#TPLF #PMOEthiopia #EPRDF
የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ መግለጫና በፌደራል መንግስቱ የተሰጠው ምላሽ የቀጠሉ ልዩነቶች የተደፋፈኑ እውነታዎች ዳግም አደባባይ የወጡበት ነው። ህወሓት ባወጣው መግለጫ የፌደራል መንግስቱን በከፍተኛ ሁኔታ ተችቷል። ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግሮች እየተበራከቱ፤ ጥፋት በጥፋት ላይ እየተደራረበ መጥቷል ይላል መግለጫው። የጥፋቱ መጠንና ስፋት በየቀኑ እየጨመረ ወደከፍተኛ ሀገር የመበተን ደረጃ እየደረሰ ነው ብሏል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የፕሬስ ክፍል ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በመግለጫው ላይ የተንፀባረቁ ሃሳቦችን አጣጥለዋል። ከለውጡ በፊት በነበሩ አመታት ኢትዮጵያ በመፍረስ አፋፍ ላይ እንደነበረች አቶ ንጉሱ አስታውሰዋል። አሁን ያለው የኢትዮጵያ አመራር የተረከበውም ችግር ነው በማለት የነበሩትን ሁኔታዎች አብራርተዋል።
በዚህ የለውጥ ሂደት ከፍተኛ ስኬቶች መመዝገባቸውን፤ ችግሮችም መኖራቸውን አስታውሰዋል። ከነዚህ ችግሮች አንዳንዶቹ ደግሞ ካለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የቀጠሉ በሽታዎች መሆናቸውን ነው የገለፁት። ያለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ውጤቶች የሆኑት የጥላቻ፣ የቂም በቀል፣ የቁርሾ፣ የመለያየት፣ የመከፋፈልና የሴራ ጠባሳዎች በቀላሉ የሚለቁ አይደሉም በማለት ነው አቶ ንጉሱ ያብራሩት። እናም ለውጡ በአንድ በኩል እነዚህን የማስተካከል በሌላ በኩል ደግሞ ህብረተሰቡ የሚጠይቃቸው የመልካም አስተዳደር የዲሞክራሲና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች የመመለስ ስራ መሸከሙን አንስተዋል። የህውሓት መግለጫ ግን ከዚህ የለውጥ ሂደት በተፃራሪ የቆሙ ወገኖችን አቋምን ያንፀባረቀ ነው ብለዋል።
Via VOA/ጋዜጠኛ እስክንድር ፍሬው/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ መግለጫና በፌደራል መንግስቱ የተሰጠው ምላሽ የቀጠሉ ልዩነቶች የተደፋፈኑ እውነታዎች ዳግም አደባባይ የወጡበት ነው። ህወሓት ባወጣው መግለጫ የፌደራል መንግስቱን በከፍተኛ ሁኔታ ተችቷል። ከጊዜ ወደ ጊዜ ችግሮች እየተበራከቱ፤ ጥፋት በጥፋት ላይ እየተደራረበ መጥቷል ይላል መግለጫው። የጥፋቱ መጠንና ስፋት በየቀኑ እየጨመረ ወደከፍተኛ ሀገር የመበተን ደረጃ እየደረሰ ነው ብሏል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የፕሬስ ክፍል ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በመግለጫው ላይ የተንፀባረቁ ሃሳቦችን አጣጥለዋል። ከለውጡ በፊት በነበሩ አመታት ኢትዮጵያ በመፍረስ አፋፍ ላይ እንደነበረች አቶ ንጉሱ አስታውሰዋል። አሁን ያለው የኢትዮጵያ አመራር የተረከበውም ችግር ነው በማለት የነበሩትን ሁኔታዎች አብራርተዋል።
በዚህ የለውጥ ሂደት ከፍተኛ ስኬቶች መመዝገባቸውን፤ ችግሮችም መኖራቸውን አስታውሰዋል። ከነዚህ ችግሮች አንዳንዶቹ ደግሞ ካለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የቀጠሉ በሽታዎች መሆናቸውን ነው የገለፁት። ያለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ውጤቶች የሆኑት የጥላቻ፣ የቂም በቀል፣ የቁርሾ፣ የመለያየት፣ የመከፋፈልና የሴራ ጠባሳዎች በቀላሉ የሚለቁ አይደሉም በማለት ነው አቶ ንጉሱ ያብራሩት። እናም ለውጡ በአንድ በኩል እነዚህን የማስተካከል በሌላ በኩል ደግሞ ህብረተሰቡ የሚጠይቃቸው የመልካም አስተዳደር የዲሞክራሲና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች የመመለስ ስራ መሸከሙን አንስተዋል። የህውሓት መግለጫ ግን ከዚህ የለውጥ ሂደት በተፃራሪ የቆሙ ወገኖችን አቋምን ያንፀባረቀ ነው ብለዋል።
Via VOA/ጋዜጠኛ እስክንድር ፍሬው/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአፋር ክልል ሰመራና ሎጊያ ከተሞች በአሁን ሰዓት ሰላማዊ ሰልፍ እየተደረገ ይገኛል። የክልሉ ነዋሪዎች በንፁሃን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት አውግዘዋል። በመከላከያ ሰራዊት ከቀናት በፊት የተሰጠው ምላሽም ተገቢ እንዳልሆነ እየገለፁ ይገኛል።
PHOTO: Abu Jaefar Dalol & Twsfaye/ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰመራና ሎጊያ ቤተሰቦች/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
PHOTO: Abu Jaefar Dalol & Twsfaye/ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰመራና ሎጊያ ቤተሰቦች/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#SEMERA
"Yes For Peace No for Terrorism!"
PHOTO: Abu Jaefar Dalol/TIKVAH FAMILY/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"Yes For Peace No for Terrorism!"
PHOTO: Abu Jaefar Dalol/TIKVAH FAMILY/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በ5 ወራት 30 ትራንስፎርመሮች ተሰርቀዋል!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅት በ2011 ዓ.ም 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ይፋ ቢያደርግም ከግንቦት ወር ወዲህ ከ30 በላይ ትራንስፎርመሮች ተሰርቀዋል። ድርጅቱ ከመጪው ታህሳስ ወር ጀምሮ የታሪፍ ማሻሻያ እንደሚያደርግ የአገልግሎቱ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አስታውቀዋል። ዳይሬክተሩ አቶ መላኩ ታዬ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2011 አፈጻጸምና በ2012 ዕቅድ ዙሪያ መግለጫ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከውዝፍ ሂሳብ እና ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ 21 ነጥብ 868 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 10 ነጥብ 123 ቢሊየን ብር ሰብስቧል።
Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ድርጅት በ2011 ዓ.ም 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ይፋ ቢያደርግም ከግንቦት ወር ወዲህ ከ30 በላይ ትራንስፎርመሮች ተሰርቀዋል። ድርጅቱ ከመጪው ታህሳስ ወር ጀምሮ የታሪፍ ማሻሻያ እንደሚያደርግ የአገልግሎቱ ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አስታውቀዋል። ዳይሬክተሩ አቶ መላኩ ታዬ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2011 አፈጻጸምና በ2012 ዕቅድ ዙሪያ መግለጫ በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከውዝፍ ሂሳብ እና ከማያገለግሉ ንብረቶች ሽያጭ 21 ነጥብ 868 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 10 ነጥብ 123 ቢሊየን ብር ሰብስቧል።
Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba
በአዲስ አበባ ከሚገኙ ወረዳዎች ግማሽ ያህሉ የዲጂታል መታወቂያ እየሰጡ መሆናቸውን የከተማው ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ በኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየው ለኢቲቪ እንደተናገሩት በከተማዋ ካሉ 121 ወረዳዎች 62ቱ የዲጂታል መታወቂያ እየሰጡ ናቸው፡፡ አገልግሎቱ የሚሰጠው በቴሌኮም ኔትወርክ እገዛ እንደመሆኑ የዚህ መሰረተ ልማት ጥራትና ተደራሽነት ጉድለት የዲጂታል መታወቂያው በሁሉም የከተማዋ አስተዳደር እንዳይሰጥ እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል አቶ ዮናስ፡፡ ከዚህ ባሻገር የሰው ሀይል እጥረት፣ ስራውን ማስፈጸሚያ በቂ ቢሮ ያለመኖር እና ለሰራተኞች የሚከፈል ደሞዝ አናሳ መሆኑ አገልግሎቱን በመዲናዋ ሙሉ ለሙሉ ለመተግበር ችግር መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ጥረት የሚደረግ ሲሆን የኢንተርኔት ተደራሽነትና ጥራት መጓደል ለማከስተካከልም የሚመለከተው አካል ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግ ሀላፊው ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢቲቪ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከሚገኙ ወረዳዎች ግማሽ ያህሉ የዲጂታል መታወቂያ እየሰጡ መሆናቸውን የከተማው ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ በኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየው ለኢቲቪ እንደተናገሩት በከተማዋ ካሉ 121 ወረዳዎች 62ቱ የዲጂታል መታወቂያ እየሰጡ ናቸው፡፡ አገልግሎቱ የሚሰጠው በቴሌኮም ኔትወርክ እገዛ እንደመሆኑ የዚህ መሰረተ ልማት ጥራትና ተደራሽነት ጉድለት የዲጂታል መታወቂያው በሁሉም የከተማዋ አስተዳደር እንዳይሰጥ እንቅፋት ፈጥሯል ብለዋል አቶ ዮናስ፡፡ ከዚህ ባሻገር የሰው ሀይል እጥረት፣ ስራውን ማስፈጸሚያ በቂ ቢሮ ያለመኖር እና ለሰራተኞች የሚከፈል ደሞዝ አናሳ መሆኑ አገልግሎቱን በመዲናዋ ሙሉ ለሙሉ ለመተግበር ችግር መፍጠሩን ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይ እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ጥረት የሚደረግ ሲሆን የኢንተርኔት ተደራሽነትና ጥራት መጓደል ለማከስተካከልም የሚመለከተው አካል ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርግ ሀላፊው ጠይቀዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢቲቪ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
DV-2021-Instructions-English (1).pdf
DV Lottery Program: DV 2021 ላይ በዚህ አመት የፖሊስ ለውጥ መደረጉ ይታወቃል፤ ይህም የ2021 ዲቪ ለማመልከት ጊዜው ያላለፈበት ፓስፖርት ሊኖረን ይገባል። ነገር ግን በተለያዩ ቦታዎች "DV ያለፓስፖርት እንሞላለን" የሚሉ አካላት ከሰዎችን ገንዘብ በመቀበል DV እየሞሉ እንደሆነ መልዕክቶች በተደጋጋሚ ይመጡልናል። ቤተሰቦቻችን እንደነገሩን ከሆነ DV እንሞላለን የሚሉት አካላት የፓስፖርት ቁጥር እያቀያየሩ እያስገቡ እየሞሉ ይገኛሉ።
🔖አሜሪካ ኤምባሲ የምትሰሩ TIKVAH ቤተሰብ አባላት በጉዳዩ ላይ የምትሰጡት መረጃ ካለ በ @tsegabwolde ወይም @tsegabtikvah መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ።
🔖አሜሪካ ኤምባሲ የምትሰሩ TIKVAH ቤተሰብ አባላት በጉዳዩ ላይ የምትሰጡት መረጃ ካለ በ @tsegabwolde ወይም @tsegabtikvah መልዕክት ማስቀመጥ ትችላላችሁ።
#ethiotelecom
ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት ዓመት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ የመስሪያ ቤቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ስራ አፈፃጸም በተመለከተ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።
ወይዘሪት ፍሬ ህይወት በመግለጫቸው ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት ላይ የተለያዩ የአሰራር ማሻሻያዎች ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ተቋሙ በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያው ሩብ ዓመት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቀዋል።
በዚህም የእቅዱን 98 በመቶ ማሳካት መቻሉን የገለጹት ወይዘሪት ፍሬህይወት፥ ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 56 በመቶው ከድምጽ አገልግሎት 29 በመቶው ደግሞ ከሞባይል ዳታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል። እንዲሁም ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 41 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላሩ ከአለም አቀፋ አገልግሎቶች የተገኘ መሆኑን ነው ተናገሩት።
የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ተመሳሳይ ሩብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 21 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በሩብ ዓመቱ የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 44 ነጥብ 4 ሚሊየን የደረሰ ሲሆን ፥ የደንበኞች ቁጥርም 10 በመቶ መጨመሩ ተመላክቷል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት ዓመት በመጀመሪያው ሩብ ዓመት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል። የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሪት ፍሬህይወት ታምሩ የመስሪያ ቤቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ስራ አፈፃጸም በተመለከተ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።
ወይዘሪት ፍሬ ህይወት በመግለጫቸው ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያ ሩብ ዓመት ላይ የተለያዩ የአሰራር ማሻሻያዎች ሲያደርግ መቆየቱን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም ተቋሙ በተያዘው በጀት ዓመት መጀመሪያው ሩብ ዓመት 10 ነጥብ 1 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አስታውቀዋል።
በዚህም የእቅዱን 98 በመቶ ማሳካት መቻሉን የገለጹት ወይዘሪት ፍሬህይወት፥ ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 56 በመቶው ከድምጽ አገልግሎት 29 በመቶው ደግሞ ከሞባይል ዳታ የተገኘ መሆኑን አንስተዋል። እንዲሁም ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ 41 ነጥብ 1 ሚሊየን ዶላሩ ከአለም አቀፋ አገልግሎቶች የተገኘ መሆኑን ነው ተናገሩት።
የተሰበሰበው ገቢ ከባለፈው ተመሳሳይ ሩብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 21 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱንም ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ተናግረዋል። በሌላ በኩል በሩብ ዓመቱ የኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር 44 ነጥብ 4 ሚሊየን የደረሰ ሲሆን ፥ የደንበኞች ቁጥርም 10 በመቶ መጨመሩ ተመላክቷል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
9ኛው የለዛ ሽልማት ዛሬ ከምሽቱ 12 ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይካሄዳል። #LezaAward #ለዛ_ሽልማት #ETHIOPIA
Via Honey
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via Honey
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
በአገሪቱ እ.አ.አ በ2017 የተዋወቀውን የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ አገልግሎት ተከትሎ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ መንገድ በሯን ለውጭ ጎብኚዎች ክፍት አድርጋለች። አገልግሎቱ ይፋ ከተደረገበት እለት አንስቶ ጎብኚዎች ከየትኛውም የአለም ክፍል ሆነው በአገልግሎቱ በመጠቀም በቀላሉ ወደ አገሪቱ መግባት ችለዋል። ይህን ተከትሎ ከ217 አገሮች በአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑ 200 ሺህ ጎብኚዎች አገሪቱን ረግጠዋል።
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአገሪቱ እ.አ.አ በ2017 የተዋወቀውን የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ አገልግሎት ተከትሎ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ መንገድ በሯን ለውጭ ጎብኚዎች ክፍት አድርጋለች። አገልግሎቱ ይፋ ከተደረገበት እለት አንስቶ ጎብኚዎች ከየትኛውም የአለም ክፍል ሆነው በአገልግሎቱ በመጠቀም በቀላሉ ወደ አገሪቱ መግባት ችለዋል። ይህን ተከትሎ ከ217 አገሮች በአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑ 200 ሺህ ጎብኚዎች አገሪቱን ረግጠዋል።
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Worabe
"በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ የጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ የአለም የኖቤል የሰላም ሽልማት የድጋፍ ሰልፍ ህዝቡ በነቂስ ወደ ወራቤ በመትመም በደመቀ ሁኔታ እየተካሄደ ነው። በድጋፍ ሰልፉም በዞንና በወራቤ በከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ኃላፊዎች መልዕክቶች እየተላለፉ ይገኛሉ።" Abdure/የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ የጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር አብይ አህመድ የአለም የኖቤል የሰላም ሽልማት የድጋፍ ሰልፍ ህዝቡ በነቂስ ወደ ወራቤ በመትመም በደመቀ ሁኔታ እየተካሄደ ነው። በድጋፍ ሰልፉም በዞንና በወራቤ በከተማ አስተዳደር የመንግስት የስራ ኃላፊዎች መልዕክቶች እየተላለፉ ይገኛሉ።" Abdure/የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BUHONA
በጭልጋ ቁጥር 1 ወረዳ በተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ተፈጸመ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት እንደሆነ ተገለጸ!
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ቁጥር 1 ወረዳ ‹ቡሆና› በተባለው አካባቢ በተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል የሚል መረጃ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተሠራጨ ነው፡፡ አብመድ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገው ጥረት ግን ‹‹ከመተማ ወደ ጎንደር ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ ቡሆና አካባቢ በከባድ መሳሪያ ተመትቷል›› በሚል የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን ከአካባቢው ባገኘው መረጃ አረጋግጧል፡፡
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደርና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳኘው በለጠ ባለሙያዎችን ቦታው ድረስ በመላክ አረጋግጠናል በማለት ለአብመድ እንደገለጹት በአካባቢው መስከረም 18 ቀን 2012 ዓ.ም ከተከሰተው ጥቃት ውጭ የተፈጸመ ሕገ ወጥ ድርጊት (ጥቃት) የለም፡፡
‹‹በአካባቢው አሁን አንጻራዊ ሠላም አለ፤ ጥምር የፀጥታ ኃይሉም ተቀናጅቶ እየተንቀሳቀሰ ነው፤ የትናንቱ መግለጫ ደግሞ በኅብረተሰቡ ዘንድ መረጋጋት እንዲፈጠር አድርጓል›› ብለዋል አቶ ዳኘው፡፡ ትናንት ምሽት በተሰጠው መግለጫ ልክ የፀጥታ ኃይሉ አካባቢውን አስተማማኝ ሠላም የሠፈነበት ለማድረግ እንዲሰራ ነዋሪዎች እያሳሰቡ መሆኑንም ነው አቶ ዳኘው ያመለከቱት፡፡
ኅብረተሰቡ ዛሬ የተፈጸመ ጥቃት አለመኖሩን አውቆ የተረጋጋ መደበኛ ሕይወቱን እንዲመራ ያሳሰቡት መምሪያ ኃላፊው በማኅበራዊ ሚዲያ ኃላፊነት በጎደለው መንገድ የቆዬ መረጃ እየለቀቁ ሕዝቡን ማደናገር እንደማይገባም አስገንዝበዋል፡፡
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በጭልጋ ቁጥር 1 ወረዳ በተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ተፈጸመ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት እንደሆነ ተገለጸ!
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ቁጥር 1 ወረዳ ‹ቡሆና› በተባለው አካባቢ በተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል የሚል መረጃ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተሠራጨ ነው፡፡ አብመድ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገው ጥረት ግን ‹‹ከመተማ ወደ ጎንደር ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ ቡሆና አካባቢ በከባድ መሳሪያ ተመትቷል›› በሚል የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን ከአካባቢው ባገኘው መረጃ አረጋግጧል፡፡
የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደርና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ዳኘው በለጠ ባለሙያዎችን ቦታው ድረስ በመላክ አረጋግጠናል በማለት ለአብመድ እንደገለጹት በአካባቢው መስከረም 18 ቀን 2012 ዓ.ም ከተከሰተው ጥቃት ውጭ የተፈጸመ ሕገ ወጥ ድርጊት (ጥቃት) የለም፡፡
‹‹በአካባቢው አሁን አንጻራዊ ሠላም አለ፤ ጥምር የፀጥታ ኃይሉም ተቀናጅቶ እየተንቀሳቀሰ ነው፤ የትናንቱ መግለጫ ደግሞ በኅብረተሰቡ ዘንድ መረጋጋት እንዲፈጠር አድርጓል›› ብለዋል አቶ ዳኘው፡፡ ትናንት ምሽት በተሰጠው መግለጫ ልክ የፀጥታ ኃይሉ አካባቢውን አስተማማኝ ሠላም የሠፈነበት ለማድረግ እንዲሰራ ነዋሪዎች እያሳሰቡ መሆኑንም ነው አቶ ዳኘው ያመለከቱት፡፡
ኅብረተሰቡ ዛሬ የተፈጸመ ጥቃት አለመኖሩን አውቆ የተረጋጋ መደበኛ ሕይወቱን እንዲመራ ያሳሰቡት መምሪያ ኃላፊው በማኅበራዊ ሚዲያ ኃላፊነት በጎደለው መንገድ የቆዬ መረጃ እየለቀቁ ሕዝቡን ማደናገር እንደማይገባም አስገንዝበዋል፡፡
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ወቅታዊው የሀገራች ሁኔታ ለፖሊስም ፈተና ሆኖበታል🤔
Ethiopian Federal Police Commission
መደበኛ ባልሆነ መንገድ፣ በተለያዩ አካባቢዎች በራሳቸው የፖሊስን ስራ በመከወን የሚንቀሳቀሱ ወጣቶችን ከዚህ በኋላ እንደማይታገስ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ምንጭ፦ ሸገር FM 102.1 /ትዕግስት ዘሪሁን/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Ethiopian Federal Police Commission
መደበኛ ባልሆነ መንገድ፣ በተለያዩ አካባቢዎች በራሳቸው የፖሊስን ስራ በመከወን የሚንቀሳቀሱ ወጣቶችን ከዚህ በኋላ እንደማይታገስ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ምንጭ፦ ሸገር FM 102.1 /ትዕግስት ዘሪሁን/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሶስትዮሽ ውይይት ውጪ ሌሎች ምክረ ሀሳቦችን እንደማትቀበል የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዛሬ ገልፀዋል።
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዛሬው ዕለት ለካቢኔ አባላት እና ለባለድርሻ አካላት የግድቡን አሁናዊ ገፅታ እና በግብፅ ወቅታዊ አቋም ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸውም የግድቡን አሁናዊሁኔታ እና የወደፊት እቅዶች ላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፥ በዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በትኩረትና በተገቢው ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል እየተደረገ ባለው ውይይት ዙሪያም ሚኒስትሩ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፥ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የቀጣናውን እና የተፋሰሱን ሀገራት ግንኙነት የሚያጠናከር መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሆኖም ግን ግብጽ ከሶስትዮሹ ውይይት ውጪ በሱዳን ካርቱም በተደረገው ውይይት ላይ ያቀረበችው ምክረ ሃሳብ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጥስ መሆኑ መሆኑን አስታውቀዋል። ግብጽ ባቀረበችው ምክረ ሀሳብ ላይም በየዓመቱ 40 ቢሊየን ሜትር ኪዮብ ውሃ ይለቀቅልኝ ማለቷ እና የአስዋን ግድብ ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ 165 ሜትር ሲደርስ ኢትዮጵያ ውሃ መልቀቅ አለባት፤ እንዲሁም ሶስተኛ ወገን በአደራዳሪነት ይግባ የሚል አቋም ማቅረቧን አንስተዋል።
ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት፥ #ግብፅ ያቀረበችው መክረ ሃሳብ ኢትዮጵያ በውሃው ላይ ያላትን መብት የሚጥስ እና ብሄራዊ ጥቅሟን የሚጎዳ በመሆኑ ኢትዮጵያ መቼም ቢሆን የምትቀበለው አይሆንም ብለዋል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሶስትዮሽ ውይይት ውጪ ሌሎች ምክረ ሀሳቦችን እንደማትቀበል የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዛሬ ገልፀዋል።
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዛሬው ዕለት ለካቢኔ አባላት እና ለባለድርሻ አካላት የግድቡን አሁናዊ ገፅታ እና በግብፅ ወቅታዊ አቋም ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸውም የግድቡን አሁናዊሁኔታ እና የወደፊት እቅዶች ላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፥ በዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በትኩረትና በተገቢው ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል እየተደረገ ባለው ውይይት ዙሪያም ሚኒስትሩ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፥ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የቀጣናውን እና የተፋሰሱን ሀገራት ግንኙነት የሚያጠናከር መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሆኖም ግን ግብጽ ከሶስትዮሹ ውይይት ውጪ በሱዳን ካርቱም በተደረገው ውይይት ላይ ያቀረበችው ምክረ ሃሳብ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጥስ መሆኑ መሆኑን አስታውቀዋል። ግብጽ ባቀረበችው ምክረ ሀሳብ ላይም በየዓመቱ 40 ቢሊየን ሜትር ኪዮብ ውሃ ይለቀቅልኝ ማለቷ እና የአስዋን ግድብ ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ 165 ሜትር ሲደርስ ኢትዮጵያ ውሃ መልቀቅ አለባት፤ እንዲሁም ሶስተኛ ወገን በአደራዳሪነት ይግባ የሚል አቋም ማቅረቧን አንስተዋል።
ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት፥ #ግብፅ ያቀረበችው መክረ ሃሳብ ኢትዮጵያ በውሃው ላይ ያላትን መብት የሚጥስ እና ብሄራዊ ጥቅሟን የሚጎዳ በመሆኑ ኢትዮጵያ መቼም ቢሆን የምትቀበለው አይሆንም ብለዋል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ethio telecom | ኢትዮ ቴሌኮም የ2012 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅዱን 98% በማሳካት 10.1 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ማግኘቱን ግለጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#GONDAR
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡለትን ተማሪዎች ዛሬ ጥቅምት 06/ 2012 ዓ.ም እየተቀበለ ይገኛል፡፡ አቀባበሉ ነገም የሚቀጥል ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ለልጆቼ ምቾትና ደህንነት ሲባል በተደራጀ መልኩ አቀባበሉን እያከናወንኩ እገኛለሁ ብሏል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ዳይሬክሬክተሮች፣ ዲኖች፣ ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የተማሪ ህብረት የከተማ አስተዳደሩና ነዋሪዎች እንዲሁም የፓሊስና ፀጥታ አካላት በተናበበ ሁኔታ በእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ተማሪዎችን በማስተናገድ ላይ እንደሆኑም በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው "እናንተን ማገልገል መታደል ነውና "ሃገራችን ለማገልገል ቆርጠን ተነስተናል!" ዓመቱ እውቀት ዘርተን ጥበብ የምናጭድበት፣ መልካም አመለካከት አብቅለን የምናሳድግበት ይሁን! ሲልም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
GONDAR UNIVERSITY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡለትን ተማሪዎች ዛሬ ጥቅምት 06/ 2012 ዓ.ም እየተቀበለ ይገኛል፡፡ አቀባበሉ ነገም የሚቀጥል ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ለልጆቼ ምቾትና ደህንነት ሲባል በተደራጀ መልኩ አቀባበሉን እያከናወንኩ እገኛለሁ ብሏል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ዳይሬክሬክተሮች፣ ዲኖች፣ ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የተማሪ ህብረት የከተማ አስተዳደሩና ነዋሪዎች እንዲሁም የፓሊስና ፀጥታ አካላት በተናበበ ሁኔታ በእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ተማሪዎችን በማስተናገድ ላይ እንደሆኑም በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው "እናንተን ማገልገል መታደል ነውና "ሃገራችን ለማገልገል ቆርጠን ተነስተናል!" ዓመቱ እውቀት ዘርተን ጥበብ የምናጭድበት፣ መልካም አመለካከት አብቅለን የምናሳድግበት ይሁን! ሲልም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
GONDAR UNIVERSITY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የዓለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የእውቅና መድረክ የፊታችን እሁድ በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል፡፡
በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች፣ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ የሚከናወነው ይህ የደስታ መግለጫ ዝግጅት እሁድ ጥቅምት 9፣2012 ዓ.ም ከቀኑ 11 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት እንደሚዘልቅ የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ አስታውቋል።
Via #WaltaTV
@tsehabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የዓለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የእውቅና መድረክ የፊታችን እሁድ በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል፡፡
በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች፣ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ የሚከናወነው ይህ የደስታ መግለጫ ዝግጅት እሁድ ጥቅምት 9፣2012 ዓ.ም ከቀኑ 11 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት እንደሚዘልቅ የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ አስታውቋል።
Via #WaltaTV
@tsehabwolde @tikvahethiopia