#ትግራይ
የኤርትራ ሰራዊት በተቆጣጠራቸው የኢሮብ የኢትዮጵያ የትግራይ አከባቢዎች ለሚገኙ ነዋሪዎች ማስጠንቀቅያ ሲሰጥ የሚያሳይ የቪድዮ መረጃ የኢሮብ ብሄረሰብ ተወላጆችን አሰቆጥቷል።
የኤርትራ ሰራዊት ተወካይ የኢሮብ ተወላጆች ስብስቦ ማስጠንቀቅያ ሲሰጥ የሚያሳየው የቪድዮ መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በመሰራጨት ላይ ሲሆን በክልሉ ሚድያዎችም ሽፋን ሰጥተውታል።
የቪድዮው የድምፂ ቅጂ ምን ይላል ?
"... እናንተ ህዝብ ናችሁ። የምትኖሩበት መሬት ደግሞ የኤርትራ ነው። ኤርትራውያን ከሆናችሁ ለዚሁ አከባቢና መሬት ተገዢ እንዲሁም እዚህ ላለው ሰራዊት የማገዝ ግዴታ አለባችሁ።
አገራዊ አገልግሎት የመስጠት ግዴታም አለባችሁ። በትወልዱም በትጠሉም አንድ የኤርትራ ዜጋ የሚያሳልፈውን ህይወት ልታልፉ ግድ ይላል።
አንድ ሰው ከዚህ አከባቢ ወደ አገራዊ አገልግሎት ከሄደ ለኤርትራ አገሩ ብሎ ነው የሚሄደው። ስለዚህ እያንዳንዳችሁ አገራዊ አገልግሎት እንደሚመለከታችሁ ማወቅ አለባችሁ። አባቶች የሃይማኖት መሪዎች ስሙ ከመካከላችሁ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ካለ የኤርትራ መንግስት እዚህ አስገድዶ አያኖረውም። ወደ ኢትዮጵያ የመሄድ መብት አለው። የኤርትራ መሬት ደግሞ ኤርትራውያን ይኖሩበታል።
ወደ አገራዊ አገልግሎት መሄድ ካለብህ ትሄዳለህ፤ ረሃብ ካለ እንደ ሌላው ኤርትራዊ ትራባለህ። በቃ ተካፍለህ ትኖራለህ። ላንተ ተብሎ የሚደረግ የተለየ ነገር የለም። ልቅ የሆነ አካሄድ ነው የቆየው ይህ ከአሁን በኃላ አይቀጥልም። " ሲል ያስጠንቅቃል የኤርትራ ሰራዊት ተወካዩ።
ቪድዮውን የተመለከቱ የኢሮብ ብሄረሰብ ተወላጆች የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና የፌደራል መንግስት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ከጥፋት እንዲታደግዋቸው ተማፅነዋል።
ብርሃን ወዲ ኢሮብ የተባለው የብሄረሰቡ ተወላጅ በሰጠው አስተያየት " ... አራት ዓመት ሙሉ በሁለት ተከፍለን ኮምፓስዋ እንደጠፋት መርከብ ሆነን ተሰፋችን ጨልሞብናል። ብሄረሰባችን እየጠፋ አረ የሰሚ ያለህ.." ሲል ምሬቱን ገልጿል።
የኤርትራ ሰራዊት በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ፦
- የዛላኣንበሳ ከተማ
- በጉሎመኸዳ ወረዳ ማርታ ፣ አዲስ ተስፋ ፣ አዲስ ዓለም ፣ ሸዊት ለምለምና ሰበያ
- በኢሮብ ወረዳ እንዳልጌዳ ፣ ወርዓትለ ዓገረ ሎኽማና ዓሊቴና የተባሉ የኢትዮጵያ አከባቢዎች ተቆጣጥሮ ይገኛል።
በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በታሕታይ ኣድያቦ የኩናማ ማህበረሰብና ሌሎች የሚኖሩባቸው ገማህሎ ፣ አደመይቲ ፣ የባድመ ከተማና አከባቢው ፣ ዓዲ ፀፀር ፣ ለምለም ሸዊት ፣ ሸምበሊና ፣ መንጠብጠብ ፣ ዓዲ ኣሰር ፣ ሰየምቲ አድያቦ እንደሁ ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል።
መረጃው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
የኤርትራ ሰራዊት በተቆጣጠራቸው የኢሮብ የኢትዮጵያ የትግራይ አከባቢዎች ለሚገኙ ነዋሪዎች ማስጠንቀቅያ ሲሰጥ የሚያሳይ የቪድዮ መረጃ የኢሮብ ብሄረሰብ ተወላጆችን አሰቆጥቷል።
የኤርትራ ሰራዊት ተወካይ የኢሮብ ተወላጆች ስብስቦ ማስጠንቀቅያ ሲሰጥ የሚያሳየው የቪድዮ መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በመሰራጨት ላይ ሲሆን በክልሉ ሚድያዎችም ሽፋን ሰጥተውታል።
የቪድዮው የድምፂ ቅጂ ምን ይላል ?
"... እናንተ ህዝብ ናችሁ። የምትኖሩበት መሬት ደግሞ የኤርትራ ነው። ኤርትራውያን ከሆናችሁ ለዚሁ አከባቢና መሬት ተገዢ እንዲሁም እዚህ ላለው ሰራዊት የማገዝ ግዴታ አለባችሁ።
አገራዊ አገልግሎት የመስጠት ግዴታም አለባችሁ። በትወልዱም በትጠሉም አንድ የኤርትራ ዜጋ የሚያሳልፈውን ህይወት ልታልፉ ግድ ይላል።
አንድ ሰው ከዚህ አከባቢ ወደ አገራዊ አገልግሎት ከሄደ ለኤርትራ አገሩ ብሎ ነው የሚሄደው። ስለዚህ እያንዳንዳችሁ አገራዊ አገልግሎት እንደሚመለከታችሁ ማወቅ አለባችሁ። አባቶች የሃይማኖት መሪዎች ስሙ ከመካከላችሁ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ካለ የኤርትራ መንግስት እዚህ አስገድዶ አያኖረውም። ወደ ኢትዮጵያ የመሄድ መብት አለው። የኤርትራ መሬት ደግሞ ኤርትራውያን ይኖሩበታል።
ወደ አገራዊ አገልግሎት መሄድ ካለብህ ትሄዳለህ፤ ረሃብ ካለ እንደ ሌላው ኤርትራዊ ትራባለህ። በቃ ተካፍለህ ትኖራለህ። ላንተ ተብሎ የሚደረግ የተለየ ነገር የለም። ልቅ የሆነ አካሄድ ነው የቆየው ይህ ከአሁን በኃላ አይቀጥልም። " ሲል ያስጠንቅቃል የኤርትራ ሰራዊት ተወካዩ።
ቪድዮውን የተመለከቱ የኢሮብ ብሄረሰብ ተወላጆች የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርና የፌደራል መንግስት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ከጥፋት እንዲታደግዋቸው ተማፅነዋል።
ብርሃን ወዲ ኢሮብ የተባለው የብሄረሰቡ ተወላጅ በሰጠው አስተያየት " ... አራት ዓመት ሙሉ በሁለት ተከፍለን ኮምፓስዋ እንደጠፋት መርከብ ሆነን ተሰፋችን ጨልሞብናል። ብሄረሰባችን እየጠፋ አረ የሰሚ ያለህ.." ሲል ምሬቱን ገልጿል።
የኤርትራ ሰራዊት በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ፦
- የዛላኣንበሳ ከተማ
- በጉሎመኸዳ ወረዳ ማርታ ፣ አዲስ ተስፋ ፣ አዲስ ዓለም ፣ ሸዊት ለምለምና ሰበያ
- በኢሮብ ወረዳ እንዳልጌዳ ፣ ወርዓትለ ዓገረ ሎኽማና ዓሊቴና የተባሉ የኢትዮጵያ አከባቢዎች ተቆጣጥሮ ይገኛል።
በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በታሕታይ ኣድያቦ የኩናማ ማህበረሰብና ሌሎች የሚኖሩባቸው ገማህሎ ፣ አደመይቲ ፣ የባድመ ከተማና አከባቢው ፣ ዓዲ ፀፀር ፣ ለምለም ሸዊት ፣ ሸምበሊና ፣ መንጠብጠብ ፣ ዓዲ ኣሰር ፣ ሰየምቲ አድያቦ እንደሁ ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወሳል።
መረጃው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ የኤርትራ ሰራዊት በተቆጣጠራቸው የኢሮብ የኢትዮጵያ የትግራይ አከባቢዎች ለሚገኙ ነዋሪዎች ማስጠንቀቅያ ሲሰጥ የሚያሳይ የቪድዮ መረጃ የኢሮብ ብሄረሰብ ተወላጆችን አሰቆጥቷል። የኤርትራ ሰራዊት ተወካይ የኢሮብ ተወላጆች ስብስቦ ማስጠንቀቅያ ሲሰጥ የሚያሳየው የቪድዮ መረጃ በማህበራዊ የትስስር ገፆች በመሰራጨት ላይ ሲሆን በክልሉ ሚድያዎችም ሽፋን ሰጥተውታል። የቪድዮው የድምፂ ቅጂ ምን ይላል ?…
#ትግራይ
የኤርትራ ሰራዊት ከሶስት የኢትዮጵያ የትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወረዳዎች ' 93 ወጣቶች ' አግቶ መሰወሩን የአካባቢው አስተዳዳሪዎች ገልጹ።
እገታው የተፈፀመው ኢትዮጵያ በትግራይ በኩል ከኤርትራ ከምትዋሰንባቸው የዛላንበሳ ከተማ የጉሎመኻዳ እና የኢሮብ ወረዳዎች ላይ ነው ተብሏል።
ይህን የተገለፀው የከተማ እና የወረዳዎቹ አስተዳዳሪዎች ከኤርትራ ድንበር በ35 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው የዓዲግራት ከተማ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ታዛቢዎች (AU military attaches) ባካሄዱት ውይይት ነው።
የዛላአንበሳ ከንቲባ መምህር ብርሀነ በርሀና ፣ የጉሎመኻዳ ዋና አስተዳዳሪ ሃፍቶም ባራኺ በጋራ ከአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ታዛቢዎች በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ :-
➡ በአከባቢያቸው የተለወጠ የፀጥታ ሁኔታ አለመኖሩ ፤
➡ ጦርነቱ ተከትሎ የተፈጠረው ችግር እንዳልተፈታ፤
➡ የኤርትራ ሰራዊት የዛላአንበሳ ከተማ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ፤
➡ ከዛላኣንበሳ ከተማ መግብያ በቅርብ ርቀት ዝባን ሑፃ ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ኬላ አቋቁሞ ፍተሻ እንደሚያካሂድ ፤
➡ የኤርትራ ሰራዊት ከዛላኣንበሳ ከተማ 15 ፣ በቁጥጥሩ ስር ከሚገኙ የጉሎመኻዳና የኢሮብ ወረዳዎች የተለያዩ ቀበሌዎች 78 ባጠቃላይ 93 ወጣቶች አግቶ የወሰዳቸው ወጣቶች ያሉበት ሁኔታ እንደማይታወቅ አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በኤርትራ ሰራዊት ቁጥጥር ስር በሚገኙ የጉሎመኻዳ እና የኢሮብ ወረዳዎች 10 ቀበሌዎች የሚኖር ህዝብ እርዳታ ጨምሮ የጤና የትምህርት እንዲሁም ሌሎች የመንግስት አገልግሎቶች እንደማያገኝ አስተዳዳሪዎቹ ለአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ታዛቢዎች በዝርዝር አስረድተዋል።
በስብሰባው ወቅት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች መሳተፋቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
የሀገር መከላከያ ሚንስትሩ ዶክተር አብራሃም በላይ በየካቲት 2016 ዓ.ም የመጨረሻው ሳምንት ላይ በትግርኛ ቋንቋ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለመጠይቅ ፥ " የሻብዕያ ሰራዊት " ብለው የገለፁት የኤርትራ ጦር ከኢትዮጵያ መሬት ስለመውጣት ጉዳይ ፤
" ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በፊት በበርካታ የትግራይ አከባቢዎች የሻዕብያ ሃይል ገብቶ ነበር ፣ ከስምምነቱ በኋላ እንዲወጣ ተደርጓል ፣ አሁንም የተቀሩ ቦታዎች ካሉ ቦታዎቹ እና ቀበሌዎች ከፌደራልና ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተውጣጣ ቡድን በዝርዝር አጥንቶ እንዲያቀርብና መፍትሄ እንዲሰጠው እየሰራን ነው ሁሉም ልክና መስመር ይይዛል " ማለታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
መረጃው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው የተዘጋጀው።
@tikvahethiopia
የኤርትራ ሰራዊት ከሶስት የኢትዮጵያ የትግራይ ምስራቃዊ ዞን ወረዳዎች ' 93 ወጣቶች ' አግቶ መሰወሩን የአካባቢው አስተዳዳሪዎች ገልጹ።
እገታው የተፈፀመው ኢትዮጵያ በትግራይ በኩል ከኤርትራ ከምትዋሰንባቸው የዛላንበሳ ከተማ የጉሎመኻዳ እና የኢሮብ ወረዳዎች ላይ ነው ተብሏል።
ይህን የተገለፀው የከተማ እና የወረዳዎቹ አስተዳዳሪዎች ከኤርትራ ድንበር በ35 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው የዓዲግራት ከተማ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ከአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ታዛቢዎች (AU military attaches) ባካሄዱት ውይይት ነው።
የዛላአንበሳ ከንቲባ መምህር ብርሀነ በርሀና ፣ የጉሎመኻዳ ዋና አስተዳዳሪ ሃፍቶም ባራኺ በጋራ ከአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ታዛቢዎች በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኃላ :-
➡ በአከባቢያቸው የተለወጠ የፀጥታ ሁኔታ አለመኖሩ ፤
➡ ጦርነቱ ተከትሎ የተፈጠረው ችግር እንዳልተፈታ፤
➡ የኤርትራ ሰራዊት የዛላአንበሳ ከተማ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ እንደሚገኝ፤
➡ ከዛላኣንበሳ ከተማ መግብያ በቅርብ ርቀት ዝባን ሑፃ ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ኬላ አቋቁሞ ፍተሻ እንደሚያካሂድ ፤
➡ የኤርትራ ሰራዊት ከዛላኣንበሳ ከተማ 15 ፣ በቁጥጥሩ ስር ከሚገኙ የጉሎመኻዳና የኢሮብ ወረዳዎች የተለያዩ ቀበሌዎች 78 ባጠቃላይ 93 ወጣቶች አግቶ የወሰዳቸው ወጣቶች ያሉበት ሁኔታ እንደማይታወቅ አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በኤርትራ ሰራዊት ቁጥጥር ስር በሚገኙ የጉሎመኻዳ እና የኢሮብ ወረዳዎች 10 ቀበሌዎች የሚኖር ህዝብ እርዳታ ጨምሮ የጤና የትምህርት እንዲሁም ሌሎች የመንግስት አገልግሎቶች እንደማያገኝ አስተዳዳሪዎቹ ለአፍሪካ ህብረት ወታደራዊ ታዛቢዎች በዝርዝር አስረድተዋል።
በስብሰባው ወቅት የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተወካዮች መሳተፋቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትግራይ ምስራቃዊ ዞን ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
የሀገር መከላከያ ሚንስትሩ ዶክተር አብራሃም በላይ በየካቲት 2016 ዓ.ም የመጨረሻው ሳምንት ላይ በትግርኛ ቋንቋ ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃለመጠይቅ ፥ " የሻብዕያ ሰራዊት " ብለው የገለፁት የኤርትራ ጦር ከኢትዮጵያ መሬት ስለመውጣት ጉዳይ ፤
" ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በፊት በበርካታ የትግራይ አከባቢዎች የሻዕብያ ሃይል ገብቶ ነበር ፣ ከስምምነቱ በኋላ እንዲወጣ ተደርጓል ፣ አሁንም የተቀሩ ቦታዎች ካሉ ቦታዎቹ እና ቀበሌዎች ከፌደራልና ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የተውጣጣ ቡድን በዝርዝር አጥንቶ እንዲያቀርብና መፍትሄ እንዲሰጠው እየሰራን ነው ሁሉም ልክና መስመር ይይዛል " ማለታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
መረጃው በመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው የተዘጋጀው።
@tikvahethiopia