TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፌስቡክ⬆️በጥቂት ፎቶዎች እየሆነ ያለውን ተመልከቱት። ቤተሰባችን ተፅእኖ መፍጠር ይችላል። ብዙ ቦታ መድረስ እንችላለን።

አሁንም በፌስቡክ ገፃቹ ላይ ይህን ከታች ያለውን መልዕክት በመለጠፍ ፌስቡክን በፍቅር እና አንድነት እናጥለቅልቀው።
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
#ኢትዮጵያዊ ነኝ ዘረኝነትን ተጠይፌ ከፍቅር ጋር ተደምሬ ሀገሬን ለመለወጥ ተነስቻለሁ!

#ETHIOPIA ሼር!
Audio
አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ⬆️ከፋና ብሮድካስቲንግ ጋር የነበረው ቆይታ።

"ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው ምክንያቱም 80 ቀለም ስላለው!" ሀጫሉ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

በህገ ወጥ መንግድ ከደቡብ ምስራቅ ሸዋ ዞን ኢሉ ወረዳ ወደ ጅማ ሲጓጓዝ የነበረ 539 ሺህ ብር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት መሆኑን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ገንዘቡ የተያዘው ከምስራቅ አዲስ አበባ ገቢዎች ጽ/ቤት የስራ ሂደት ባለቤት በመሆን ይሰራ ከነበረው ስንታየሁ ይልማ ከተሰኘው ግለሰብ ነው፡፡

ገንዘቡ የተጫነበትን ተሽከርካሪ ሲያሽከረክር የነበረው አብዱራዛቅ አህመድ የተባለው ግለሰብም በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል፡፡

ተጠርጣሪው #ስንታየሁ_ይልማ ከስራው ጋር በተያያዘ ገንዘቡን በህገ ወጥ መንገድ ይዟል በመባል በፖሊስ ተጠርጥሯል፡፡

የመካከለኛ ግብር ከፋዮች መክፈያ ቀናቸውን አሳልፈው እንዳይቀጡ በማድረግ ሰነድ በመሰረዝና በመደለዝ ባልተገባ መንገድ ገንዘቡን ተቀብሏል በሚል በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገልጿል፡፡

ተጠርጣሪው ግብር ከፋዮች ለታክስ ቅጣት ክፍያ የሚያሲዙትን እና ተመላሽ የሚደረገውን ገንዘብ ከጽ/ቤቱ ሂሳብ አሰራር ውጪ ተመላሽ እንዲሆን ማድረጉን ፖሊስ አብራርቷል፡፡

በዚህ ድርጊትም መንግስት ማግኘት የነበረበትን አንድ ሚሊዮን ብር ማጣቱ ነው የተነገረው፡፡

ፖሊስም ከፌደራል ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ጋር በመተባበር የምርመራ ስራውን እያከናወነ ነው ተብሏል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

#ተዋዶ ያለበት እስላም ክርስቲያኑ
ተዘነጋሽ እንዴ ኢትዮጵያ መሆኑ!
.
.
እኛ ያለ ኢትዮጵያ ቦዶ ነን፤ ኢትዮጵያም ያለኛ ባዶ ነች!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከተለያዩ ክልሎች የተወጣጡ ቁጥራቸው 125 የሚሆኑ ወሰን ተሻጋሪ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰጭ ወጣቶች በባህር ዳር ከተማ ዙሪያ ልዩ ስሙ ሰባት አሚት በተባለ አካባቢ በአባይ ወንዝ ላይ የእምቦጭ አረምን የማስወገድ ሥራ ሰርተዋል፡፡

©VOA 24
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬇️

በአዲስ አበባ አሁን ላይ የሚታየውን ከፍተኛ የኤች አይቪ ኤድስ(HIV AIDS) የስርጭት ምጣኔ ለመቀነስ የምክርና የምርመራ አገልግሎትን ጨምሮ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ፡፡ በመዲናዋ የኤች አይቪ ኤድስ የስርጭት ምጣኔ 3 ነጥብ 4 በመቶ ላይ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

©ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update መቀለ⬇️

ከሁለት ሳምንት በፊት ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ፍቃድ ውጭ ገብተዋል ያላቸው አርባ አምስት የፌደራል ፖሊስ ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል አባላት ከመቀሌ እንዲመለሱ ተደርገዋል።

አባላቱ በአሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የመጡበት አላማም እስኪታወቅ ድረስ እንቅስቃሴቸው ተገድቦበ በፌደራል ካምፕ ውስጥ እንዲቆዩ ተደርጎ እንደነበር ለቢቢሲ ገልፀዋል።

የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳኢ ኃለፎም ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ የፀጥታ ችግር ባለመኖሩ የፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል አስፈላጊ አለመሆኑን ተናግረዋል። ጨምረውም ክልሉ ድጋፍ የሚጠይቀው ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ ነገር ሲያጋጥም ወይም በልዩ ሁኔታ ከተወሰነ መሆኑን ጠቅሰው "ሁለቱም ጉዳዮች እኛ ጋር የሉም" ብለዋል።

"ለተወሰኑ ቀናት የፌደራል ፖሊስ አባላት በካምፑ ውስጥ ቆይተዋል። ወደ ክልሉ የገቡበት መንገድ ችግር ነበረው። እኛ ባልጠየቅንበት እና በማናውቀው ጉዳይ ነው የመጡት" በማለት የፀረ-ሽብር ግብረ ኃይሉ ለምን መቀሌ እንደተገኘም ግልፅ እንዳልሆነም ተናግረዋል።

"ለምን እንደመጡ ከፌደራል መንግሥት ጋር መነጋገር ያስፈልግ ስለነበር፤ ከፌደራል መንግሥት ጋር እስክንግባባ በቦታው እንዲቆዩ ተደርጓል። አሁን ደግሞ እዚህ መቆየታቸው የሚጨምረው ነገር ስለሌለ ወደመጡበት አካባቢ እንዲመለሱ አድርገናል።" ብለዋል

በወቅቱ የፌደራል ፖሊስና የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳኢ ጉዳዩን መካዳቸው የሚታወስ ነው። የዚያ አይነት ምላሽ የተሰጠበት ምክንያት እንደነበረው አቶ ረዳኢ ይናገራሉ።

"እውነት ነው ለተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ተራ ወሬ ነው የሚል መልስ ስንሰጥ ቆይተናል። ምክንያቱም በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከእውነት የራቀ መረጃ እየተሰራጨ ስለነበርና፤ ለትግራይ ህዝብ እና ለትግራይ መንግስት ብሎም ለስርአቱ ስለማይጠቅም የሚሰሩ ስራዎች ተሰርተው ወቅቱን ጠብቆ በትክክለኛ ጊዜ መነገር ስለነበረበት ነው" ብለዋል።

የፌደራል ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል ከክልሉ መንግሥት ፍቃድ ውጭ መግባቱን አስመልክቶ ከፌደራል መንግሥት ጋር ቅራኔ ተፈጥሮ እንደሆነ አቶ ረዳኢን ቢቢሲ ጠይቋቸዋል።

"ከፌደራል መንግሥት ጋር የሚያቃቅር ነገር የለም። ለተልእኮ መጥተው ከሆነ ለዚያ የሚሆን ነገር የለም። አንድ ሃገር ከመሆናችን አንፃር ከመረዳዳት ውጭ ምንም ነገር የለም" ብለዋል።

የክልሉ መንግሥት ግብረ ኃይሉ እንዲወጣ ባዘዛው መሰረት ዛሬ ወደ አዲስ አበባ መመለሱ ተገልጿል።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ⬆️የትምህርት ሚኒስቴር ባሉት ክፍት የስራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

©Giz
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለ1ኛ አመት ተማሪዎች⬆️በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ገብታችሁ መማር የምትፈልጉ መዝገባ እየተከናወነ ይገኛል። የመመዝገቢያ መስፈርቶቹን ከላይ ባለው ማስታወቂያ ታገኛላችሁ።

#ሼር
©Giza
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከደ/ም/ሸዋ ጎሮ⬇️

"በደ/ም/ሸዋ ጎሮ ውስጥ አዳሚ ቀበሌ ከቀኑ 11:00 ሰዓት ከብት በመጠበቅ ላይ የነበረ ታዳጊ አካባቢው ባለ ከግልገል ጊቤ ወደ ወሊሶ በሚመጣ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ የብረት ምሰሶ ላይ በመውጣቱ ገመዱጋ ሳይደርስ የነበረው ከፍተኛ ሀይልና ስበት የለበሰውን ልብስ አቃጥሎ ጨርሶ በሰውነቱ ላይም ከፍተኛ #ጉዳት ደርሶበት በህዝብ ትብብርና በተለያዩ ቦታዎች በመደወል እንዲጠፋ ተደርጎ ህይወቱ ሊተርፍ ችሏል፡፡"

ይህን መልዕክር ያነበችሁ የቻናላችን ቤተሰቦች #ጥንቃቄ ማድረግ እንዳትዘነጉ!

©Akililu
@tsegabwolde @tikvahethiopia