የእሳት አደጋ‼️
በኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ መግቢያ ላይ የሚገኘው #ኢንተማ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሻማ ፋብሪካ ላይ በደረሰበት የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገለፀ።
በዚህ የእሳት አደጋ ከፋብሪካው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት የንግድ ሱቆችና አንድ መኖሪያ ህንፃ ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ በአጠቃላይ 11 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ተናግረዋል።
ከንግድ ሱቆች 500 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን ከመኖሪያ ህንፃውና ከሱቆቹ 7 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማትረፍ መቻሉንም ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠርም ከአመስት ቅርንጫፎቹ የተውጣቱ 80 የአደጋ ተቆጣጣሪ ባለሙያዎች፣217 ሺህ 500 ሊትር ውሃ፣ 5 ሺህ 975 ኬሚካል ፎም እና 13 ከባድ ተሸከርካሪዎችን መጠቀሙን አንስተዋል።
አደጋውን ለመቆጣጠር በነበረው ሂደትም አንድ የባለስልጣኑ ሰራተኛ ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የገለፁት ባለሙያው የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል።
ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኦሮሚያ ልዩ ዞን ቡራዩ ከተማ መግቢያ ላይ የሚገኘው #ኢንተማ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ሻማ ፋብሪካ ላይ በደረሰበት የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተገለፀ።
በዚህ የእሳት አደጋ ከፋብሪካው አቅራቢያ የሚገኙ ሁለት የንግድ ሱቆችና አንድ መኖሪያ ህንፃ ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ስለሺ ተስፋዬ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት ከሌሊቱ 9 ሰዓት ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ በአጠቃላይ 11 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ተናግረዋል።
ከንግድ ሱቆች 500 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት የወደመ ሲሆን ከመኖሪያ ህንፃውና ከሱቆቹ 7 ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማትረፍ መቻሉንም ገልፀዋል።
ባለስልጣኑ የእሳት አደጋውን ለመቆጣጠርም ከአመስት ቅርንጫፎቹ የተውጣቱ 80 የአደጋ ተቆጣጣሪ ባለሙያዎች፣217 ሺህ 500 ሊትር ውሃ፣ 5 ሺህ 975 ኬሚካል ፎም እና 13 ከባድ ተሸከርካሪዎችን መጠቀሙን አንስተዋል።
አደጋውን ለመቆጣጠር በነበረው ሂደትም አንድ የባለስልጣኑ ሰራተኛ ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን የገለፁት ባለሙያው የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል።
ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia