TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ቅዱስ ፓትርያርኩ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት ህክምናቸውን በመከታተል ላይ ይገኛሉ። በዚህም መሰረት ቅዱስነታቸው በአሁኑ ሰዓት በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ህክምናቸውን በንቃት እየተከታተሉ እንደሚገኙ ታውቋል።…
#Update
ቅዱስ ፓትርያርኩ ህክምናቸውን ጨርሰው ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተመለሱ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሆስፒታል ሲደረግላቸው የነበረውን ህክምና ጨርሰው በሙሉ ጤንነት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ በሰላም ተመልሰዋል።
መረጃውን ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው ያገኘነው።
@tikvahethiopia
ቅዱስ ፓትርያርኩ ህክምናቸውን ጨርሰው ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተመለሱ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሆስፒታል ሲደረግላቸው የነበረውን ህክምና ጨርሰው በሙሉ ጤንነት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ በሰላም ተመልሰዋል።
መረጃውን ከኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው ያገኘነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba 📍ቦሌ አትላስ አካባቢ የደረሰው አደጋ 9:20 አካባቢ በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል። ዛሬ ከሰዓት 8 ሰዓት አካባቢ ቦሌ አትላስ አካባቢ የሚገኙት የግንባታ ዕቃዎች መጋዘኖች ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ተነስቶ በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል። የእሳት አደጋው በቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስትያን እና በአትላስ እንዲሁም በፀጋ ሆስፒታል መሃል ላይ በሚገኙት የንግድ ሱቆች መጋዘኖች ላይ የደረሰው።…
#Update
" በእሳት አደጋው 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል " - የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን
በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ አትላስ አካባቢ በደረሰው የእሳት አደጋ 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳውቋል።
በአደጋው ከንብረት ውድመት በቀር በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ባደረጉት ጥረት ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ከውድመት ማዳን መቻሉም ተገልጿል።
8 ሰዓታትን በፈጀው እሳት የማጥፋት ሥራ 119 የአደጋ መከላከል ባለሙያዎች መሳተፋቸውንም ተናግሯል፡፡
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥የአደጋው መንስኤ አለመታወቁንና 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መጋዘን ሙሉ በሙሉ መውደሙን ተናግረዋል፡፡
አደጋውን ለመቆጣጠር 14 የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዎች፣ 2 አምቡላንሶች፣ 142,000 ሊትር ውሃ እና 155 ሊትር ኬሚካል ጥቅም ላይ መዋሉንም አሳውቀዋል።
ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1
@tikvahethiopia
" በእሳት አደጋው 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል " - የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን
በትናንትናው ዕለት በአዲስ አበባ አትላስ አካባቢ በደረሰው የእሳት አደጋ 2.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳውቋል።
በአደጋው ከንብረት ውድመት በቀር በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ባደረጉት ጥረት ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ከውድመት ማዳን መቻሉም ተገልጿል።
8 ሰዓታትን በፈጀው እሳት የማጥፋት ሥራ 119 የአደጋ መከላከል ባለሙያዎች መሳተፋቸውንም ተናግሯል፡፡
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ፥የአደጋው መንስኤ አለመታወቁንና 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መጋዘን ሙሉ በሙሉ መውደሙን ተናግረዋል፡፡
አደጋውን ለመቆጣጠር 14 የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዎች፣ 2 አምቡላንሶች፣ 142,000 ሊትር ውሃ እና 155 ሊትር ኬሚካል ጥቅም ላይ መዋሉንም አሳውቀዋል።
ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም 102.1
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ወይብላ_ማርያም የኢ.ኦ.ተ.ቤ. መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት ፥ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ መቅደሷ ሳትገባ ወደ ኋላ ተመልሳ ቀራንዮ መድኃኔዓለም የቆየችውን ወይብላ ማርያም ታቦትን ለማስገባት ምእመናንንም ለማጽናናት በቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን መገኘታቸውን አሳውቋል። ከእርሳቸው ጋር የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ…
#UPDATE
" መንግሥት ማጣራት በማድረግ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ ያቀርባል " - የመንግስት ኮሚኒኬሽን
የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፤ የጥምቀት በዓል በመላ ኢትዮጵያ በደመቀና በሰላማዊ መንገድ ቢከበርም በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ እና በቡራዩ አዋሳኝ ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን አካባቢ በተፈጠረው ችግር በዓሉ መስተጓጎሉና በሰዎች ላይም ሞትና ከባድ ጉዳት መድረሱን አሳውቋል።
በዓሉ በተገቢው መንገድ ባለመከበሩ፣ እንዲሁም በደረሰው የሰው ሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት መንግሥት ጥልቅ ኀዘን እንደተሰማው ገልጿል።
መንግሥት በስፍራው የተፈጠረውን ክሥተት በማጣራት ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ እንደሚያቀርብም አስታውቋል።
" ለዘመናት የኢትዮጵያዊነታችን መገለጫ እንዲሁም የጠንካራ ማኅበራዊ መስተጋብራችን ማሳያ በሆኑ እንደ ጥምቀት በዓል ያሉ ሀብቶቻችንን ለማደብዘዝ የሚደረግ ማንኛውም ጥረት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር ይከሽፋል። " ብሏል።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
" መንግሥት ማጣራት በማድረግ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ ያቀርባል " - የመንግስት ኮሚኒኬሽን
የኢትዮጵያ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፤ የጥምቀት በዓል በመላ ኢትዮጵያ በደመቀና በሰላማዊ መንገድ ቢከበርም በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ እና በቡራዩ አዋሳኝ ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን አካባቢ በተፈጠረው ችግር በዓሉ መስተጓጎሉና በሰዎች ላይም ሞትና ከባድ ጉዳት መድረሱን አሳውቋል።
በዓሉ በተገቢው መንገድ ባለመከበሩ፣ እንዲሁም በደረሰው የሰው ሕይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት መንግሥት ጥልቅ ኀዘን እንደተሰማው ገልጿል።
መንግሥት በስፍራው የተፈጠረውን ክሥተት በማጣራት ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለሕግ እንደሚያቀርብም አስታውቋል።
" ለዘመናት የኢትዮጵያዊነታችን መገለጫ እንዲሁም የጠንካራ ማኅበራዊ መስተጋብራችን ማሳያ በሆኑ እንደ ጥምቀት በዓል ያሉ ሀብቶቻችንን ለማደብዘዝ የሚደረግ ማንኛውም ጥረት በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር ይከሽፋል። " ብሏል።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ወይብላ_ማርያም የኢ.ኦ.ተ.ቤ. መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት ፥ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ መቅደሷ ሳትገባ ወደ ኋላ ተመልሳ ቀራንዮ መድኃኔዓለም የቆየችውን ወይብላ ማርያም ታቦትን ለማስገባት ምእመናንንም ለማጽናናት በቀራንዮ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን መገኘታቸውን አሳውቋል። ከእርሳቸው ጋር የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ…
#Update
የማኅደረ ስብሀት ወይብላ ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ወደ መንበረ ክብራቸው ገቡ።
የማኅደረ ስብሐት ወይብላ ቅድስት ማርያምና የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ትላንት ካደሩበት ቀራንዮ መድኅኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ ፣ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ፣በአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ በብዙ መቶ ሺዎች በሚቆጠሩ ምእመናን ታጅቦ ወደ መንበረ ክብሩ ገብቷል።
በትላንትናው ዕለት የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ህይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ ፤ ከደብሩ ኃላፊ፣ ከወጣቶች ተወካዮች እንዲሁም ከምእመናን ተወካዮች ጋር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ 6 ሰዓታትን የፈጀ ውይይት በማድረግ በቀጣይ ቀናት አሉ የተባሉ ጥያቄዎችን በተመለከተ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር በኩል እንዲቀርብ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የተፈጠረውን ችግር በተመለከተ ከካህናት ፣ ከሰንበት ትምህርት ቤትና ከምዕመናን ተወካዮች ተውጣጥቶ ከተቋቋመው ኮሚቴ ጋር በጋራ ለመስራትና ጥያቄዎቹ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ ተቋማዊ የሆነ አሰራርን ተከትሎ በቅድሚያ ለአ/አ ሀገረ ስብከት እንዲቀርብ ስምምነት ላይ መደረሱ መታወቁን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ገልጿል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫው በትላንትናው ክስተት የሰው ህይወት መጥፋቱን በማረጋገጥ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለህግ እንደሚያቀርብ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የማኅደረ ስብሀት ወይብላ ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ወደ መንበረ ክብራቸው ገቡ።
የማኅደረ ስብሐት ወይብላ ቅድስት ማርያምና የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ትላንት ካደሩበት ቀራንዮ መድኅኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ ፣ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ፣በአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ በብዙ መቶ ሺዎች በሚቆጠሩ ምእመናን ታጅቦ ወደ መንበረ ክብሩ ገብቷል።
በትላንትናው ዕለት የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ህይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ክፍል ኃላፊ ፤ ከደብሩ ኃላፊ፣ ከወጣቶች ተወካዮች እንዲሁም ከምእመናን ተወካዮች ጋር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ 6 ሰዓታትን የፈጀ ውይይት በማድረግ በቀጣይ ቀናት አሉ የተባሉ ጥያቄዎችን በተመለከተ በቤተ ክርስቲያን መዋቅር በኩል እንዲቀርብ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የተፈጠረውን ችግር በተመለከተ ከካህናት ፣ ከሰንበት ትምህርት ቤትና ከምዕመናን ተወካዮች ተውጣጥቶ ከተቋቋመው ኮሚቴ ጋር በጋራ ለመስራትና ጥያቄዎቹ በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ ተቋማዊ የሆነ አሰራርን ተከትሎ በቅድሚያ ለአ/አ ሀገረ ስብከት እንዲቀርብ ስምምነት ላይ መደረሱ መታወቁን የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ገልጿል።
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫው በትላንትናው ክስተት የሰው ህይወት መጥፋቱን በማረጋገጥ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑ አካላትን ለህግ እንደሚያቀርብ ገልጿል።
@tikvahethiopia
#twitter
ትዊተር ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ "ህግ የጣሱ " ያላቸዉን ተጠቃሚዎች ማገዱን ዛሬ አሳውቋል።
ትዊተር እንዳለው ብዙ አካዉንቶች ታግደዋል፤ ከታገዱት መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩት የትግራይ ደጋፊ ተጠቃሚዎች ይመስላሉ ብሏል።
ይሁንና ትዊተር የታገደዉ አካዉንት መጠን ምን ያህል እንደሆን በውል አልገለፀም።
ትዊተር እርምጃዉ የተወሰደው "የትዊተርን ህግ በመጣስ፣ የተወሰኑ ሃሽታጎች እና የትዊተር ገፆች፤ በተለጠፈዉ መረጃ ላይ በተደጋጋሚ በአላስፈላጊ ሁኔታዎች በማካተታቸው ነው። በተጨማሪ ርምጃዉ " በኢትዮጵያ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተገናኘ በትዊተር ላይ የሚደረጉ ውይይቶች ደኅንነታቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲሄድ ከምናደርገው ጥረት ጋር የተገናኘ ነው " ብሏል።
እገዳዉን በተመለከተ " በተጨባጭ በአካውንቶቹና ይዘቶቹ ላይ ያተኮሩ " መሆኑን እና " ከፖለተካዊ ማንነት እና ርዕዮተ ዓለም ገለልተኞች ነን " ሲል ገልጿል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ / ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
ትዊተር ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ጋር በተያያዘ "ህግ የጣሱ " ያላቸዉን ተጠቃሚዎች ማገዱን ዛሬ አሳውቋል።
ትዊተር እንዳለው ብዙ አካዉንቶች ታግደዋል፤ ከታገዱት መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩት የትግራይ ደጋፊ ተጠቃሚዎች ይመስላሉ ብሏል።
ይሁንና ትዊተር የታገደዉ አካዉንት መጠን ምን ያህል እንደሆን በውል አልገለፀም።
ትዊተር እርምጃዉ የተወሰደው "የትዊተርን ህግ በመጣስ፣ የተወሰኑ ሃሽታጎች እና የትዊተር ገፆች፤ በተለጠፈዉ መረጃ ላይ በተደጋጋሚ በአላስፈላጊ ሁኔታዎች በማካተታቸው ነው። በተጨማሪ ርምጃዉ " በኢትዮጵያ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተገናኘ በትዊተር ላይ የሚደረጉ ውይይቶች ደኅንነታቸው በተጠበቀ መልኩ እንዲሄድ ከምናደርገው ጥረት ጋር የተገናኘ ነው " ብሏል።
እገዳዉን በተመለከተ " በተጨባጭ በአካውንቶቹና ይዘቶቹ ላይ ያተኮሩ " መሆኑን እና " ከፖለተካዊ ማንነት እና ርዕዮተ ዓለም ገለልተኞች ነን " ሲል ገልጿል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ / ዶቼቨለ
@tikvahethiopia
ግዙፉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህንፃ ሊመረቅ ነው።
ባንኩ ፥ " ከምስራቅ አፍሪካ ረጅሙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ የዋና መ/ቤት ህንፃ ምርቃት ከባንኩ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጋር ገጥሟል፡ " ብሏል።
በትክክል የሚመረቅበት ቀን ይፋ ይሆንም በቅርቡ ግን ህንፃው እንደሚመረቅ ተገልጿል።
@tikvahethiopia
ባንኩ ፥ " ከምስራቅ አፍሪካ ረጅሙ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲሱ የዋና መ/ቤት ህንፃ ምርቃት ከባንኩ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ጋር ገጥሟል፡ " ብሏል።
በትክክል የሚመረቅበት ቀን ይፋ ይሆንም በቅርቡ ግን ህንፃው እንደሚመረቅ ተገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የማኅደረ ስብሀት ወይብላ ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ወደ መንበረ ክብራቸው ገቡ። የማኅደረ ስብሐት ወይብላ ቅድስት ማርያምና የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ትላንት ካደሩበት ቀራንዮ መድኅኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ ፣ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ፣በአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ በብዙ መቶ…
" እየተፈጠረብን ያለውን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል" - ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ
የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው " እየተፈጠረብን ያለውን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል" ሲሉ አስታውቀዋል።
ብፁዕነታቸው በቦታው ተገኝተው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያፅናኑ እና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን እየተፈጠሩ ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች እስከ ሕይወት መስዋዕትነት እያስከፈለ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል ሲል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በፌስ ቡክ ገጹ አስነብቧል።
የተፈጠረውን ችግር ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ሪፖርት ማድረጋቸውን በመግለፅ ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ብፁዕነታቸው አስታውቀዋል።
አክለውም ብፁዕነታቸው ምዕመናን አንድነታቸውንና ኅብረታቸውን በማጠናከር ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ እንዳለባቸው አሳስበዋል ሲል ሀገረ ስብከቱ ገልጿል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው " እየተፈጠረብን ያለውን ችግር ለመፍታት ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል" ሲሉ አስታውቀዋል።
ብፁዕነታቸው በቦታው ተገኝተው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያፅናኑ እና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን እየተፈጠሩ ያሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች እስከ ሕይወት መስዋዕትነት እያስከፈለ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል ሲል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በፌስ ቡክ ገጹ አስነብቧል።
የተፈጠረውን ችግር ለቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ሪፖርት ማድረጋቸውን በመግለፅ ቅዱስ ሲኖዶስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ብፁዕነታቸው አስታውቀዋል።
አክለውም ብፁዕነታቸው ምዕመናን አንድነታቸውንና ኅብረታቸውን በማጠናከር ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ እንዳለባቸው አሳስበዋል ሲል ሀገረ ስብከቱ ገልጿል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት
@tikvahethiopia
#Tigray
በትግራይ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ሕይወት አደጋ እንደተጋረጠበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አስታወቀ።
በጦርነቱ ምክንያት የስደተኞቹ ኑሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበላሸ መሆኑንም ገልጿል።
በቅርቡ ማይ ዓይኒ እና አዲ ሐሩሽ በሚባሉ አካባቢዎች በሚገኝ የስደተኞች ጣብያ የሚኖሩ ስደተኞችን የመንግሥታቱ ድርጅት ሰራተኞች ጎብኝተዉ እንደነበር ድርጅቱ አስታውቋል።
ከ3 ሳምንት በፊት አካባቢዉ የአየር ድብደባ ከደረሰበት ወዲህ የድርጅቱ ሰራተኞች ስደተኞቹን መጎብኘት አልቻሉም ነበር።
ኤርትራዉያኑ ስደተኞች በቂ ምግብ፣ መድሐኒትና ንጹህ የመጠጥ ዉኃ የላቸዉም። ባለፉት 6 ሳምንታት ዉስጥ 20 ስደተኞች በመድሐኒት እጦት መሞታቸዉን ስፍራዉን የጎበኙት የUNHCR ሰራተኞች አስታዉቀዋል።
ትግራይ ዉስጥ የሚገኙ 25 ሺህ የኤርትራ ስደተኞን ወደ ሌላ ቦታ ለማዛወር ተኩስ አቁም እንዲደረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠይቋል።
በሌላ በኩል ፤ በጦርነት ለተጎዳዉ የትግራይ ሕዝብ የሚሰጠዉ የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ እየተሟጠጠ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው ሪፖርት አሳውቋል።
ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/?s=09
ምንጭ፦ UNHCR , UN OCHA , DW
@tikvahethiopia
በትግራይ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ሕይወት አደጋ እንደተጋረጠበት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አስታወቀ።
በጦርነቱ ምክንያት የስደተኞቹ ኑሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበላሸ መሆኑንም ገልጿል።
በቅርቡ ማይ ዓይኒ እና አዲ ሐሩሽ በሚባሉ አካባቢዎች በሚገኝ የስደተኞች ጣብያ የሚኖሩ ስደተኞችን የመንግሥታቱ ድርጅት ሰራተኞች ጎብኝተዉ እንደነበር ድርጅቱ አስታውቋል።
ከ3 ሳምንት በፊት አካባቢዉ የአየር ድብደባ ከደረሰበት ወዲህ የድርጅቱ ሰራተኞች ስደተኞቹን መጎብኘት አልቻሉም ነበር።
ኤርትራዉያኑ ስደተኞች በቂ ምግብ፣ መድሐኒትና ንጹህ የመጠጥ ዉኃ የላቸዉም። ባለፉት 6 ሳምንታት ዉስጥ 20 ስደተኞች በመድሐኒት እጦት መሞታቸዉን ስፍራዉን የጎበኙት የUNHCR ሰራተኞች አስታዉቀዋል።
ትግራይ ዉስጥ የሚገኙ 25 ሺህ የኤርትራ ስደተኞን ወደ ሌላ ቦታ ለማዛወር ተኩስ አቁም እንዲደረግ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠይቋል።
በሌላ በኩል ፤ በጦርነት ለተጎዳዉ የትግራይ ሕዝብ የሚሰጠዉ የአስቸኳይ ጊዜ ርዳታ እየተሟጠጠ መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ (OCHA) ባወጣው ሪፖርት አሳውቋል።
ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/?s=09
ምንጭ፦ UNHCR , UN OCHA , DW
@tikvahethiopia
#Safaricom
" ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ያደርጋል " - አንዋር ሱሳ
የኬንያው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ መዋዕለ ነዋይ እንደሚያፈስ ገልጿል።
የሳፋሪኮም የኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አንዋር ሱሳ ኩባንያው በተያዘው የፈረንጆቹ 2022 ወደ 300 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በኢትዮጵያ ፈሰስ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራውን ለመጀመር የኔትወርክ ዝርጋታ እያካሄደ መሆኑንና የመጀመሪያ የመረጃ ማዕከሉን በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ መዘርጋቱን ተናግረዋል።
ሳፋሪኮም በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎቱን በይፋ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia
" ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ ያደርጋል " - አንዋር ሱሳ
የኬንያው የቴሌኮም ኩባንያ ሳፋሪኮም በፈረንጆቹ 2022 በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ 300 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ወጪ መዋዕለ ነዋይ እንደሚያፈስ ገልጿል።
የሳፋሪኮም የኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አንዋር ሱሳ ኩባንያው በተያዘው የፈረንጆቹ 2022 ወደ 300 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በኢትዮጵያ ፈሰስ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
ኩባንያው በኢትዮጵያ ስራውን ለመጀመር የኔትወርክ ዝርጋታ እያካሄደ መሆኑንና የመጀመሪያ የመረጃ ማዕከሉን በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ መዘርጋቱን ተናግረዋል።
ሳፋሪኮም በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ አገልግሎቱን በይፋ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia
" በሃይማኖታዊ በዓላት የታደሙ ምእመናንን መግደል ሃይማኖቱ ብሎም ሀገር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ነው " - እናት ፓርቲ
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ እናት ፓርቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጥር 12 እንደ ሃይማኖታቸው የአምልኮ እና ቀኖና ሥርዓት ታቦተ ሕጉን ወደ መንበረ ክብሩ ለመመለስ በማኅደረ መለኮት ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን በታደሙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ላይ በጸጥታ ኃይሉ የተፈጸመው ግድያ ኢ ሕጋዊ፣ ኢ ሃይማኖታዊና የሞራል አልባነት ድርጊት ነው ብሎታል።
ጥንቱንም ላለፉት ዓመታት የመስቀልና የጥምቀት በዓላት በሚከበሩበት ጊዜ "ጠብ ያለሽ በዳቦ" ምክንያት እየፈለጉ ወከባ መፍጠር፣ ማሰር፣ መደብደብ ሕጋዊነት እስኪመስል ድረስ በተደጋጋሚ ሲፈጸም የቆየ ተግባር ቢሆንም በወይብላ ማርያም ያለፈውን ዓመት ጨምሮ መሰል ድርጊቶች በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የጸጥታ አካላት እየተፈጸመ ነው ሲል ከሷል።
ፓርቲው ፥ " ሃይማኖት ለእኛ ለኢትዮጵያውያን እስትንፋሳችን መሆኑ እየታወቀ በየጊዜው ጸብ እየጫሩ ፓለቲካዊ ጉዳዮቻቸውን ሃይማኖታዊ ቀርጽ እንዲኖረው ለማስያዝ እየተሔደ ያለበት ርቀት በጊዜ ካልታረመ መዘዙ ከባድ ውጤቱም የከፋ መሆኑ የማይቀር ጉዳይ ነው " ሲል አሳስቧል።
እናት ፓርቲ ፥ የኦሮምያ ክልል መንግስት ሰለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ ሕዝብንም በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤ ድርጊቱን ባነሳሱ እና በፈጸሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፣ የሕግ ውሳኔውም ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ፤ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ለሃይማኖቱ ተከታዮች የሞራል ካሳ እንዲከፈል፤ ያለአግባብ የታሰሩ ምዕመናንም በአስቸኳይ እንዲፈቱ አሳስቧል።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ እናት ፓርቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ጥር 12 እንደ ሃይማኖታቸው የአምልኮ እና ቀኖና ሥርዓት ታቦተ ሕጉን ወደ መንበረ ክብሩ ለመመለስ በማኅደረ መለኮት ወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን በታደሙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች ላይ በጸጥታ ኃይሉ የተፈጸመው ግድያ ኢ ሕጋዊ፣ ኢ ሃይማኖታዊና የሞራል አልባነት ድርጊት ነው ብሎታል።
ጥንቱንም ላለፉት ዓመታት የመስቀልና የጥምቀት በዓላት በሚከበሩበት ጊዜ "ጠብ ያለሽ በዳቦ" ምክንያት እየፈለጉ ወከባ መፍጠር፣ ማሰር፣ መደብደብ ሕጋዊነት እስኪመስል ድረስ በተደጋጋሚ ሲፈጸም የቆየ ተግባር ቢሆንም በወይብላ ማርያም ያለፈውን ዓመት ጨምሮ መሰል ድርጊቶች በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የጸጥታ አካላት እየተፈጸመ ነው ሲል ከሷል።
ፓርቲው ፥ " ሃይማኖት ለእኛ ለኢትዮጵያውያን እስትንፋሳችን መሆኑ እየታወቀ በየጊዜው ጸብ እየጫሩ ፓለቲካዊ ጉዳዮቻቸውን ሃይማኖታዊ ቀርጽ እንዲኖረው ለማስያዝ እየተሔደ ያለበት ርቀት በጊዜ ካልታረመ መዘዙ ከባድ ውጤቱም የከፋ መሆኑ የማይቀር ጉዳይ ነው " ሲል አሳስቧል።
እናት ፓርቲ ፥ የኦሮምያ ክልል መንግስት ሰለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ ሕዝብንም በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቅ፤ ድርጊቱን ባነሳሱ እና በፈጸሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ፣ የሕግ ውሳኔውም ለሕዝብ ይፋ እንዲደረግ፤ ለተጎጂ ቤተሰቦች እና ለሃይማኖቱ ተከታዮች የሞራል ካሳ እንዲከፈል፤ ያለአግባብ የታሰሩ ምዕመናንም በአስቸኳይ እንዲፈቱ አሳስቧል።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
" መንግስት አጥፊዎችን ተከታትሎ ለህግ ማቅረብ ይገባዋል " - የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ
በጥምቀት በዓል ላይ በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ወይብላ ቅድስት ማሪያም ቤተክርስቲያን ላይ የተፈጸመውን ድርጊት እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታውቋል።
ጉባኤው ሃይማኖቶች የትህትና፣ የሰላምና የአንድነት፣ የፍቅርና መከባበር መሠረቶች ናቸው ብሏል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት የሰላም መሠረት ሆና ዘልቃለች ያለው የጉባኤው መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው ግጭት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን አጥብቀን እንቃዎማለን ሲልም ገልጿል።
ጉባኤው ፤ ጥር 12/2014 ዓ.ም በቡራዩ ከተማ አስተዳደር በሕግ ማስከበር ሽፋን በቤተክርስቲያኗ ላይ የተቃጣው ድርጊት ፍጹም ሕገ ወጥ ነው ያለው መግለጫው መንግሥት አጥፊዎችን ተከታትሎ ለሕግ እንዲያቀርብም ጠይቋል።
መንግሥት የሃይማኖትን እና የዜጎችን ሰላም እና ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቀው ጉባኤው የሕይዎት፣ የአካልና የመንፈስ ስብራት በደረሰባቸው ወገኖች የተሠማንን ጥልቅ ሐዘንም በተሰበረ ልብ እንገልፃለን ብሏል።
#EPA
@tikvahethiopia
በጥምቀት በዓል ላይ በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ወይብላ ቅድስት ማሪያም ቤተክርስቲያን ላይ የተፈጸመውን ድርጊት እንደሚያወግዝ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አስታውቋል።
ጉባኤው ሃይማኖቶች የትህትና፣ የሰላምና የአንድነት፣ የፍቅርና መከባበር መሠረቶች ናቸው ብሏል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት የሰላም መሠረት ሆና ዘልቃለች ያለው የጉባኤው መግለጫ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው ግጭት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን አጥብቀን እንቃዎማለን ሲልም ገልጿል።
ጉባኤው ፤ ጥር 12/2014 ዓ.ም በቡራዩ ከተማ አስተዳደር በሕግ ማስከበር ሽፋን በቤተክርስቲያኗ ላይ የተቃጣው ድርጊት ፍጹም ሕገ ወጥ ነው ያለው መግለጫው መንግሥት አጥፊዎችን ተከታትሎ ለሕግ እንዲያቀርብም ጠይቋል።
መንግሥት የሃይማኖትን እና የዜጎችን ሰላም እና ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቀው ጉባኤው የሕይዎት፣ የአካልና የመንፈስ ስብራት በደረሰባቸው ወገኖች የተሠማንን ጥልቅ ሐዘንም በተሰበረ ልብ እንገልፃለን ብሏል።
#EPA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ኢትዮጵያ 📍
ሞሊ ፊ እና ዴቪድ ሳተርፊልድ ኢትዮጵያ ናቸው።
የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድን ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሙሳ ፋኪ መሀመት ከሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር በነበራቸው ቆይታ የሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ገልፀዋል።
ሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በተለይ ለሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት መፍትሄ ለማፈላለግ ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ 📍
ሞሊ ፊ እና ዴቪድ ሳተርፊልድ ኢትዮጵያ ናቸው።
የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር የሆኑት ሙሳ ፋኪ መሀመት በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የሆኑት ሞሊ ፊ እና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድን ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሙሳ ፋኪ መሀመት ከሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር በነበራቸው ቆይታ የሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ገልፀዋል።
ሁለቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት ወደ ኢትዮጵያ የመጡት በተለይ ለሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት መፍትሄ ለማፈላለግ ነው።
@tikvahethiopia