok: https://www.tiktok.com/@yonatanbtfurniture
በዓሉን ምክንያት በማድረግ የ25% ቅናሽ የተደረገባቸውን የቤት ዕቃዎቻችንን ገዝተው ቤትዎን ያድምቁ!
የዘመናዊነት ተምሳሌት!
አድራሻችን
1. ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251 995 27 2727 / +251 911 51 6843
2. ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251 957 86 8686
3. ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251 993 82 8282
👉 Telegram: https://t.iss.one/yonatanbt_furniture
👉 Facebook: https://www.facebook.com/profile.php?id=100087238034736
👉 TikTok: https://www.tiktok.com/@yonatanbtfurniture
በመቐለ እና በዙሪያዋ በሚገኙ 18 አከባቢዎች ከዛሬ ጀምሮ ለአራት ቀናት (እስከ ሚያዚያ 25) የኤሌክትሪክ አገልግሎት ይቋረጣል።
የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጠው በጥገና ምክንያት መሆኑን ገልጿል።
አገልግሎቱ ከሚቋረጥባቸው አከባቢዎች 11 በመቐለ ፤ቀሪዎቹ 7 ደግሞ ከመቐለ ውጭ የሚገኙ መሆናቸው ተመላክቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#AmharaRegion
አቶ መልካሙ ፀጋዬ በአቶ ጣሂር መሀመድ ምትክ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተነግሯል።
የአማራ ብልፅግና ፓርቲ፥" ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከፍተኛ አመራር የሆኑትን አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በማድረግ ሹመዋል " ሲል አሳውቋል።
በዚህ ኃላፊነት ቦታ የነበሩት አቶ ጣሂር መሃመድ ከቦታው ተነስተዋል። ለምን በእሳቸው ምትክ ሌላ አዲስ ሰው እንደተሾመ / ከቦታው እንደተነሱ ፣ ለሌላ ሹመት እና ኃላፊነት ታጭተው እንደሆነ በግልጽ የተባለ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
አቶ መልካሙ ፀጋዬ በአቶ ጣሂር መሀመድ ምትክ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተነግሯል።
የአማራ ብልፅግና ፓርቲ፥" ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከፍተኛ አመራር የሆኑትን አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በማድረግ ሹመዋል " ሲል አሳውቋል።
በዚህ ኃላፊነት ቦታ የነበሩት አቶ ጣሂር መሃመድ ከቦታው ተነስተዋል። ለምን በእሳቸው ምትክ ሌላ አዲስ ሰው እንደተሾመ / ከቦታው እንደተነሱ ፣ ለሌላ ሹመት እና ኃላፊነት ታጭተው እንደሆነ በግልጽ የተባለ ነገር የለም።
@tikvahethiopia
" የተጠየቀው የህክምና ወጪው በመንግሥት የሀኪም ደመወዝ እና በቤተሰቦቼ አቅም የሚቻል አይደለም " - ዶ/ር ሳምሶን ይስሀቅ
ዶ/ር ሳምሶን ይስሀቅ ላጋጠመው የጤና እክል መታከሚያ ደጋግ ኢትዮጵያውያን እንዲተባበሩት ጠየቀ።
ዶክተሩ 2015 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በህክምና ሙያ ትምህርት ነው የተመረቀው።
ከተመረቀ በኃላም ለ6 ወራት በጠቅላላ ሀኪምነት ወገኑን ሲያገለግል ቆይቷል።
በድንገት ግን ሚዛኑን ስቶ መውደቅ እና ሌሎችም ምልክቶችን በማሳየቱ ወደ ጤና ተቋም ሄዶ ምርመራ ካደረገ በኋላ ' የጭንቅላት እጢ ' እንዳለበት ተነግሮታል። የናሙና ምርመራ ተደርጎ ' GradeIII Astrocytoma ' እንዳለበት ተገልጾለታል።
" ትልቅ ቦታ ደርሼ ማየት ለሚመኙት ቤተሰቦቼና ከኔ በታች ላሉት እህት ወንድሞቼ ዜናው በጣም ትልቅ ዱብዳ ነው የሆነባቸው " ያለው ዶክተር ይስሃቅ " የጥቁር አንበሳ የጭንቅላት ቀዶ ጥገና ሀኪሞች ወደ ውጪ ሀገር ሄጄ ህክምና ማድረግ እንዳለብኝ ወስነዋል " ሲል ገልጿል።
ለህክምናው ወጪው እስከ 👉 2.3 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግም እንደተነገረው አስረድቷል።
ይህን ከፍተኛ ወጪ በመንግስት ሰራተኛ የሀኪም ደሞዝም ሆነ በቤተሰቦቹ አቅም የሚቻል ባለመሆኑ ሁላችሁም የቻላችሁትን እንድትረዱት ተማጽኗል።
ዶ/ር ይስሃቅ " በየሃይማኖታችሁ ፈጣሪ በመንገዴ ሁሉ እንዲረዳኝ በጸሎታችሁ አስቡኝ " ሲልም ጠይቋል።
ከዶክተሩ የተላከ የህክምና ማስረጃን መመልከት የቻልን ሲሆን ወላጅ እናቱን ብርሃኔ በየነን በስልክ ቁጥ ር +251911353752 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል።
እገዛ ለማድረግ የምትፈልጉ ፦
ዶክተር ሳምሶን ይስሃቅ በየነ
ንግድ ባንክ ፦ 1000139965691
አዋሽ ባንክ ፦ 013201172039000
ብርሃኔ በየነ ሚደቅሳ (እናት)
ንግድ ባንክ ፦ 1000549927681
አዋሽ ባንክ ፦ 01347903970500
GoFundMe👇
https://gofund.me/618fc8ee
@tikvahethiopia
ዶ/ር ሳምሶን ይስሀቅ ላጋጠመው የጤና እክል መታከሚያ ደጋግ ኢትዮጵያውያን እንዲተባበሩት ጠየቀ።
ዶክተሩ 2015 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በህክምና ሙያ ትምህርት ነው የተመረቀው።
ከተመረቀ በኃላም ለ6 ወራት በጠቅላላ ሀኪምነት ወገኑን ሲያገለግል ቆይቷል።
በድንገት ግን ሚዛኑን ስቶ መውደቅ እና ሌሎችም ምልክቶችን በማሳየቱ ወደ ጤና ተቋም ሄዶ ምርመራ ካደረገ በኋላ ' የጭንቅላት እጢ ' እንዳለበት ተነግሮታል። የናሙና ምርመራ ተደርጎ ' GradeIII Astrocytoma ' እንዳለበት ተገልጾለታል።
" ትልቅ ቦታ ደርሼ ማየት ለሚመኙት ቤተሰቦቼና ከኔ በታች ላሉት እህት ወንድሞቼ ዜናው በጣም ትልቅ ዱብዳ ነው የሆነባቸው " ያለው ዶክተር ይስሃቅ " የጥቁር አንበሳ የጭንቅላት ቀዶ ጥገና ሀኪሞች ወደ ውጪ ሀገር ሄጄ ህክምና ማድረግ እንዳለብኝ ወስነዋል " ሲል ገልጿል።
ለህክምናው ወጪው እስከ 👉 2.3 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግም እንደተነገረው አስረድቷል።
ይህን ከፍተኛ ወጪ በመንግስት ሰራተኛ የሀኪም ደሞዝም ሆነ በቤተሰቦቹ አቅም የሚቻል ባለመሆኑ ሁላችሁም የቻላችሁትን እንድትረዱት ተማጽኗል።
ዶ/ር ይስሃቅ " በየሃይማኖታችሁ ፈጣሪ በመንገዴ ሁሉ እንዲረዳኝ በጸሎታችሁ አስቡኝ " ሲልም ጠይቋል።
ከዶክተሩ የተላከ የህክምና ማስረጃን መመልከት የቻልን ሲሆን ወላጅ እናቱን ብርሃኔ በየነን በስልክ ቁጥ ር +251911353752 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል።
እገዛ ለማድረግ የምትፈልጉ ፦
ዶክተር ሳምሶን ይስሃቅ በየነ
ንግድ ባንክ ፦ 1000139965691
አዋሽ ባንክ ፦ 013201172039000
ብርሃኔ በየነ ሚደቅሳ (እናት)
ንግድ ባንክ ፦ 1000549927681
አዋሽ ባንክ ፦ 01347903970500
GoFundMe👇
https://gofund.me/618fc8ee
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AmharaRegion አቶ መልካሙ ፀጋዬ በአቶ ጣሂር መሀመድ ምትክ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተነግሯል። የአማራ ብልፅግና ፓርቲ፥" ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከፍተኛ አመራር የሆኑትን አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በማድረግ ሹመዋል " ሲል አሳውቋል። በዚህ ኃላፊነት ቦታ የነበሩት…
#Update
የአብን አባሉ አቶ ጣሂር መሐመድ " በግል ምክንያት " ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊነት መልቀቃቸውን ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ተናግረዋል።
" ከባለፉት ሶስት፣ አራት ወራት ወዲህ አንስቶ ከኃላፊነት የመልቀቅ ጉዳይ ላይ ከክልሉ አመራሮች ጋር በዝርዝር ንግግር አድርጌያለሁ " ያለቱ አቶ ጣሂር " የክልሉ መንግሥት ጥያቄውን ተቀብሏል " ብለዋል።
" ትንሽ የቤተሰብ ጉዳይ ስለነበረብኝ በቤተሰብ እና በራሴ ጉዳይ ነው የለቀቅሁት ከክልሉ አመራሮች ጋር በመነጋገር ከፓርቲያችን ሰው ተክተን ነው የወጣሁት " ሲሉ ገልጸዋል።
በአቶ ጣሂር መሐመድ ምትክ ሌላኛው የፓርቲው አባል አቶ መልካሙ ፀጋዬ ናቸው በክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ አረጋ ከበደ የተሾሙት።
@tikvahethiopia
የአብን አባሉ አቶ ጣሂር መሐመድ " በግል ምክንያት " ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊነት መልቀቃቸውን ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ተናግረዋል።
" ከባለፉት ሶስት፣ አራት ወራት ወዲህ አንስቶ ከኃላፊነት የመልቀቅ ጉዳይ ላይ ከክልሉ አመራሮች ጋር በዝርዝር ንግግር አድርጌያለሁ " ያለቱ አቶ ጣሂር " የክልሉ መንግሥት ጥያቄውን ተቀብሏል " ብለዋል።
" ትንሽ የቤተሰብ ጉዳይ ስለነበረብኝ በቤተሰብ እና በራሴ ጉዳይ ነው የለቀቅሁት ከክልሉ አመራሮች ጋር በመነጋገር ከፓርቲያችን ሰው ተክተን ነው የወጣሁት " ሲሉ ገልጸዋል።
በአቶ ጣሂር መሐመድ ምትክ ሌላኛው የፓርቲው አባል አቶ መልካሙ ፀጋዬ ናቸው በክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ አረጋ ከበደ የተሾሙት።
@tikvahethiopia
ቴሌብር ሱፐርአፕ ከአዲስ ተጨማሪ ስጦታ ጋር ቀረበልዎ!
💰የ 15 ብር ስጦታ
🌐 የ100 ሜባ ስጦታ
የሞባይል ጥቅል ሲገዙ 10% ተጨማሪ ስጦታን ጨምሮ አሁን ደግሞ የአየር ሰዓት ሲገዙ እስከ 25% ተጨማሪ ያገኛሉ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን ከ https://onelink.to/fpgu4m አውርደው በርካታ ጉዳዮችን በአንድ መተግበሪያ ይከውኑ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
💰የ 15 ብር ስጦታ
🌐 የ100 ሜባ ስጦታ
የሞባይል ጥቅል ሲገዙ 10% ተጨማሪ ስጦታን ጨምሮ አሁን ደግሞ የአየር ሰዓት ሲገዙ እስከ 25% ተጨማሪ ያገኛሉ!
ቴሌብር ሱፐርአፕን ከ https://onelink.to/fpgu4m አውርደው በርካታ ጉዳዮችን በአንድ መተግበሪያ ይከውኑ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
ወዳጅ ዘመድ ለበዓል የሚልክላችሁን ገንዘብ ከ900 በላይ ቅርንጫፎች እንዲሁም 24 ሰዓት በሚሰሩት 31 የቨርችዋል ባንኪንግ ማዕከላት ይቀበሉ።
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#virtualbanking #bankinginethiopia #banksinethiopia #ITM #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
ወዳጅ ዘመድ ለበዓል የሚልክላችሁን ገንዘብ ከ900 በላይ ቅርንጫፎች እንዲሁም 24 ሰዓት በሚሰሩት 31 የቨርችዋል ባንኪንግ ማዕከላት ይቀበሉ።
አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
#virtualbanking #bankinginethiopia #banksinethiopia #ITM #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
" ነገሩ ሁሉ በጥድፊያ ነበር የሆነው #በፌስቡክ የተለቀቀውን ፎቶ እንኳን መነሳቴን አላውቅም " - ወ/ሮ አማረች ያዕቆብ
ከወር በፊት በመንግሥት የኮሚኒኬሽን ገጾች ፣ በመንግሥት ሚዲያዎች እና ከነዚህ በወሰዱ የማህበራዊ ትስስር ገጾች አንዲት ሰራተኛ " መድሃኒት ሰርቃ ልትወጣ ስልት እጅ ከፍንጅ ተይዛ በቁጥጥር ስር ዋለች " የሚል ዜና መሰራጨቱ ይታወሳል።
ይህች ግለሰብ ወ/ሮ አማረች ያዕቆብ ትባላለች።
በወላይታ ዞን ፣ አባላ አባያ ወረዳ ከምትሰራበት የህክምና ተቋም ተረኛ ሆና ለሊት አድራ ልትወጣ እየተዘጋጀች በነበረበት ወቅት መድሀኒት ጠፋ ተብሎ ሲፈለግ ቆይቶ በመጨረሻ እርሷ ትያዛለች።
" መድሃኒቱ ግን የእርሷ ባልሆነ ጋወን ውስጥ መገኘቱን " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጻለች።
ወ/ሮ አማረች ፥ " መድሀኒት ስትሰርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘች " ተብላ በጥድፊያ ለእስር እና ለእንግልት መዳረጓን አስረድታለች።
ይህ ሳያንስ የመንግስት ኮሚኒኬሽኖች ገጾችና የመንግስት ሚዲያዎች ዜናውን በማህበራዊ ገጾቻቸዉ ማራገባቸዉ ለከፍተኛ የስነልቦና ጉዳት እንደዳረጋት ተናግራለች።
በመጨረሻ በእስር ቤት ውስጥ እያለች የደረሱላት የጠበቆች ቡድን እውነቱን አውጥተው ነጻ እንዳደረጓት ገልጻለች።
" እነሱ ባይደርሱልኝ ኖሮ ባልሰራሁት ወንጀል ወደ ወህኒ ልወርድ ነበር " ያለችው ወ/ሮ አማረች " ጉዳዩን አሁን ላይ ሳስበው ህልም መስሎ ነው የሚታየኝ " ብላለች።
በጉዳዩ ላይ ቃላቸውን የሰጡት የጠበቆች ቡድን አባሉ ጠበቃና የህግ አማካሪዉ አቶ መብራቱ ኮርኪሳ ፥ " በደንበኛችን ላይ የቀረበዉ የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ #ነጻ_ተብላ_የመገመት መብቷን ከመጣስ ባለፈ ሁኔታዉን ለማጣራት ስንሞክርም ብዙ የሚያጠራጥሩ መረጃዎች ልናገኝ ችለናል " ብለዋል።
በዚህም በወላይታ ከፍተኛ ፍ/ቤት የተበዳዩዋን የዋስ መብት ከመጠየቅ አንስቶ " በነጻ በእስር እስክትወጣ ድረስ ታግለናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላዉ የጠበቆች ቡድን አባሉ የህግ ጠበቃ እና መምህሩ አቶ አበባየሁ ጌታ ፤ " ክሱን ያቀረበባት አቃቤ ህግ ያቀረባቸዉ ምስክሮች በሰጡት ቃል ወንጀሉን እንዳልፈጸመች ማረጋገጡን ተከትሎ ፍ/ቤቱ በነጻ አሰናብቷታል " ብለዋል።
አሁን ላይ ነጻ ብትወጣም የደረሰባት የስም ማጥፋት ከፍተኛ የስነልቦና ጫና እንዳሳደረባት ጠቁመዋል።
ከዚህ በኋላ የሚቀረዉ በሚዲያ የጠፋዉን ስሟን የመመለስና ለደረሰባት ጉዳት ካሳ የመጠየቅ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው ይህም በግለሰቧ ፍላጎት የሚመሰረት ነው ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ከወር በፊት በመንግሥት የኮሚኒኬሽን ገጾች ፣ በመንግሥት ሚዲያዎች እና ከነዚህ በወሰዱ የማህበራዊ ትስስር ገጾች አንዲት ሰራተኛ " መድሃኒት ሰርቃ ልትወጣ ስልት እጅ ከፍንጅ ተይዛ በቁጥጥር ስር ዋለች " የሚል ዜና መሰራጨቱ ይታወሳል።
ይህች ግለሰብ ወ/ሮ አማረች ያዕቆብ ትባላለች።
በወላይታ ዞን ፣ አባላ አባያ ወረዳ ከምትሰራበት የህክምና ተቋም ተረኛ ሆና ለሊት አድራ ልትወጣ እየተዘጋጀች በነበረበት ወቅት መድሀኒት ጠፋ ተብሎ ሲፈለግ ቆይቶ በመጨረሻ እርሷ ትያዛለች።
" መድሃኒቱ ግን የእርሷ ባልሆነ ጋወን ውስጥ መገኘቱን " ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጻለች።
ወ/ሮ አማረች ፥ " መድሀኒት ስትሰርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘች " ተብላ በጥድፊያ ለእስር እና ለእንግልት መዳረጓን አስረድታለች።
ይህ ሳያንስ የመንግስት ኮሚኒኬሽኖች ገጾችና የመንግስት ሚዲያዎች ዜናውን በማህበራዊ ገጾቻቸዉ ማራገባቸዉ ለከፍተኛ የስነልቦና ጉዳት እንደዳረጋት ተናግራለች።
በመጨረሻ በእስር ቤት ውስጥ እያለች የደረሱላት የጠበቆች ቡድን እውነቱን አውጥተው ነጻ እንዳደረጓት ገልጻለች።
" እነሱ ባይደርሱልኝ ኖሮ ባልሰራሁት ወንጀል ወደ ወህኒ ልወርድ ነበር " ያለችው ወ/ሮ አማረች " ጉዳዩን አሁን ላይ ሳስበው ህልም መስሎ ነው የሚታየኝ " ብላለች።
በጉዳዩ ላይ ቃላቸውን የሰጡት የጠበቆች ቡድን አባሉ ጠበቃና የህግ አማካሪዉ አቶ መብራቱ ኮርኪሳ ፥ " በደንበኛችን ላይ የቀረበዉ የሶሻል ሚዲያ ዘመቻ #ነጻ_ተብላ_የመገመት መብቷን ከመጣስ ባለፈ ሁኔታዉን ለማጣራት ስንሞክርም ብዙ የሚያጠራጥሩ መረጃዎች ልናገኝ ችለናል " ብለዋል።
በዚህም በወላይታ ከፍተኛ ፍ/ቤት የተበዳዩዋን የዋስ መብት ከመጠየቅ አንስቶ " በነጻ በእስር እስክትወጣ ድረስ ታግለናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላዉ የጠበቆች ቡድን አባሉ የህግ ጠበቃ እና መምህሩ አቶ አበባየሁ ጌታ ፤ " ክሱን ያቀረበባት አቃቤ ህግ ያቀረባቸዉ ምስክሮች በሰጡት ቃል ወንጀሉን እንዳልፈጸመች ማረጋገጡን ተከትሎ ፍ/ቤቱ በነጻ አሰናብቷታል " ብለዋል።
አሁን ላይ ነጻ ብትወጣም የደረሰባት የስም ማጥፋት ከፍተኛ የስነልቦና ጫና እንዳሳደረባት ጠቁመዋል።
ከዚህ በኋላ የሚቀረዉ በሚዲያ የጠፋዉን ስሟን የመመለስና ለደረሰባት ጉዳት ካሳ የመጠየቅ ጉዳይ መሆኑን ገልጸው ይህም በግለሰቧ ፍላጎት የሚመሰረት ነው ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia