TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Kombolcha

#ሙሉ_በሙሉ የግንባታ ወጭው በውጭ ሀገራት በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራዎች የሚሸፈን መልቲ ጀነራል ሆስፒታል የመሰረት ድንጋይ የቀመጠ።

ሆስፒታሉ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ የሚገነባ ሲሆን ከ300 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ይሆንበታል ተብሏል።

ፕሮጀክቱ በ1 ነጥብ 6 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ወጪው ሙሉ በሙሉ በውጭ ሀገራት በሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚሸፈን ነው።

በወረዳው ለሚገነባው ሆስፒታል የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ጀማል ዪስፍ፣ የኮምቦልቻ ወረዳ አስተዳደር አቶ አልዪ ኢብራሂም እና የዲያስፖራ ተወካይ አቶ ፈረሃን አህመድ የመሰረት ድንጋዩን አስቀምጠዋል።

#ENA

@tikvahethiopia
#Somali #Afar

በሶማሌ እና አፋር ክልል አዋሳኝ ቀበሌዎች የሚከሰቱ ግጭቶችን በዘላቂነት መፍታት እንዲቻል 2ቱ ክልሎች ከስምምነት መድረሳቸውን አስታወቁ።

ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት ያስችላል የተባለው መሠረታዊ ስምምነት የታጠቁ ኃይሎች ከግጭት አካባቢዎች እንዲወጡ እና የፌደራል ፀጥታ ኃይሎች ወደነዚህ ቦታዎች እንዲገቡ የሚፈቅድ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን መናገራቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

በአዋሳኝ ቀበሌዎች በየቦታው ተኩስ ፣ ስርቆት እና መፈናቀል ይከሰቱ እንደነበር የተናገሩት አቶ ኢብራሂም ዘላቂ ሰላም ለማምጣትም የተፈናቀሉ ሰዎችን ወደቀያቸው መመለስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ኢብራሂም « ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ችግር እንዳይከሰት፣… ዘላቂ የሆነ ሰላም እንዲመጣ እና ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ሚና መሆን እንዳለበትም ነው ትናንት ከስምምነት ላይ የደረስነው።» ብለዋል።

የሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን ማሣረጊያ እንዲሆን የሁለቱ ክልሎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ኮንፈረንስ እንደሚያካሂዱም ተናግረዋል።

በሶማሌ ክልል መቀመጫ ጅግጅጋ በተካሄደው ውይይት የሰላም ሚንስትሩ አቶ ብናልፍ አንዱአለም ጨምሮ የአፋር እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት ተገኝተው እንደነበር ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ በጎረቤታችን ሶማሊያ ቀጣዩ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት የሚታወቅበት ምርጫ እየተካሄደ ይገኛል። በአሁን ሰዓት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እየተካሄደ ነው። ይህ የዛሬው ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ለ6ኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን ረጅም ጊዜ ሲጠበቅ ነበር። ቀጥተኛ ባልሆነው በዚህ ምርጫ ላይ 30 በላይ እጩዎች እየተወዳደሩ ይገኛሉ። @tikvahethiopia
#Update

የጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ምርጫ ፦

የመጀመሪያው ዙር ውጤት :

👉 ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ➡️ 65
👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 59
👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 52
👉 ሀሰን አሊ ኻይሬ ➡️ 47

⬇️

👉 ሸሪፍ ሼክ አህመድ ➡️ 39
👉 አብዲራህማን ዋርሳሜ ➡️ 15
👉 አብዱልቃድር ኦሶብል ➡️ 12
👉 አዶው አሊ ጊስ ➡️ 8


328 የፓርላማ አባላት ድምጽ የሰጡ ሲሆን 4 ከፍተኛ ድምፅ ያገኙ ወደ 2ኛው ዙር አልፈዋል።

በአሁን ሰዓት የሁለተኛ ዙር ድምፅ አሰጣጥ እየተካሄደ ይገኛል።

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ሀሩን ማሩፍ (ቪኦኤ)

@tikvahethiopia
" አሽከርካሪዎች የሚያሽከረክሩትን የመኪና አቅምና በወንበር ልክ ጭነው በማሽከርከር የህብረተሰቡን ህይወት መጠበቅ ይገባቸዋል " - ፖሊስ

ዛሬ ጥዋት 2 ሰዓት ላይ በቦረና ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሠዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።

በደቡብ ወሎ ዞን በቦረና ወረዳ 019 ቀበሌ " መንደዩ " ከተባለው ቦታ መነሻውን መካነ-ሠላም አድርጎ ወደ መርጦለማሪያም ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በደረሠበት የመገልበጥ አደጋ አሽከርካሪውን ጨምሮ የ6 ሠዎች ህይወት ሲያልፍ 9 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳትና የ11 ሠዎች ቀላል የአካል ጉዳት መከሰቱን የቦረና ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

ፖሊስ እንደገለፀው አደጋው የደረሰበት ኮድ 3 ታርጋ ቁጥር 18872 አ.ማ የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ሲሆን ከጠዋቱ በግምት 2:00 ሰዓት ሲሆን 26 ተሳፊሪዎችን ጭኖ ከ75 ሜትር ገደል ገብቷል።

እንደ ፖሊስ መረጃ መኪናው ከአቅም በላይ መጫኑ ነው የተገለፀው።

ፖሊስ አሽከርካሪዎች የሚያሽከረክሩትን የመኪና አቅምና በወንበር ልክ ጭነው በማሽከርከር የህብረተሰቡን ህይወት መጠበቅ ይገባቸዋል ብሏል።

መረጀው የወረዳው መንግስት ኮሙንኬሽን አገልግሎት ፅ/ቤት ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ምርጫ ፦ የመጀመሪያው ዙር ውጤት : 👉 ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ➡️ 65 👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 59 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 52 👉 ሀሰን አሊ ኻይሬ ➡️ 47 ⬇️ 👉 ሸሪፍ ሼክ አህመድ ➡️ 39 👉 አብዲራህማን ዋርሳሜ ➡️ 15 👉 አብዱልቃድር ኦሶብል ➡️ 12 👉 አዶው አሊ ጊስ ➡️ 8 328 የፓርላማ አባላት ድምጽ የሰጡ ሲሆን 4 ከፍተኛ…
#Update

በጎረቤታችን ሶማሊያ እየተካሄደ በሚገኘው ምርጫ የ2ኛው ዙር ድምፅ አሰጣጥ ሂደት አብቅቷል ፤ ይህን ተከትሎ የድምጽ ቆጠራው ይካሄዳል።

#ማስታወሻ ፦ የመጀመሪያው ዙር ውጤት ፦

👉 ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ➡️ 65
👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 59
👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 52
👉 ሀሰን አሊ ኻይሬ ➡️ 47

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በጎረቤታችን ሶማሊያ እየተካሄደ በሚገኘው ምርጫ የ2ኛው ዙር ድምፅ አሰጣጥ ሂደት አብቅቷል ፤ ይህን ተከትሎ የድምጽ ቆጠራው ይካሄዳል። #ማስታወሻ ፦ የመጀመሪያው ዙር ውጤት ፦ 👉 ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ➡️ 65 👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 59 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 52 👉 ሀሰን አሊ ኻይሬ ➡️ 47 @tikvahethiopia
#ሶማሊያ

እጅግ ከባድ ፉክክር እየታየበት በሚገኘው የሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የሁለተኛው ዙር ድምፅ አሰጣጥ ተጠናቆ የድምፅ ቆጠራው እየተካሄደ ይገኛል።

የ2ኛው ዙር የምርጫ ውጤትን እንዲሁም አጠቃላይ የምርጫውን ሂደት ከሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እየተከታተል እንልክላችኃለን።

ቀጣዩ የጎረቤታችን ሶማሊያ ፕሬዜዳንት ማን ይሆን ? አብረን የምናየው ይሆናል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሶማሊያ እጅግ ከባድ ፉክክር እየታየበት በሚገኘው የሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የሁለተኛው ዙር ድምፅ አሰጣጥ ተጠናቆ የድምፅ ቆጠራው እየተካሄደ ይገኛል። የ2ኛው ዙር የምርጫ ውጤትን እንዲሁም አጠቃላይ የምርጫውን ሂደት ከሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እየተከታተል እንልክላችኃለን። ቀጣዩ የጎረቤታችን ሶማሊያ ፕሬዜዳንት ማን ይሆን ? አብረን የምናየው ይሆናል። @tikvahethiopia
#Update

የሶማሊያ ምርጫ ሁለተኛው ዙር ውጤት ፦

በሁለተኛው ዙር የቀድሞ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ አንደኛ አሁን ሶማሊያን በፕሬዜዳንትነት እየመሩ ያሉት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ሁለተኛ ሆነው አጠናቀዋል።

እንዲሁም ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ሶስተኛ ፤ ሀሰን አሊ ኻይሬ አራተኛ ሆነው የ2ኛውን ዙር የምርጫ ፉክክር አጠናቀዋል።

የምርጫው ውጤት በቁጥር ፦

👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 110

👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 83

👉 ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ➡️ 68

👉 ሀሰን አሊ ኻይሬ ➡️ 63

በፋርማጆ እና ሀሰን ሼክ መካከል ሶስተኛውና የመጨረሻው ዙር የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ፉክክር ይካሄዳል።

የምርጫውን ሂደት ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ምርጫ ሁለተኛው ዙር ውጤት ፦ በሁለተኛው ዙር የቀድሞ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ አንደኛ አሁን ሶማሊያን በፕሬዜዳንትነት እየመሩ ያሉት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ሁለተኛ ሆነው አጠናቀዋል። እንዲሁም ሰዒድ አብዱላሂ ዴኒ ሶስተኛ ፤ ሀሰን አሊ ኻይሬ አራተኛ ሆነው የ2ኛውን ዙር የምርጫ ፉክክር አጠናቀዋል። የምርጫው ውጤት በቁጥር ፦ 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 110 👉 ሞሀመድ…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ በሞቃዲሾ ካራን እና አብዲአዚዝ አካባቢዎች በደስታ ተኩስ እሩምታ እየተናጡ ናቸው።

አካባቢዎቹን በተኩስ እሩምታ እየናጡ የሚገኙት በሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለ3ኛውና የመጨረሻ ዙር የደረሱት የሀሰን ሼክ ሞሐመድ ደጋፊዎች ናቸው ተብሏል።

በመጨረሻውና ሶስተኛው ዙር የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ከወቅቱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ጋር ይፎካከራሉ።

የመጨረሻው የምርጫ ውጤት በሶማሊያ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካ ቀንድ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።

በሶስተኛው ዙር ከሁለት አንዱ 165 ድምፅ ያገኘው ምርጫውን በድል ያጠናቅቃል፤ ቀጣዩ የሶማሊያ ፕሬዜዳንትነትም ይሆናል።

ፈርማጆ አልያም ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ ማን ቀጣዩ የጎረቤት ሀገር ፕሬዝዳንት ይሆናል ? የሶስተኛው ዙር ምርጫ ምላሽ ይሰጠናል።

Credit : Morad

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቪድዮ ፦ በሞቃዲሾ ካራን እና አብዲአዚዝ አካባቢዎች በደስታ ተኩስ እሩምታ እየተናጡ ናቸው። አካባቢዎቹን በተኩስ እሩምታ እየናጡ የሚገኙት በሶማሊያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለ3ኛውና የመጨረሻ ዙር የደረሱት የሀሰን ሼክ ሞሐመድ ደጋፊዎች ናቸው ተብሏል። በመጨረሻውና ሶስተኛው ዙር የፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ከወቅቱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ጋር ይፎካከራሉ። የመጨረሻው የምርጫ…
#Update

በሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የመጨረሻው ዙር የድምፅ አሰጣጥ ተጠናቋል።

በቀጣይ የድምፅ ቆጠራው ይካሄዳል።

በመጨረሻው ዙር ምርጫ ፈርማጆ አልያም ደግሞ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፉክክሩን በድል ያጠናቅቃሉ።

ፈርማጆ ካሸነፉ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሆነው ዳግም ይመረጣሉ ፤ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ካሸነፉ ከፈርማጆ በፊት የነበሩበትን የፕሬዜዳንትነት መንበር በመረከብ ሀገራቸውን ዳግም የመምራት እድልን ያገኛሉ።

#ማስታወሻ ፦ የሁለተኛው ዙር ውጤት ፦

👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 110

👉 ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 83

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ የመጨረሻው ዙር የድምፅ አሰጣጥ ተጠናቋል። በቀጣይ የድምፅ ቆጠራው ይካሄዳል። በመጨረሻው ዙር ምርጫ ፈርማጆ አልያም ደግሞ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፉክክሩን በድል ያጠናቅቃሉ። ፈርማጆ ካሸነፉ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሆነው ዳግም ይመረጣሉ ፤ ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ካሸነፉ ከፈርማጆ በፊት የነበሩበትን የፕሬዜዳንትነት መንበር በመረከብ ሀገራቸውን ዳግም የመምራት እድልን ያገኛሉ።…
#ሰበር_ዜና

የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ በድጋሚ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሆነው ተመረጡ።

ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል።

የመጨረሻ ውጤት ፦

👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 214 ድምፅ
👉 ሞሐመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 110 ድምፅ

3 ድምፅ ዋጋ ቢስ ሆኗል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሰበር_ዜና የቀድሞው የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ በድጋሚ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሆነው ተመረጡ። ሀሰን ሼክ ሞሐመድ የአሁኑን የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሞሀመድ አብድላሂ ፈርማጆን እጅግ ፉክክር በተሞላበት ሶስት ዙር የምርጫ ሂደት አሸንፈዋቸዋል። የመጨረሻ ውጤት ፦ 👉 ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ➡️ 214 ድምፅ 👉 ሞሐመድ አብዱላሂ ፈርማጆ ➡️ 110 ድምፅ 3 ድምፅ ዋጋ ቢስ ሆኗል። @tikvahethiopia
#BREAKING

የሶማሊያ ፌደራል ፓርላማ ሀሰን ሼክ ሞሀመድን የሀገሪቱ 10ኛ ፕሬዝዳንት አድርጎ መርጧል።

አዲሱ ፕሬዜዳንት እ.ኤ.አ. ከመስከረም 2012 እስከ የካቲት 16 / 2017 ድረስ በፕሬዝዳንትነት አገልግለዋል።

ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ተሰናባቹን ፕሬዝዳንት ሞሀመድ አብዱላሂ ፈርማጆን በማሸነፍ በሶማሊያ ታሪክ ለሁለት ጊዜ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡ የመጀመሪያው ሰው መሆን ችለዋል።

ምንጭ፦ የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia