#Election2012
የኢዜማ የአዲስ አበባ ምርጫ ወረዳ 11 ከአባላት፣ ደጋፊዎች እና የአካባቢው ነዋሪ ጋር የሚያደርገው ውይይት በስብሰባዎች ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።
ስብሰባውን በአካባቢው በሚኖሩ የሀገር ሽማሀግሌዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን የምርጫ ወረዳው ሥራ አስፈጻሚ እስካሁን የተከናወኑ ሥራዎችን እና እቅዶቻቸውን ለተሰብሳቢው አሳውቀዋል።
የኢዜማ ሊቀመንበር የሺዋስ አሰፋ፣ ምክትል መሪው አንዱዓለም አራጌ እና የምርጫ ስትራቴጂ እና ማኔጅመንት ካውንስል አባል አማንይኹን ረዳ በስብሰባው ላይ ተገኝተው የፓርቲውን ሀገራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ።
#EZEMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢዜማ የአዲስ አበባ ምርጫ ወረዳ 11 ከአባላት፣ ደጋፊዎች እና የአካባቢው ነዋሪ ጋር የሚያደርገው ውይይት በስብሰባዎች ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።
ስብሰባውን በአካባቢው በሚኖሩ የሀገር ሽማሀግሌዎች ምርቃት የተጀመረ ሲሆን የምርጫ ወረዳው ሥራ አስፈጻሚ እስካሁን የተከናወኑ ሥራዎችን እና እቅዶቻቸውን ለተሰብሳቢው አሳውቀዋል።
የኢዜማ ሊቀመንበር የሺዋስ አሰፋ፣ ምክትል መሪው አንዱዓለም አራጌ እና የምርጫ ስትራቴጂ እና ማኔጅመንት ካውንስል አባል አማንይኹን ረዳ በስብሰባው ላይ ተገኝተው የፓርቲውን ሀገራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ።
#EZEMA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EZEMA
ብልጽግና ፓርቲ የህዝብና የመንግስት ሃብትን ለምርጫ ቅስቀሳ እየተጠቀመ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ አስታወቀ። የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወቅታዊ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ በአዲስ አበባ መግለጫ በመስጠት ላይ ናቸው።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት ብልጽግና ፓርቲ የህዝብን እና የመንግስትን ገንዘብ ለምርጫ ቅስቀሳ እያዋለ ነው ብለዋል።
በመሆኑም የብልጽግና ፓርቲ ድርጊት ሌሎች ፓርቲዎችን ወደ አላስፈላጊ መንገድ የሚመራ ከማድረጉ በተጨማሪ የአገሪቱን የዲሞክራሲ ግንባታ ስለሚጎዳ ከዚህ ድርጊቱ እንዲታቀብ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድም ይሄንን ህገወጥ እንቅስቃሴ እንዲያስቆም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጠይቀዋል።
#ኢትዮኤፍኤም107.8 #ሔኖክአስራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ብልጽግና ፓርቲ የህዝብና የመንግስት ሃብትን ለምርጫ ቅስቀሳ እየተጠቀመ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ አስታወቀ። የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወቅታዊ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ በአዲስ አበባ መግለጫ በመስጠት ላይ ናቸው።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት ብልጽግና ፓርቲ የህዝብን እና የመንግስትን ገንዘብ ለምርጫ ቅስቀሳ እያዋለ ነው ብለዋል።
በመሆኑም የብልጽግና ፓርቲ ድርጊት ሌሎች ፓርቲዎችን ወደ አላስፈላጊ መንገድ የሚመራ ከማድረጉ በተጨማሪ የአገሪቱን የዲሞክራሲ ግንባታ ስለሚጎዳ ከዚህ ድርጊቱ እንዲታቀብ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድም ይሄንን ህገወጥ እንቅስቃሴ እንዲያስቆም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጠይቀዋል።
#ኢትዮኤፍኤም107.8 #ሔኖክአስራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia