TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አዎ! ዛሬ ቁጭ ብለህ በፌስቡክ ላይ ፃፍ፣ ተሳደብ፣ ቀስቅስ፣ ሰዎችን አጋጭ፣ በሆነው ባልሆነው፤ በረባው ባልረባው ተባላ ...ነገ ሀገር #ሲተራመስ -- ኔትዎርኩ ሲዘጋ፤ መብራቱ ሲጠፋ፤ ውሀው ሲቋረጥ፤ የምትበላው ስታጣ፤ ገንዘብ በኪስህ ሞልቶ ለሻይ እንኳን ከቤትህ ለመውጣት ሲያቅትህ የት እንደምትገባ ግራ ይገባሀል። ዛሬ ያቀለልካት #ሰላም ደም እምባ ብታለቅስ መልሰህ አታገኛትም።
.
.
ዛሬማ ሰላም ነው #ፎክር እንጂ...የቤትህ አናት ላይ ሲተኮስ፤ የቦንብ ናዳው ሲውርድ፤ ሰው ወጥቶ ሲቀር ስትሰማ፤ ህፃናት #ሲረግፉ ስታይ፤ ህዝብ እየተሰደደ የበረሀ ሲሳይ ሲሆን፥ ባህር ውስጥ ሰጥሞ ሲቀር ስታይ...የዛሬዋን ቀን #ትረግማታለህ። ምነው ጌታ ባልፈጠርከኝ ትላለህ። ብቻህን ያለወንድም፤ ያለእናት አባት፤ ያለዘመድ ስትቀር መፈጠርህን ትጠላለህ። ዛሬ ያቀለልካትን ሰላም ደም እምባ ብታለቅስ መልሰህ አታገኛትም።

.
.
ዛሬማ ሰላም ነው ፎክር...አቅራራ...ህዝብ ቀስቅስ...ተነሳ በለው፣ ግደለው በል!
.
.
የለኮስከው #እሳት አመድ ሲያደርግህ የሰላምን #ዋጋ ያን ጊዜ ትረዳዋለህ!

#ETHIOPIA
ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዎ! ዛሬ ቁጭ ብለህ በፌስቡክ ላይ ፃፍ፣ ተሳደብ፣ ቀስቅስ፣ ሰዎችን አጋጭ፣ በሆነው ባልሆነው፤ በረባው ባልረባው ተባላ ...ነገ ሀገር #ሲተራመስ -- ኔትዎርኩ ሲዘጋ፤ መብራቱ ሲጠፋ፤ ውሀው ሲቋረጥ፤ የምትበላው ስታጣ፤ ገንዘብ በኪስህ ሞልቶ ለሻይ እንኳን ከቤትህ ለመውጣት ሲያቅትህ የት እንደምትገባ ግራ ይገባሀል። ዛሬ ያቀለልካት #ሰላም ደም እምባ ብታለቅስ መልሰህ አታገኛትም።
.
.
ዛሬማ ሰላም ነው #ፎክር እንጂ...የቤትህ አናት ላይ ሲተኮስ፤ የቦንብ ናዳው ሲውርድ፤ ሰው ወጥቶ ሲቀር ስትሰማ፤ ህፃናት #ሲረግፉ ስታይ፤ ህዝብ እየተሰደደ የበረሀ ሲሳይ ሲሆን፥ ባህር ውስጥ ሰጥሞ ሲቀር ስታይ...የዛሬዋን ቀን #ትረግማታለህ። ምነው ጌታ ባልፈጠርከኝ ትላለህ። ብቻህን ያለወንድም፤ ያለእናት አባት፤ ያለዘመድ ስትቀር መፈጠርህን ትጠላለህ። ዛሬ ያቀለልካትን ሰላም ደም እምባ ብታለቅስ መልሰህ አታገኛትም።

.
.
ዛሬማ ሰላም ነው ፎክር...አቅራራ...ህዝብ ቀስቅስ...ተነሳ በለው፣ ግደለው በል!
.
.
የለኮስከው #እሳት አመድ ሲያደርግህ የሰላምን #ዋጋ ያን ጊዜ ትረዳዋለህ!

#ETHIOPIA
ፀጋአብ ወልዴ~ኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ዋጋ

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ያለአገልግሎት የተከማቹ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ በስክራፕ መልክ የሚወገዱ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎችን መሸጫ የዋጋ ዝርዝር ይፋ ሆኗል።

1ኛ. ስቲል - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር)  64.00

2. ካስት አይረን  - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር) 51.75

3. አልሙኒየም - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (ብር) 120.00

4. ስክራፕ ያደረገ ተሽከርካሪ / ማሽነሪ - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ (በብር) 51.25

5. ያገለገለ የተሽከርካሪ / ማሽነሪ መለዋወጫ - የአንድ ኪሎ ማስረከቢያ ዋጋ  (በብር) 51.25

በዚህ መሰረት መሰሪያ ቤቶች ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶችን የማዕድን ሚኒስቴር ለሚመድብላቸው የብረታ ብረት አቅላጭ ኢንዱስትሪ/ለአምራች ኢንዱስትሪ #ብቻ በቀጥታ እንዲሸጡ ከሽያጭም የሚገኘውን ገንዘብ ወደ መንግስት ማዕከላዊ ግ/ቤት የባንክ አካውንት ገቢ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

(ለተጨማሪ መረጃ ከላይ የተያያዙትን ደብዳቤዎች ይመልከቱ)

Credit : M. (Tikvah Family)

@tikvahethiopia