TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የመከላከያ ግብረ ሃይል ውይይት አካሂዷል!

የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ለመከላከል የተቋቋመው የመከላከያ ሰራዊት ግብረ ሃይል ያለፈው ሳምንት የስራ አፈፃፀም የተመለከተ ውይይት አካሂዷል።

በኢፌዲሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሃመድ የሚመራው ግብረ ሃይሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በመላው ሰራዊቱ የተከናወኑ ተግባራትንና ውጤታቸውን እንዲሁም ወደፊት መሰራት ስለሚገባቸው ስራዎች በጥልቀት ተወያይቷል::

በውይይቱም እስካሁን የተከናወኑት የመከላከል ተግባራት ውጤታቸው አመርቂ መሆኑና አንድም የሰራዊት አባል በቫይረሱ እንዳልተያዘና ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በውይይቱ ተገልፇል።

#FDREDefenesForce
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለቲክቫህ ሳዑዲ አረቢያ ቤተሰቦች፦

የሳዑዲ አረቢያ ፀረ-ኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ዘመቻ ሰዓት እልፍ አዋጅን የሚቃረን ፎቶ/ምስልና ተንቀሳቃሽ ምስል/ቪድዮ ክሊፕ በማህበራዊ ሚዲያ በሚለጥፍ ግለሰብ ላይ አምስት ዓመት ፅኑ እስራት እና የሶስት ሚሊዮን የሳዑዲ ሪያል ክፍያ የሚያስከፍል መቀጮ የሳዑዲ ዐቃቤ ህግ መጣሉን አስታውቋል።

ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ሪያድ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በትግራይ ክልል!

የትግራይ ክልላዊ መንግስት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል የሚያስችል ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል፡፡

በትግራይ ክልል ደረጃ የቫይረሱ ስርጭት የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ በ22 ዋና ዋና ጉዳች ላይ ከመከረ በኋላ ሶስት ዐበይት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ማሳለፉን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ ሚካኤል አስታውቀዋል፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ በሰጡት መግለጫ በትግራይ ክልል ከገጠር ወደ ከተማ ፣ ከከተማ ወደ ገጠር፣ ከከተማ ወደ ከተማ የሚደረጉ ዝውውሮች ለሚቀጥሉት 15 ቀናት ታግደዋል፡፡ ህዝብ የሚበዛባቸው ገበያዎችም እንዳይካሄዱ መታገዳቸውንም ዶ/ር ደብረጽዮን ገልፀዋል፡፡

እንደ ሠርግና ተስካር ያሉ ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ጉዳዮችም ለጊዜው እንዳይካሄዱ የክልሉ ስራ አስፈጻሚ ወስኗል፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እንዳሉት የተላሉፉት ውሳኔዎች ለሚቀጥሉት 15 ቀናት ተግባራዊ እንሚደረጉና በሽታው ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ እየተገመገመ የተለያዩ ውሳኔዎች እንደሚተላለፉ መናገራቸውን የትግራይ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል፡፡

ምንጭ፦ የትግራይ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዓለም የምግብ ፕሮግራም ለኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ኢትዮጵያ የመቆጣጠር ሂደት ላይ የሚያገለግሉ አምስት (5) ታብሌቶችን መስጠቱን የኢትዮጵየ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመከላከያ ሰራዊት ምሥራቅ ዕዝ!

የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚያስችሉ የቅድመ መከላከል ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት ምስራቅ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በኢትዮጵያ ቫይረሱ [ኮቪድ-19] እንደገባ ከተነገረበት ጊዜ አንስቶ ስርጭቱን ለመከላከልና ለመግታት በመንግስት በኩል ውሳኔዎች እየተላለፉና ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ።

በመሆኑም የቫይረሱን ስርጭት ለመከላከልና የሰራዊቱን ጤንነት ለመጠበቅ የሚያስችሉ የቅድመ መከላከል ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ዘውዱ በላይ ገልጸዋል።

የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት በጋራ የሚኖሩ፣ በጋራ የሚበሉ እና የሚንቀሳቀሱ በመሆኑ የቅድመ መከላከል ስራው ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እነደሆነም ተናግረዋል።

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

የኮሮና ቫይረስን ወረርሽኝ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ የሚሌኒየም አዳራሽን የጤና አገልግሎት መስጫ አድርጎ ለመጠቀም ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ገልጸዋል፡፡

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የተለያዩ የቅድመ ጥንቃቄ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሚገኙ ሚኒስትሯ ጠቅሰዋል፡፡

ዶክተር ሊያ እንዳስታወቁት በሽታው የከፋ ጉዳት ሳያደርስ ግለሰቦች እና ተቋማት የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢቲቪ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዶክተር ሊያ ታደሰ፦

"የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ባዘጋጀው የኢትዮጵያ የተቀናጀ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) መከታተያና መቆጣጠሪያ መረብ ሲስተም ላይ በትናንትናው እለት በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 20 ተብሎ የተጠቀሰው በስህተት መሆኑን እያሳወቅን በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 12 መሆኑን እናረገግጣለን።"

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EthioTelecom

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ በምዕራብ ኦሮሚያ ስለተቋረጠው የስልክ እና የኢንተርኔት አገልግሎት በድጋሚ ይቅርታ ጠይቀዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በሸገር ኤፍ 102.1 የሬድዮ ጣቢያ ሲናገሩ እንደተደመጡት የአግልግሎት መቋረጡ መንግስት በአካባቢው ፀጥታና ደህንነት ለማስፈን እየወዳሰደ ካለው እርምጃ ጋር በተያያዘ መሆኑን ዳግም አስታውሰዋል።

የኢተርኔት እና የስልክ አገልግሎቱ መቼ ነው የሚጀምረው ተብለው በሬድዮ ጣቢያው የተጠየቁት ወ/ሪት ፍሬህይወት ተከታዩን ምላሽ ሰጥተዋል፦

"ይሄ ወረርሽኝ ከተከሰተ በኃላ ዝም ብለን አላለፍንም ፤ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በተለይም ከኦሮሚያ ክልል መንግሥት ጋር ውይይት አድርገናል እዛ አካባቢ ያለው ማህበረሰብ በቂ መረጃ ስለወረርሽኙ እንዲያገኝ አስፈላጊው ጥረት እንዲደረግ፤ በእኛም በኩል መውሰድ ያለብንን ነገር ካለ ውይይት አድርገናል። ስለዚህ ከሚመለከታቸው የደህንነት አካላት በአካባቢው ያለውን የፀጥታና ደህንነት ችግር ከተፈታ ወይም መከፈት ካለበት የቴሌኮም አገልግሎቱ ፤ አቅጣጫ ሲሰጠን እኛም እርምጃ የምንወስድ ይሆናል። አሁን ያለው በዚህ ሁኔታ ላይ ነው። ይህን ነው ልል የምችለው።"

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ስርጭትን ለመግታት በመላው ሩዋንዳ እንቅስቃሴ ማድረግ የተከለከለ እንደሆነ ይታወቃል ፤ ይህን 'ከቤታችሁ አትውጡ' ትዕዛዝ ተላልፈው የተገኙ እና በፖሊሶች ላይ ጥቃት የፈፀሙ ሁለት ወጣቶችን የሩዋንዳ ፖሊስ በጥይት መትቶ መግደሉን ብሉምበርግ አፍሪካ አስነብቧል።

#BloombergAfrica
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ግመሌንም አስራለው፣ በአላህም እመካለው!

በስፔን ሀገር የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝ በተከሰተ የመጀመሪያው ሳምንት 8 ሰው ብቻ ነበር ሪፖርት የተደረገው። በሶስት (3) ሳምንታት ግን ከ21,000 ሰው በላይ በበሽታው ተጠቂ መሆኑ ተዘግቧል። ቀልዱን እንተው! ተሰብስቦ መጫወቱ ለጊዜውም ቢሆን ይቅርብን። ካልተጠነቀቅን እዚህ ቁጥር ላይ ማንደርስበት ምንም አይነት ማስተማመኛ የለንም። ግመሌንም አስራለሁ ፤ በአላህም እመካለሁ!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሱማሊያ ጤና ሚኒስቴር ሁለተኛውን የኮሮና ቫይረስ ኬዝ ዛሬ ሪፖርት አደረጓል። ሚኒስቴሩ የቫይረሱ ተጠቂ የሱማሊያ ዜጋ መሆኑን ከመግለፅ ውጭ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአልመዳ የጨርቃጨርቅና አልባሳት ፋብሪካ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የሚረዳ በቀን በአማካይ 50 ሺህ የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል እያመረተ መሆኑን አስታወቀ። ፋብሪካው ከኢትዮጵያ የምግብ የመድሀኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደር ፍቃድና እውቅና ማግኘቱን ገልጿል።

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኮሮና ቫይረስ ለተራራ ጎሪላዎች ሕይወት አስጊ ሆኗል!

የኮሮና ቫይረስ አስጊነት ተከትሎ የኮንጎ ዲሞክራሲያዊት ሪፐብሊክ ቨሩንጋ ብሔራዊ ፓርኳን እስከ ወርኃ ጁን ለቱሪስት ዘግታለች።

ሩዋንዳም በተመሳሳይ ሶስት ብሄራዊ ፓርኮችን ለቱሪስቶች እንዲሁም ለጥናት ስራዎች ዘግታለች። ኡጋንዳ ግን እንደ ሩዋንዳ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ተመሳሳይ እርምጃ አልወሰደችም።

በኡጋንዳ ፣ ሩዋንዳና ኮንጎ ጥበቃ በሚደረግላቸው ሥፍራዎች የሚገኙት የተራራ ጎሪላዎቹ ቁጥር ከ1,000 ያልበለጠ ነው።

#AP #SBS
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ይህ ፎቶ ሚሊኒየም አዳራሽ ነው ?

በእርግጥ የጤና ሚኒስቴር 'ሚሊኒየም አዳራሽን' የጤና አገልግሎት መስጫ አድርጎ ለመጠቀም ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል። ነገር ግን ከላይ የምትመለከቱት ፎቶ ከስፔን የተወሰደ እንጂ አሁን በሚሊኒየም አዳራሽ ያለውን ገፅታ የሚያስይ አይደለም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በወሰነው መሰረት ዛሬ መጋቢት 17/2012 ዓ/ም በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት እና ጤና ሚኒስቴር በመገኘት ለህዳሴ ግድቡ ግንባታና ለኮሮና ቫይረስ መከላከያ የሚውል የብር 2,000,000.00 (ሁለት ሚሊዮን ብር) ድጋፍ አድርጓል፡፡ ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉም በበኩሏ የብር 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ ብር) ድጋፍ አድርጋለች More @tikvahethsport

@tikvahethsport @tikvahethiopia
#COVID19

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኮቪድ-19 ላይ ጥናት ለማካሄድ 10 ሚሊየን ብር መደበ፡፡ በዛሬው እለት በኮቪድ-19 ላይ ጥናት የሚያኪያሂድ የጥናት ቡድን የተቋቋመ ሲሆን ቡድኑ ጥናቱን ለመጀመር ይችል ዘንድ ከተመደበው አጠቃላይ ፈንድ ውስጥ አንድ ሚሊየን ብር ወጪ ሆኖ ተሰጥቶታል፡፡

#AAU
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአሜሪካ ኤምባሲ ላልተወሰነ ጊዜ ተዘጋ!

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በኮሮናቫይረስ ስርጭት ምክንያት ላልተወሰ ጊዜ ዝግ መደረጉን ቢቢሲ ዘግቧል።

ኤምባሲው ዛሬ ባወጣው መግለጫ ከቫይረሱ ስርጭት እና የኢትዮጵያ መንግሥት ስርጩቱን ለመግታት ከሚያደርገው ጥረት አንጻር ኤምባሲውን በጊዜያዊነት መዝጋት አስፈልጓል ብሏል።

ኤምባሲው ለዜጎቹ ጭምር ያደረግ የነበረውን የፓስፖርት እድሳት፣ ከአገር ውጪ የወሊድ እና የሞት ምዝገባን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶችን እንደማይሰጥ አስታውቋል።

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
# UPDATE

በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ ሺህ ስምንት መቶ ስምንት መድረሱን የዓለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ይፋ አድርጓል፡፡

ባለፉት ሃያ አራት ሰዓታት በ15 ሀገራት ውስጥ ሁለት መቶ አስራ ስድስት አዲስ ታማሚዎች መመዝገባቸው ተገልጿል፡፡

ኮሮና ቫይረስ ጊኒ ቢሳዎ እና ማሊ ለመጀመሪያ ጊዜ መግባቱ እና እያንዳንዳቸው አንድ ታማሚ ማግኘታቸውም ተገልጿል፡፡

#WHO #AfricaCDC #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia