“ ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም። ” - ኢሕአፓ ስለታሰረው አመራሩ
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የአዲስ አበባ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ አባሉ አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንደታሰሩበት ገልጿል።
ፓርቲው አመራሬ “በሐሰተኛ ፍረጃ ነው” የታሰሩብኝ ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት መጋቢብሉይ አብርሃም ሃይማኖት በሰጡት ቃል ፥ " የካቲት 6/2017 ዓ/ም ከቤታቸው በፓሊስ ተወስደው ነው የታሰሩት። ' ፋኖ ይደግፋል ' በሚል ሐሰተኛ ውንጀላ ነው የተወነጀለው " ሲሉ ገልጸዋል።
የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ሰላማዊ ታጋዮችን በሐሰተኛ መረጃ እያሸማቀቁ እያሰሩ፤ ጋዜጠኞችን እያሳደዱ ሀገር ሰላም ማድረግ አይቻልም። ስለዚህ ሰላም ጠሉ ራሱ መንግስት እንደሆነ ነው እያረጋገጠልን ያለው።
አቶ ይሳቅ ከተባለበት ጉዳይ ጋር የሚያያይዘው አንዳችም ነገር የለም። መንግስት ሕግ ማክበር እንዳለበት የዘነጋው ይመስለኛል። መንግስት ሕገ መንግስቱን አክብሮ ነው የሚያስከብረው፤ ራሱ እየደፈጠጠ መሆን የለበትም።
ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም። ግን ‘የአፍሪካ ህብረትን ለመበጥበጥ፣ መሪዎችን ለመግደል’ የሚል ሐሰተኛ ፈጠራ ሲያቀናብሩ አእምሯቸው እንዴት አቀናበረው ? ብለን እንድንጠይቅ አድርጎናል።
ከዚህ በፊት ዓርዓያ ተስፋማርያም በሚባል ጋዜጠኛ ነኝ በሚል ግለሰብ ይሄው አባላችን ታስሮ በጩኸት ወጥቷል። አሁንም በሐሰተኛ ቅንብር፣ ከመንግስት አካላት ጋር ያላቸው ግንኙነትን በመጠቀም ታስሯል ” ብለዋል።
አመራሩ ከ“ፋኖ” ጋር በተገናኘ የተጠረጠሩት ፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን ከምን ጋር አገናኝቶት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ በኮሪደር ልማት አዲስ አበባ ቤት የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ካሳ እንዳልተከፈላቸው በማጋለጣቸው ነው ሲሉ ጠቅሰዋል።
አክለው፣ “ ያንን ተከትሎ ኢሕአፓን ለማሸማቀቅና ቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጠንካራ ሰላማዊ ትግል እንዳያደርግ ሆን ተብሎ ለማስፈራራት የተቀናበረ ቅንብር ነው ” ብለው፣ ፓርቲው በዚህ እንደማይሸማቀቅ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የፌደራል ፓሊስ የምርመራ ጊዜ ማጣሪያ የጠየቀበት ደብዳቤ፣ ከአቶ ይሳቅ ጋር 13 ግለሰቦችን ጠቅሶ " በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሰው " ቡድን ግንኙነት አላቸው በሚል ይወነጅላል።
ፓሊስ፣ “ ምርመራውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት ” የ14 ቀናት የቀጠሮ ጊዜ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረቡን ደብዳቤው ያትታል።
የፓርቲው ተቀዳሚ ከንቲባ በበኩላቸው፣ “ ሰኞ ፍርድ ቤት ለኛ ቀጠሮ ሰጥቶናል የፌደራል ፓሊስ የ14 ቀን ቀጠሮን ውድቅ በማድረግ ‘ተጨባጭ መረጃ ካላችሁ አምጡ’ በማለት” ብለዋል።
“ ፍርድ ቤቱም ‘እንደዚህ አይነት ሐሰተኛ ቅንብሮች እየተለመደ ስለመጡ ተጨባጭ ነገር ካለ አምጡ አለዚያ ጊዜ ቀጠሮ አልሰጣችሁም’ ብሎ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል ” ነው ያሉት።
13ቱም “ተጠርጣሪዎች” የፓርቲው አካላት ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው ተቀዳሚ ፕሬዛዳንቱ፤ ከአቶ ይሳቅ ውጪ ያሉት 12 ተጠረጠሩ ተብለው የታሰሩ ግለሰቦች ከፓርቲው ጋ ግንኙነት እንደሌላቸው አስረድተዋል።
“ ነጋዴዎች አሉ ምንም ፓለቲካ ውስጥ የሌሉ። በተጨባጭ መረጃ ያለን አንድ ካድሬ ከጠላ ይፈርጅህና ለወራት ታሽተህ ትለቀቃለህ። ዜጎችን ማሸማቀቂያ፣ ማሰቃያ ሆኗል የፍትህ ስርዓቱ ” ሲሉ ወቅሰዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) የአዲስ አበባ ኮሚቴ ሥራ አስፈጻሚ አባሉ አቶ ይሳቅ ወልዳይ እንደታሰሩበት ገልጿል።
ፓርቲው አመራሬ “በሐሰተኛ ፍረጃ ነው” የታሰሩብኝ ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት መጋቢብሉይ አብርሃም ሃይማኖት በሰጡት ቃል ፥ " የካቲት 6/2017 ዓ/ም ከቤታቸው በፓሊስ ተወስደው ነው የታሰሩት። ' ፋኖ ይደግፋል ' በሚል ሐሰተኛ ውንጀላ ነው የተወነጀለው " ሲሉ ገልጸዋል።
የፓርቲው ተቀዳሚ ፕሬዜዳንት በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ሰላማዊ ታጋዮችን በሐሰተኛ መረጃ እያሸማቀቁ እያሰሩ፤ ጋዜጠኞችን እያሳደዱ ሀገር ሰላም ማድረግ አይቻልም። ስለዚህ ሰላም ጠሉ ራሱ መንግስት እንደሆነ ነው እያረጋገጠልን ያለው።
አቶ ይሳቅ ከተባለበት ጉዳይ ጋር የሚያያይዘው አንዳችም ነገር የለም። መንግስት ሕግ ማክበር እንዳለበት የዘነጋው ይመስለኛል። መንግስት ሕገ መንግስቱን አክብሮ ነው የሚያስከብረው፤ ራሱ እየደፈጠጠ መሆን የለበትም።
ይሳቅ ህሩይ የትግራዋይ ነው። ከፋኖ ጋር ሊያገናኘው የሚችል አንዳችም ነገር የለም። ግን ‘የአፍሪካ ህብረትን ለመበጥበጥ፣ መሪዎችን ለመግደል’ የሚል ሐሰተኛ ፈጠራ ሲያቀናብሩ አእምሯቸው እንዴት አቀናበረው ? ብለን እንድንጠይቅ አድርጎናል።
ከዚህ በፊት ዓርዓያ ተስፋማርያም በሚባል ጋዜጠኛ ነኝ በሚል ግለሰብ ይሄው አባላችን ታስሮ በጩኸት ወጥቷል። አሁንም በሐሰተኛ ቅንብር፣ ከመንግስት አካላት ጋር ያላቸው ግንኙነትን በመጠቀም ታስሯል ” ብለዋል።
አመራሩ ከ“ፋኖ” ጋር በተገናኘ የተጠረጠሩት ፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን ከምን ጋር አገናኝቶት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ በኮሪደር ልማት አዲስ አበባ ቤት የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ካሳ እንዳልተከፈላቸው በማጋለጣቸው ነው ሲሉ ጠቅሰዋል።
አክለው፣ “ ያንን ተከትሎ ኢሕአፓን ለማሸማቀቅና ቀጣይ የሚያደርጋቸውን ጠንካራ ሰላማዊ ትግል እንዳያደርግ ሆን ተብሎ ለማስፈራራት የተቀናበረ ቅንብር ነው ” ብለው፣ ፓርቲው በዚህ እንደማይሸማቀቅ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የፌደራል ፓሊስ የምርመራ ጊዜ ማጣሪያ የጠየቀበት ደብዳቤ፣ ከአቶ ይሳቅ ጋር 13 ግለሰቦችን ጠቅሶ " በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሰው " ቡድን ግንኙነት አላቸው በሚል ይወነጅላል።
ፓሊስ፣ “ ምርመራውን በሰውና በሰነድ ማስረጃ በስፋት ለማጣራት ” የ14 ቀናት የቀጠሮ ጊዜ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤት ጥያቄ ማቅረቡን ደብዳቤው ያትታል።
የፓርቲው ተቀዳሚ ከንቲባ በበኩላቸው፣ “ ሰኞ ፍርድ ቤት ለኛ ቀጠሮ ሰጥቶናል የፌደራል ፓሊስ የ14 ቀን ቀጠሮን ውድቅ በማድረግ ‘ተጨባጭ መረጃ ካላችሁ አምጡ’ በማለት” ብለዋል።
“ ፍርድ ቤቱም ‘እንደዚህ አይነት ሐሰተኛ ቅንብሮች እየተለመደ ስለመጡ ተጨባጭ ነገር ካለ አምጡ አለዚያ ጊዜ ቀጠሮ አልሰጣችሁም’ ብሎ ጥያቄ አቅርቦላቸዋል ” ነው ያሉት።
13ቱም “ተጠርጣሪዎች” የፓርቲው አካላት ናቸው ? ስንል የጠየቅናቸው ተቀዳሚ ፕሬዛዳንቱ፤ ከአቶ ይሳቅ ውጪ ያሉት 12 ተጠረጠሩ ተብለው የታሰሩ ግለሰቦች ከፓርቲው ጋ ግንኙነት እንደሌላቸው አስረድተዋል።
“ ነጋዴዎች አሉ ምንም ፓለቲካ ውስጥ የሌሉ። በተጨባጭ መረጃ ያለን አንድ ካድሬ ከጠላ ይፈርጅህና ለወራት ታሽተህ ትለቀቃለህ። ዜጎችን ማሸማቀቂያ፣ ማሰቃያ ሆኗል የፍትህ ስርዓቱ ” ሲሉ ወቅሰዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
🔴 “ የተሰጠው መልስ ከእውነት የራቀና በህዝቡ ስቃይ እንደመሳለቅ የሚቆጠር ነው ” - አርሶ አደሮች
➡️ “ አንድ ኩንታል እንደዬአካባቢው ስለሚለያይ ይህን ያክል ነው ብለን ለመግለጽ ያስቸግረናል ” - ግብርና ሚኒስቴር
ሀዋሳ ዙሪያ የሚገኙ አርሶ አደሮች የማዳበሪያና በበቆሎ ምርጥ ዘር ዘንድሮ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከአምናው እጥፍ በላይ በመጨመሩ ማምረት እንደማይችሉ ሰሞኑን በቲክቫህ ኢትዮጵያ ድምፃቸውን ማሰማታቸው አይዘነጋም።
“ አምና 3,600 ብር ስንገዛው የነበረውን ማዳበሪያ ዘንድሮ 8,400 ብር ለመግዛት ተገደናል። አምና 1,800 ብር የነበረው የአንድ ፕሎት ምርጥ ዘር በቆሎ ዘንድሮ 4,600 ብር ገብቷል ” ሲሉ ነበር ያማረሩት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወቅቱ ምላሽ የጠየቀው የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ፣ “ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። የጨመርነው ነገር የለም። የትራንስፓርት ብቻ ነው የጨመርነው ” ብሎ፣ የምርጥ ዘር በቆሎ ዋጋም ከትራክተር፣ ከነዳጅ ዋጋ ጋር በተያያዘ መጨመሩን ቢሮው አልደበቀም።
አርሶ አደሮቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
“ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ ካለመሆኑም አልፎ ከእውነት የራቀና በህዝቡ ስቃይ እንደመሳለቅ የሚቆጠር ነው። ምላሹ ‘ማዳበሪያ ላይ የተደረገው ጭማሪ የትራንስፖርት ብር ብቻ ነው’ ብሏል።
የትራንስፖርቱ ብቻ ሳይሆን ለማዳበሪያ በአመት 4,000 ብር መጨመር ዝርፊያ እንጂ ጭማሪ አይባልም። የበቆሎውን በተመለከተም ቢሮው፣ የትራክተርና የነዳጅ ጭማሬን በመጥቀስ ነው ምላሽ የሰጠው።
ለህዝቡ ማሳውን የሚያርሰው መንግስት አይደለም ህዝቡ በራሱ ገንዘብ እንጂ። ስለዚህ የማይገናኝ ነገር አገናኝቶ ህዝቡን ማሰቃየት አግባብ አይደለም።
በቆሎ የሚዘራው ከታህሳስ 15 ጀምሮ ነው። የሻመና ህዝብ ለአንድ ፕሎት እስከ 17,000 ብር በላይ አውጥቶ እንዴት ሊገዛ ይችላል ? ምንስ ሊያተርፍ ነው ? በዚህ ኑሮ ውድነት ገንዘቡንስ የት ነው የሚያመጣው ? ነው ወይስ ህዝቡን ነገ በረሃብ መቅጣት ነው የተፈለገው ?
በአንድ በኩል ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ የማይጠቀም አርሶ አደር እንዳይኖር ያስገድዳሉ፣ በሌላ በኩል ዋጋ በማናር እንዳይጠቀም ማድረግ አይጋጭም ? አርሶ አደሩ ዘንድሮ ምርት አያመርትም። መንግስት ችግሩን ይፍታልን ” ሲሉ አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ማዳበሪያ ወደ አርሶ አደሩ ሲከፋፈል ዋጋው ምን ያክል ነው ? አርሶ አደሮች ዘንድሮ የተጋጋነ ዋጋ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል። ጭማሬው ከላይ ነው ከታች ? ኩንታል ማዳበሪያ (ለምሳሌ ዳፕ) ዋጋው ስንት ነው ? ሲል ለግብርና ሚኒስቴር ጥያቄ አቅርቧል።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ምን መለሱ?
“ አንድ ኩንታል እንደዬአካባቢው ስለሚለያይ ይህን ያክል ነው ብለን ለመግለጽ ያስቸግረናል። ምክንያቱም በርቀቱ ስለሚወሰን። በትራንስፓርት ነው የሚለያዩት።
ከዚያ ውጪ በሁሉም የአገራቷ ክፍል የሚሰራጨውን ማዳበሪያ ሴንትራሊ ዋጋ አውጥቶ የሚልከው ግብርና ሚኒስቴር ነው። ዋጋ ስናወጣ በግብርና ሚኒስቴር በኩል የሚጨመር ምንም አይነት የፕሮፊት ማሪጅን የለም።
ማዳበሪያው የተገዛበት፣ የትራንስፓርትና ሌሎች እንዲሁም ወጪዎች ተደርገው የአንድ ኩንታል ዋጋ ተሰልቶ ነው ወደ ታች የሚወርደው። መንግስት 84 ቢሊዮን ብር ድጎማ አድርጓል።
ማዳበሪያ ከአምናው አንጸር ሲወዳደር ዋጋ በተወሰነ መንገድ ጨምሯል። ስለዚህ ታች የጨመረ ዋጋ ሳይሆን ማዳበሪያው የተገዛበት፣ ከሪፎርሙ ጋር የተወሰነ የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ስላለ፣ በዚያ ምክንያት የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል።
ማዳበሪያ በዶላር ከውጪ ነው የሚገዛው። ታች ሊጨመር የሚችለው ትንሽዬ ወይ 100 ብር ወይ 50 ብር የዩኒየን ማሪጅን፣ ወደ ታች ደግሞ ሲወርድ እኛ እስከ ማዕከላዊ መጋዘን ነው የምናቀርበው።
ከማዕከላዊ መጋዘን ወደ መሠረታዊ ህብረት ሥራ ማኀበር ሲያወርዱ ሁሉም ክልሎች እንደየርቀቱ የትራንስፓርት ዋጋ ልዩነት ይኖራል።
ስለዚህ አንድ ኩንታል ዋጋ ይሄን ያክል ብር ነው ብልህ ሀገራዊ ዋጋን ሪፕረሰንት ስለማያደርግ እንደዬ አካባቢው የተለያዬ ነው የሚሆነው። ግን ሴንትራሊ ለሁሉም የተገዛበትም ድጎማውም እኩል ነው የሚሰራው ” ብለዋል።
በአጠቃላይ ያለውን አቅርቦት ሲያስረዱም፣ “ 24 ሚሊዮን ኩንታል ነው የምናቀርበው። እስካሁን የ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ግዥ ፈጸመናል ” ነው ያሉት።
(ማዳበሪያን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ የምናቀርብ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ የተሰጠው መልስ ከእውነት የራቀና በህዝቡ ስቃይ እንደመሳለቅ የሚቆጠር ነው ” - አርሶ አደሮች
➡️ “ አንድ ኩንታል እንደዬአካባቢው ስለሚለያይ ይህን ያክል ነው ብለን ለመግለጽ ያስቸግረናል ” - ግብርና ሚኒስቴር
ሀዋሳ ዙሪያ የሚገኙ አርሶ አደሮች የማዳበሪያና በበቆሎ ምርጥ ዘር ዘንድሮ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከአምናው እጥፍ በላይ በመጨመሩ ማምረት እንደማይችሉ ሰሞኑን በቲክቫህ ኢትዮጵያ ድምፃቸውን ማሰማታቸው አይዘነጋም።
“ አምና 3,600 ብር ስንገዛው የነበረውን ማዳበሪያ ዘንድሮ 8,400 ብር ለመግዛት ተገደናል። አምና 1,800 ብር የነበረው የአንድ ፕሎት ምርጥ ዘር በቆሎ ዘንድሮ 4,600 ብር ገብቷል ” ሲሉ ነበር ያማረሩት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወቅቱ ምላሽ የጠየቀው የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ፣ “ ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል። የጨመርነው ነገር የለም። የትራንስፓርት ብቻ ነው የጨመርነው ” ብሎ፣ የምርጥ ዘር በቆሎ ዋጋም ከትራክተር፣ ከነዳጅ ዋጋ ጋር በተያያዘ መጨመሩን ቢሮው አልደበቀም።
አርሶ አደሮቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
“ የሲዳማ ክልል ግብርና ቢሮ የሰጠው ምላሽ አጥጋቢ ካለመሆኑም አልፎ ከእውነት የራቀና በህዝቡ ስቃይ እንደመሳለቅ የሚቆጠር ነው። ምላሹ ‘ማዳበሪያ ላይ የተደረገው ጭማሪ የትራንስፖርት ብር ብቻ ነው’ ብሏል።
የትራንስፖርቱ ብቻ ሳይሆን ለማዳበሪያ በአመት 4,000 ብር መጨመር ዝርፊያ እንጂ ጭማሪ አይባልም። የበቆሎውን በተመለከተም ቢሮው፣ የትራክተርና የነዳጅ ጭማሬን በመጥቀስ ነው ምላሽ የሰጠው።
ለህዝቡ ማሳውን የሚያርሰው መንግስት አይደለም ህዝቡ በራሱ ገንዘብ እንጂ። ስለዚህ የማይገናኝ ነገር አገናኝቶ ህዝቡን ማሰቃየት አግባብ አይደለም።
በቆሎ የሚዘራው ከታህሳስ 15 ጀምሮ ነው። የሻመና ህዝብ ለአንድ ፕሎት እስከ 17,000 ብር በላይ አውጥቶ እንዴት ሊገዛ ይችላል ? ምንስ ሊያተርፍ ነው ? በዚህ ኑሮ ውድነት ገንዘቡንስ የት ነው የሚያመጣው ? ነው ወይስ ህዝቡን ነገ በረሃብ መቅጣት ነው የተፈለገው ?
በአንድ በኩል ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ የማይጠቀም አርሶ አደር እንዳይኖር ያስገድዳሉ፣ በሌላ በኩል ዋጋ በማናር እንዳይጠቀም ማድረግ አይጋጭም ? አርሶ አደሩ ዘንድሮ ምርት አያመርትም። መንግስት ችግሩን ይፍታልን ” ሲሉ አሳስበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ማዳበሪያ ወደ አርሶ አደሩ ሲከፋፈል ዋጋው ምን ያክል ነው ? አርሶ አደሮች ዘንድሮ የተጋጋነ ዋጋ ጭማሪ እንደተደረገባቸው ገልጸዋል። ጭማሬው ከላይ ነው ከታች ? ኩንታል ማዳበሪያ (ለምሳሌ ዳፕ) ዋጋው ስንት ነው ? ሲል ለግብርና ሚኒስቴር ጥያቄ አቅርቧል።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) ምን መለሱ?
“ አንድ ኩንታል እንደዬአካባቢው ስለሚለያይ ይህን ያክል ነው ብለን ለመግለጽ ያስቸግረናል። ምክንያቱም በርቀቱ ስለሚወሰን። በትራንስፓርት ነው የሚለያዩት።
ከዚያ ውጪ በሁሉም የአገራቷ ክፍል የሚሰራጨውን ማዳበሪያ ሴንትራሊ ዋጋ አውጥቶ የሚልከው ግብርና ሚኒስቴር ነው። ዋጋ ስናወጣ በግብርና ሚኒስቴር በኩል የሚጨመር ምንም አይነት የፕሮፊት ማሪጅን የለም።
ማዳበሪያው የተገዛበት፣ የትራንስፓርትና ሌሎች እንዲሁም ወጪዎች ተደርገው የአንድ ኩንታል ዋጋ ተሰልቶ ነው ወደ ታች የሚወርደው። መንግስት 84 ቢሊዮን ብር ድጎማ አድርጓል።
ማዳበሪያ ከአምናው አንጸር ሲወዳደር ዋጋ በተወሰነ መንገድ ጨምሯል። ስለዚህ ታች የጨመረ ዋጋ ሳይሆን ማዳበሪያው የተገዛበት፣ ከሪፎርሙ ጋር የተወሰነ የነዳጅ ዋጋ ጭማሬ ስላለ፣ በዚያ ምክንያት የማዳበሪያ ዋጋ ጨምሯል።
ማዳበሪያ በዶላር ከውጪ ነው የሚገዛው። ታች ሊጨመር የሚችለው ትንሽዬ ወይ 100 ብር ወይ 50 ብር የዩኒየን ማሪጅን፣ ወደ ታች ደግሞ ሲወርድ እኛ እስከ ማዕከላዊ መጋዘን ነው የምናቀርበው።
ከማዕከላዊ መጋዘን ወደ መሠረታዊ ህብረት ሥራ ማኀበር ሲያወርዱ ሁሉም ክልሎች እንደየርቀቱ የትራንስፓርት ዋጋ ልዩነት ይኖራል።
ስለዚህ አንድ ኩንታል ዋጋ ይሄን ያክል ብር ነው ብልህ ሀገራዊ ዋጋን ሪፕረሰንት ስለማያደርግ እንደዬ አካባቢው የተለያዬ ነው የሚሆነው። ግን ሴንትራሊ ለሁሉም የተገዛበትም ድጎማውም እኩል ነው የሚሰራው ” ብለዋል።
በአጠቃላይ ያለውን አቅርቦት ሲያስረዱም፣ “ 24 ሚሊዮን ኩንታል ነው የምናቀርበው። እስካሁን የ13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ግዥ ፈጸመናል ” ነው ያሉት።
(ማዳበሪያን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ የምናቀርብ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሥራ ዘመን ለአንድ አመት ተራዘመ።
ኮሚሽኑ ዛሬ የሦስት አመታት ሪፓርቱን ለፓርላማ ያቀረበ ሲሆን፣ የፓርላማ አባላት በሪፓርቱ ላይ የተለዩዩ ጥያቄዎችንና አስተየቶችን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ሦስት አመቱን የካቲት 14 ቀን በመድፈን የሥራ ዘመኑ ይጠናቀቅ የነበረው ኮሚሽኑ፣ በፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቶታል።
በቋሚ ኮሚቴው የተሰጠው የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ውሳኔው የቀረበበት ሦስት የተቃውሞ ድምፅ ብቻ ነው።
በተለይ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ስላለው ሁኔታ የፓርላማ አባላት ያነሷቸውን ነጥቦችና የተሰጡ ምላሾችን በተመለከተ ተጨማሪ ይኖረናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ኮሚሽኑ ዛሬ የሦስት አመታት ሪፓርቱን ለፓርላማ ያቀረበ ሲሆን፣ የፓርላማ አባላት በሪፓርቱ ላይ የተለዩዩ ጥያቄዎችንና አስተየቶችን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ሦስት አመቱን የካቲት 14 ቀን በመድፈን የሥራ ዘመኑ ይጠናቀቅ የነበረው ኮሚሽኑ፣ በፓርላማው ቋሚ ኮሚቴ የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ተሰጥቶታል።
በቋሚ ኮሚቴው የተሰጠው የአንድ አመት ተጨማሪ ጊዜ ውሳኔው የቀረበበት ሦስት የተቃውሞ ድምፅ ብቻ ነው።
በተለይ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ስላለው ሁኔታ የፓርላማ አባላት ያነሷቸውን ነጥቦችና የተሰጡ ምላሾችን በተመለከተ ተጨማሪ ይኖረናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
🔴 “ የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም ” - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
➡️ “ ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አልመጣም ብዬ አላስብም ” - ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመታት ሪፓርት ለፓርላማ ማቅረቡ፣ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ/ም ሦስት አመቱን የሚደፍነው የኮሚሽኑ የሥራ ጊዜ በቋሚ ኮሚቴው ለአንድ አመት መራዘሙ ታውቋል።
ኮሚሽኑ በሪፓርቱ፣ በ10 ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች የምክክር፣ የአጀንዳ ልየታ እና ለሀገራዊ ምክክር የሚሳተፉ ተወካዮች የማስመረጥ ተግባራትን እንዳጠናቀቀ አመልክቷል።
በአማራ ክልል ያለው ሥራ መቀጠሉን፣ የትግራይ ክልል ገና መሆኑም ተመላክቷል።
ሪፓርቱ በቀረበበት ወቅት የፓርላማ አባት ያነሷቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው ?
የኮሚሽኑ ሪፓርት ከቀረበ በኋላ አብዛኛዎቹ የፓርላማ አባላት በተለይ የጸጥታ ችግር ያሉባቸው አካባቢዎች ለምክክሩ የገጣማቸውን የተሳትፎ ውጥንቅጥ የሚመለከቱ ጥቄዎችን ሰንዝረዋል።
አንድ የፓርላማ አባል፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ማኅበረሰቡ በንቃት ነው የተሳተፈው? ለሀገር እንቅፋት የሆኑ ነገሮችን ለማስቀረት ኮሚሽኑ ምን እየሰራ ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
ሌላኛው የፓርላማ አባል ደግሞ፣ ፓርቲዎች ከምክክሩ የወጡበት ምክንያት ምንድን ነው? አጀንዳቸውን አሁንስ በምን መልኩ ነው የሚሰጡት? በማለት ጠይቀዋል።
የታጠቁ ኃይሎችና አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዳልተሳተፉ ሲናገሩ የተደመጡት ሌላኛው የፓርላማ አባል፣ ወደ ፊት ኮሚሽኑ በዚሁ ጉዳይ ምን ለመስራት እንዳሰበ ማብራሪያ ጠይቀዋል።
ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጠው ኮሚሽኑ በበኩሉ፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎችም የህዝቡ ተሳትፎ ጥሩ እንደነበር፣ ፓርቲዎችም ሆኑ ታጣቂዎች አሁንም አጀንዳቸውን ካቀረቡ በሩ ክፍት መሆኑን ገልጿል።
የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ምን ጠየቁ?
ጠንከር ያሉ ሀሳቦችን በማቅረብ የሚታወቁት የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)፣ “የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም” ሲሉ ተችተዋል።
በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት አጀንዳቸውን እንዳላቀረቡ፣ የአካታትነት ችግር እንዳለ ገልጸው፣ “ይህ ባልተካሄደበት ሁኔታ ምን አይነት ምክክር ማድረግ ይቻላል?” ሲሉም ጠይቀዋል።
በአማራም ሆነ ኦሮሚያ ክልሎች ባለው ጦርነት ኮሚሽኑ የተኩስ አቁም ጥሪ ማድረግ እንደሚገባው ገልጸው፣ “ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የቁርጠኝነት ችግር እንዳለ አያለሁ” ነው ያሉት።
እንዲሁም የጸጥታ ችግር ዜጎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው የመመካከር ደኅንነታቸው ላይ ችግር መፍጠሩንም የተናገሩ ሲሆን፣ “አማራ ክልል ህዝቡ ከፍተኛ ትራውማ ውስጥ ገብቷል። ከክልሉ ውጪ ያሉትም የማንነት ጥቃት ሰለባ ሆነዋል” ብለዋል።
ሥጋት ለሚያነሱ ሰዎች የተለያዩ ፍረጃዎች እየተሰጠ የሚኬደው ነገር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ በትጥቅ ትግል ያሉ አካላትን እንዲያካትት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ፣ መንግስትና በልጽግና አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ለዚሁ ጥያቄ አጸፋ የሰጡት በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ እነደሳለኝና አብን ፓርቲያቸው ምን አስተዋጽኦ አድርጓል? ሲሉ ጠይቀዋል።
የታጠቁ አካላት በምክክሩ ባለመሳተፋቸው ደሳለኝ (ዶ/ር) ባቀረቡት ትችት የተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አጸፋ፣ “የታጠቁ ቡድኖችም ሁሉም አይደሉም ያልተሳተፉት” ሲሉ ተደምጠዋል።
የተሰወሱ የፋኖ ክንፎች ሁኔታም አንስተው፣ እነ ጃል ሰኒ ደግሞ በምክክሩ እንደተሳተፉ የገለጹ ሲሆን፣ “የቀሩት የሸኔ ክፋይ የተለዬ ሀሳብ አላቸው ብለን አናምንም” ብለዋል።
ተስፋዬ ዶ/ር)፣ ጉዳዩን እያጋጋልን ነው የቆየነው ወይስ ጉዳዩ ወደ መሀል እንዲመጣ አድርገን ለመፍትሄ እየሰራን? ሲሉም ፓርቲዎችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
የሀገሪዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ በአማራ ክልል የተሳትፎ ልየታ እንዳደረገ፣ የቀሩት 8 ወረዳዎች ብቻ እንደሆኑ ምላሽ ሰጥተዋል።
በጫካ ስላሉ አካላት አጀንዳ አለመቅረብ በተመለከተ የቀረበውን ጥያቄ ሲመልሱም፣ “ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አላመጡም ብዬ አላስብም” ብለው፣ በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን፣ ጎንደር ያሉ ክላስተሮች የሕዝቡን ችግር እንዳስረዷቸው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም ” - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
➡️ “ ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አልመጣም ብዬ አላስብም ” - ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመታት ሪፓርት ለፓርላማ ማቅረቡ፣ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ/ም ሦስት አመቱን የሚደፍነው የኮሚሽኑ የሥራ ጊዜ በቋሚ ኮሚቴው ለአንድ አመት መራዘሙ ታውቋል።
ኮሚሽኑ በሪፓርቱ፣ በ10 ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች የምክክር፣ የአጀንዳ ልየታ እና ለሀገራዊ ምክክር የሚሳተፉ ተወካዮች የማስመረጥ ተግባራትን እንዳጠናቀቀ አመልክቷል።
በአማራ ክልል ያለው ሥራ መቀጠሉን፣ የትግራይ ክልል ገና መሆኑም ተመላክቷል።
ሪፓርቱ በቀረበበት ወቅት የፓርላማ አባት ያነሷቸው ጥያቄዎች ምንድን ናቸው ?
የኮሚሽኑ ሪፓርት ከቀረበ በኋላ አብዛኛዎቹ የፓርላማ አባላት በተለይ የጸጥታ ችግር ያሉባቸው አካባቢዎች ለምክክሩ የገጣማቸውን የተሳትፎ ውጥንቅጥ የሚመለከቱ ጥቄዎችን ሰንዝረዋል።
አንድ የፓርላማ አባል፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ማኅበረሰቡ በንቃት ነው የተሳተፈው? ለሀገር እንቅፋት የሆኑ ነገሮችን ለማስቀረት ኮሚሽኑ ምን እየሰራ ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
ሌላኛው የፓርላማ አባል ደግሞ፣ ፓርቲዎች ከምክክሩ የወጡበት ምክንያት ምንድን ነው? አጀንዳቸውን አሁንስ በምን መልኩ ነው የሚሰጡት? በማለት ጠይቀዋል።
የታጠቁ ኃይሎችና አንዳንድ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዳልተሳተፉ ሲናገሩ የተደመጡት ሌላኛው የፓርላማ አባል፣ ወደ ፊት ኮሚሽኑ በዚሁ ጉዳይ ምን ለመስራት እንዳሰበ ማብራሪያ ጠይቀዋል።
ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጠው ኮሚሽኑ በበኩሉ፣ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎችም የህዝቡ ተሳትፎ ጥሩ እንደነበር፣ ፓርቲዎችም ሆኑ ታጣቂዎች አሁንም አጀንዳቸውን ካቀረቡ በሩ ክፍት መሆኑን ገልጿል።
የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ምን ጠየቁ?
ጠንከር ያሉ ሀሳቦችን በማቅረብ የሚታወቁት የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)፣ “የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም” ሲሉ ተችተዋል።
በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት አጀንዳቸውን እንዳላቀረቡ፣ የአካታትነት ችግር እንዳለ ገልጸው፣ “ይህ ባልተካሄደበት ሁኔታ ምን አይነት ምክክር ማድረግ ይቻላል?” ሲሉም ጠይቀዋል።
በአማራም ሆነ ኦሮሚያ ክልሎች ባለው ጦርነት ኮሚሽኑ የተኩስ አቁም ጥሪ ማድረግ እንደሚገባው ገልጸው፣ “ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የቁርጠኝነት ችግር እንዳለ አያለሁ” ነው ያሉት።
እንዲሁም የጸጥታ ችግር ዜጎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው የመመካከር ደኅንነታቸው ላይ ችግር መፍጠሩንም የተናገሩ ሲሆን፣ “አማራ ክልል ህዝቡ ከፍተኛ ትራውማ ውስጥ ገብቷል። ከክልሉ ውጪ ያሉትም የማንነት ጥቃት ሰለባ ሆነዋል” ብለዋል።
ሥጋት ለሚያነሱ ሰዎች የተለያዩ ፍረጃዎች እየተሰጠ የሚኬደው ነገር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ በትጥቅ ትግል ያሉ አካላትን እንዲያካትት አስተያየት የሰጡ ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ፣ መንግስትና በልጽግና አስቻይ ሁኔታ ፈጥሯል ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ለዚሁ ጥያቄ አጸፋ የሰጡት በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ እነደሳለኝና አብን ፓርቲያቸው ምን አስተዋጽኦ አድርጓል? ሲሉ ጠይቀዋል።
የታጠቁ አካላት በምክክሩ ባለመሳተፋቸው ደሳለኝ (ዶ/ር) ባቀረቡት ትችት የተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አጸፋ፣ “የታጠቁ ቡድኖችም ሁሉም አይደሉም ያልተሳተፉት” ሲሉ ተደምጠዋል።
የተሰወሱ የፋኖ ክንፎች ሁኔታም አንስተው፣ እነ ጃል ሰኒ ደግሞ በምክክሩ እንደተሳተፉ የገለጹ ሲሆን፣ “የቀሩት የሸኔ ክፋይ የተለዬ ሀሳብ አላቸው ብለን አናምንም” ብለዋል።
ተስፋዬ ዶ/ር)፣ ጉዳዩን እያጋጋልን ነው የቆየነው ወይስ ጉዳዩ ወደ መሀል እንዲመጣ አድርገን ለመፍትሄ እየሰራን? ሲሉም ፓርቲዎችን የተመለከተ ጥያቄ አቅርበዋል።
የሀገሪዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ በአማራ ክልል የተሳትፎ ልየታ እንዳደረገ፣ የቀሩት 8 ወረዳዎች ብቻ እንደሆኑ ምላሽ ሰጥተዋል።
በጫካ ስላሉ አካላት አጀንዳ አለመቅረብ በተመለከተ የቀረበውን ጥያቄ ሲመልሱም፣ “ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አላመጡም ብዬ አላስብም” ብለው፣ በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን፣ ጎንደር ያሉ ክላስተሮች የሕዝቡን ችግር እንዳስረዷቸው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔴 “ የአማራ ክልል ምሁራንና ሊህቃን በሰፊው እስር ቤት ነው ያሉት። አንድ ህዝብ ሊህቃን ታስሮበት ሊሳተፍ አይችልም ” - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ➡️ “ ጫካ ውስጥ ያሉ ሰዎች አጀንዳ አልመጣም ብዬ አላስብም ” - ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሦስት ዓመታት ሪፓርት ለፓርላማ ማቅረቡ፣ የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ/ም ሦስት አመቱን የሚደፍነው የኮሚሽኑ…
የኢትዮጵያ_ሀገራዊ_ምክክር_ኮሚሽን_የ_1.pdf
1.2 MB
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባቀረበው የሦስት ዓመታት ሪፓርት ቁጥሮች ምን አሉ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተመለከተው የኮሚሽኑ ሪፓርት መሠረት፦
-7,561 ወንዶች፣ 954 ሴቶች በድምሩ 8,515 አካላት ስልጠና ተሰጥተው ወደ ስራ በማስገባት የእቅዱን 80.2% ተፈጽሟል። ከ11 ክልሎችና በሁለት (2) የከተማ አስተዳደሮች መካከል ከፍተኛው የሴቶች ተሳትፎ 22.2% ከሀረሪ ክልል፣ ዝቅተኛው 4.4% ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆኖ ተመዝግቧል።
-በ11 ክልሎችና 2 የከተማ አስተዳደሮች የተሳታፊ ልየታ በማከናወን 87,615 ወንዶች፣ 37,080 ሴቶች፣ በድምሩ 124,695 የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በእቅድ ከተያዘው 164,580 አንጻር 75.6% የሸፈነ ሲሆን፣ የሴቶች ተሳትፎም 29.7 በመቶ ድርሻ አለው። የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ 5 በመቶ ነው።
-ከዲያስፓራው ማህበረሰብ አንድ የፊት ለፊት መድረክ፣ 5 የበይነ መረብ በጠቃላይ 6 ውይይቶችን ያደረገ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹም 894 እንደሆኑ ተመልክቷል።
-በ10 ክልሎችና በ2 ከተማ አስተዳደሮች የምክክር የአጀንዳ ልየታና ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎች ተጠናቀዋል። በዚህም 15,965 የወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች ለማሳተፍ ታቅዶ 15,204 በማሳተፍ 95.2% ተፈጽሟል።
-13,262 ባለድርሻ አካላትን (የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪዎዎች፣ መንግስት ተቋማት፣ ማኀበራትና ተቋማትና የወረዳ ተወካዮች) በዚሁ ረገድ ለማሳተፍ አቅዶ 10,439 በማሳተፍ 78.7% ተፈጽሟል።
-ከ10 ክልሎችና ሁለት (2) የከተማ አስተዳደሮች የወረዳ ማህበረሰብ ወክለው የየክልላቸውን አጀንዳ ልየታ ላይ የተሳተፉና በቀጣይ ሀገራዊ ምክክር ኮንፈሰንስ የሚሳተፉ 1,105 ተወካዮች የተመረጡ ሲሆን፣ በዚህም 501 ሴቶች ናቸው።
-የክልል የምክክርና ከጀንዳ ልየታ ባለድርሻ አካላት የተሳትፎ ደረጃን በተመለከተ፥ ከ1,260 በላይ የጥቃቅንና ንዑስ ቡድኖች፣ 109 የተጠቃለሉ የህብረተሰብ ክፍል፤ 55 የአጀንዳ ልየታ ቡድኖች በተናጠል፣ 11 የተጠቃለሉ የክልሎችና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አጀንዳ ሰነዶች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተግኝቷል።
-206 የዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ 436 የዩኒቨርሺቲ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች በክልል የአጀንዳ ወቅት በማስተባበር ተሳትፈዋል። 92 የዩኒቨርሲቲ መምህራን ለ4 ክልሎች በየቋንቋቸው ስልጠና እንዲሰጡ መደረጉ ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የኮሚሽኑ ሪፓርት ከዚህ በተጨማሪ የፋይናንስና ሌሎች ጉዳዮችን የያዙ ዳታዎችን አካቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በተመለከተው የኮሚሽኑ ሪፓርት መሠረት፦
-7,561 ወንዶች፣ 954 ሴቶች በድምሩ 8,515 አካላት ስልጠና ተሰጥተው ወደ ስራ በማስገባት የእቅዱን 80.2% ተፈጽሟል። ከ11 ክልሎችና በሁለት (2) የከተማ አስተዳደሮች መካከል ከፍተኛው የሴቶች ተሳትፎ 22.2% ከሀረሪ ክልል፣ ዝቅተኛው 4.4% ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሆኖ ተመዝግቧል።
-በ11 ክልሎችና 2 የከተማ አስተዳደሮች የተሳታፊ ልየታ በማከናወን 87,615 ወንዶች፣ 37,080 ሴቶች፣ በድምሩ 124,695 የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ በእቅድ ከተያዘው 164,580 አንጻር 75.6% የሸፈነ ሲሆን፣ የሴቶች ተሳትፎም 29.7 በመቶ ድርሻ አለው። የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ 5 በመቶ ነው።
-ከዲያስፓራው ማህበረሰብ አንድ የፊት ለፊት መድረክ፣ 5 የበይነ መረብ በጠቃላይ 6 ውይይቶችን ያደረገ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹም 894 እንደሆኑ ተመልክቷል።
-በ10 ክልሎችና በ2 ከተማ አስተዳደሮች የምክክር የአጀንዳ ልየታና ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ስራዎች ተጠናቀዋል። በዚህም 15,965 የወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች ለማሳተፍ ታቅዶ 15,204 በማሳተፍ 95.2% ተፈጽሟል።
-13,262 ባለድርሻ አካላትን (የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪዎዎች፣ መንግስት ተቋማት፣ ማኀበራትና ተቋማትና የወረዳ ተወካዮች) በዚሁ ረገድ ለማሳተፍ አቅዶ 10,439 በማሳተፍ 78.7% ተፈጽሟል።
-ከ10 ክልሎችና ሁለት (2) የከተማ አስተዳደሮች የወረዳ ማህበረሰብ ወክለው የየክልላቸውን አጀንዳ ልየታ ላይ የተሳተፉና በቀጣይ ሀገራዊ ምክክር ኮንፈሰንስ የሚሳተፉ 1,105 ተወካዮች የተመረጡ ሲሆን፣ በዚህም 501 ሴቶች ናቸው።
-የክልል የምክክርና ከጀንዳ ልየታ ባለድርሻ አካላት የተሳትፎ ደረጃን በተመለከተ፥ ከ1,260 በላይ የጥቃቅንና ንዑስ ቡድኖች፣ 109 የተጠቃለሉ የህብረተሰብ ክፍል፤ 55 የአጀንዳ ልየታ ቡድኖች በተናጠል፣ 11 የተጠቃለሉ የክልሎችና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አጀንዳ ሰነዶች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ተግኝቷል።
-206 የዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ 436 የዩኒቨርሺቲ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች በክልል የአጀንዳ ወቅት በማስተባበር ተሳትፈዋል። 92 የዩኒቨርሲቲ መምህራን ለ4 ክልሎች በየቋንቋቸው ስልጠና እንዲሰጡ መደረጉ ተመልክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የኮሚሽኑ ሪፓርት ከዚህ በተጨማሪ የፋይናንስና ሌሎች ጉዳዮችን የያዙ ዳታዎችን አካቷል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ትግራይ
🚨“ በአንድ አመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል” - በአይደር ሆስፒታል የዲያሌሲስ ዩኒት
➡️ “ ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው ” - የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር
በትግራይ ክልል ያሉ የኩላሊት ህሙማን ወገኖች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ የዲያሌሲስ ክትትል ለማድረግ በመቸገራቸው ለሞት መዳረጋቸውን የክልሉ ኩላሊት ህሙማን ማኀበርና አይደር ሆስፒታል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
በሆስፒታሉ የዲያሌሲስ ዩኒት አስተባባሪ አቶ ጥዑም መድኅን በሰጡን ቃል፣ “ ህሙማኑ ከውጪ ፋርማሲ ነው መድኃኒት የሚገዙት። ከመንግስት ፋርሚሲ አይገኝም ” ብለዋል።
አቶ ጥዑም መድኅን በዝርዝር ምን አሉ ?
“ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል። ብዙዎቹ የሚሞቱት የህክምና ክትትል ባለማድረጋቸው ነው። ክትትል የማያደርጉት ደግሞ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው ነው።
ችግሩ ብዙ ነው። በትግራይ ክልል ደረጃ አንድ የዲያሌሲስ ሴንተር ብቻ ነው ያለው በአይደር ሆስፒታል። ለዛውም መንግስት ምንም ድርሻ የለውም መድኃኒት አያቀርብም።
በ2013 ዓ/ም ጦርነት ከተጀመረ በኋላ በጣም ሰፊ ችግር ነው ያለው። በጦርነቱ ወቅትም ብዙ ሰዎች ናቸው የሞቱት። አሁንም የመድኃኒት እጥረት አለ ሰላም ቢሆንም።
መድኃኒት በትግራይ አይገኝም። ብዙ ጊዜ ከውጪ፣ በብላክ ማርኬት ከአዲስ አበባ ነው የሚገዙት። ዋጋውም ውድ ነው። ለአንድ እጥበት 3900 ብር ነው ከሌሎች መድኃኒቶች ወጪ ውጪ።
በሆስፒታሉ 44 ህሙማን አሉ ክትትል የሚያደርጉ። ከ44ቱ ወደ 4 የሚሆኑት ‘አንችልም’ ብለው አቁመዋል። 40ዎቹ አሉ።
ግን በሳምንት ሦስት ጊዜ ኩላሊታቸውን መታጠብ ቢኖርባቸውም የገንዘብ አቅም ስለሌላቸው በሳምንት አንድ ጊዜ፤ ሁለት ጊዜ፣ ቀሪ ስምነቱ ደግሞ የባሰ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው በሁለት ሳምንት ይታጠባሉ ” ብለዋል።
የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሐፍቶም አባዲ በበኩላቸው “ አርቲፊሻል ኪዲኒ ዲያላይዘርን ከ8 እስከ 10 ጊዜ ነው እያጠብን ነው ስንጠቀም የነበረው በጦርነቱ ጊዜ” ነው ያሉት።
“ በዚያ ምክንያት የፕሪቶሪያ ስምምነት እስከሚፈረም ድረስ በሁለት ዓመት ከ100 በላይ ህሙማን ሞተዋል። ከ100 በላይ የማኀበሩ ታካሚ ህሙማን ውስጥ 14 ሰዎች ብቻ ነበሩ በእድል የቀሩት ” ሲሉም አስታውሰዋል።
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አክለው ምን አሉ ?
“ አንድ ታካሚ ለአንድ ዲያሌሲስ ከ35,000 እስከ 40,000 ነው በወር የሚያወጣው ለዲያሌሲስ ብቻ። ለዚህም አቅም የለውም ሰው። ኮስቱ በጣም ከፍተኛ ነው።
ህክምናው የጀመሩ ህሙማንም አቅም ስለሌላቸው ትንሽ ተከታትለው አቋርጠው ነው የሚሄዱት። ዲያሌሲስ ካቋረጡ ደግሞ የሚጠብቃቸው ሞት ነው።
ከፕሪቶሪያ ስምምነቱ በኋላ ብዙ ሰዎች ሞተውብናል። ሦስት ጊዜ ማድረግ ሲጠበቅባቸው በገንዘብ እጦት በሳንምት አንድ ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርጉ አሉ። በዚሁ ምክንያት ብቻ እኔኳ የማውቃቸው ወደ 5፣ 6 ሰዎች ሞተዋል።
ኮስቱ እንዳለ ታካሚው ላይ ነው ያረፈው። ታካሚው ካለው ይከፍላል ከሌለው ያው የሚጠብቀው ሞት ነው። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ለዲያሌሲሱ ድጋፍ ያድርግልን።
ለምሳሌ ፦ እነ ጳውሎስ፣ እነ ሚኒሊክ ሆስፒታሎች ኮስታቸው በጣም ፌር ነው መንግስት ስለሚደግፋቸው።
እኛ ግን የግል ሆስፒታሎች ከሚከፍሉት በላይ ነው እየከፈልን ያለነው በመንግስት ሆስፒታል ላይ ሆነን። መንግስት መደገፍ ያለበትን ራሳችን ወጪ እያደረግን ነው የምናደርገው።
ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው። በመንግስት ሆስፒታሎች የሚገኙትን መድኃኒቶች መንግስት ያቅርብልን” ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሜኑ ጦርነት በፊት የመድኃኒት ድጋፍ ሲያደርግላቸው የነበረው ሱዳናዊ ድርጅት በጦርቱ ሳቢያ ውሉና ድጋፉ እንደተቋረጠ፣ ከሁለት አመታት በላይ የህክምና የሚደረገው ከህሙማኑ በሚሰባሰብ ገንዘብ መሆኑን ማኀበሩና ሆስፒታሉ አስረድተዋል።
እስከ ጥር 2017 ዓ/ም መጀመሪያ ድረስ መድኃኒት የሚገዛው ከህሙማኑ በሚዋጣ ገንዘብ እንደነበር፣ አሁን አንድ መድኃኒት አቅራቢ ድርጅት ውል ገብቶ በሆፒታሉ በኩል የመድኃኒት አቅርቦት እንደጀመረ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🚨“ በአንድ አመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል” - በአይደር ሆስፒታል የዲያሌሲስ ዩኒት
➡️ “ ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው ” - የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር
በትግራይ ክልል ያሉ የኩላሊት ህሙማን ወገኖች በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ የዲያሌሲስ ክትትል ለማድረግ በመቸገራቸው ለሞት መዳረጋቸውን የክልሉ ኩላሊት ህሙማን ማኀበርና አይደር ሆስፒታል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
በሆስፒታሉ የዲያሌሲስ ዩኒት አስተባባሪ አቶ ጥዑም መድኅን በሰጡን ቃል፣ “ ህሙማኑ ከውጪ ፋርማሲ ነው መድኃኒት የሚገዙት። ከመንግስት ፋርሚሲ አይገኝም ” ብለዋል።
አቶ ጥዑም መድኅን በዝርዝር ምን አሉ ?
“ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ40 በላይ ሰዎች ሞተዋል። ብዙዎቹ የሚሞቱት የህክምና ክትትል ባለማድረጋቸው ነው። ክትትል የማያደርጉት ደግሞ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው ነው።
ችግሩ ብዙ ነው። በትግራይ ክልል ደረጃ አንድ የዲያሌሲስ ሴንተር ብቻ ነው ያለው በአይደር ሆስፒታል። ለዛውም መንግስት ምንም ድርሻ የለውም መድኃኒት አያቀርብም።
በ2013 ዓ/ም ጦርነት ከተጀመረ በኋላ በጣም ሰፊ ችግር ነው ያለው። በጦርነቱ ወቅትም ብዙ ሰዎች ናቸው የሞቱት። አሁንም የመድኃኒት እጥረት አለ ሰላም ቢሆንም።
መድኃኒት በትግራይ አይገኝም። ብዙ ጊዜ ከውጪ፣ በብላክ ማርኬት ከአዲስ አበባ ነው የሚገዙት። ዋጋውም ውድ ነው። ለአንድ እጥበት 3900 ብር ነው ከሌሎች መድኃኒቶች ወጪ ውጪ።
በሆስፒታሉ 44 ህሙማን አሉ ክትትል የሚያደርጉ። ከ44ቱ ወደ 4 የሚሆኑት ‘አንችልም’ ብለው አቁመዋል። 40ዎቹ አሉ።
ግን በሳምንት ሦስት ጊዜ ኩላሊታቸውን መታጠብ ቢኖርባቸውም የገንዘብ አቅም ስለሌላቸው በሳምንት አንድ ጊዜ፤ ሁለት ጊዜ፣ ቀሪ ስምነቱ ደግሞ የባሰ የገንዘብ እጥረት ስላለባቸው በሁለት ሳምንት ይታጠባሉ ” ብለዋል።
የትግራይ ክልል ኩላሊት ህሙማን ማኀበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ሐፍቶም አባዲ በበኩላቸው “ አርቲፊሻል ኪዲኒ ዲያላይዘርን ከ8 እስከ 10 ጊዜ ነው እያጠብን ነው ስንጠቀም የነበረው በጦርነቱ ጊዜ” ነው ያሉት።
“ በዚያ ምክንያት የፕሪቶሪያ ስምምነት እስከሚፈረም ድረስ በሁለት ዓመት ከ100 በላይ ህሙማን ሞተዋል። ከ100 በላይ የማኀበሩ ታካሚ ህሙማን ውስጥ 14 ሰዎች ብቻ ነበሩ በእድል የቀሩት ” ሲሉም አስታውሰዋል።
የማኀበሩ ሥራ አስኪያጅ አክለው ምን አሉ ?
“ አንድ ታካሚ ለአንድ ዲያሌሲስ ከ35,000 እስከ 40,000 ነው በወር የሚያወጣው ለዲያሌሲስ ብቻ። ለዚህም አቅም የለውም ሰው። ኮስቱ በጣም ከፍተኛ ነው።
ህክምናው የጀመሩ ህሙማንም አቅም ስለሌላቸው ትንሽ ተከታትለው አቋርጠው ነው የሚሄዱት። ዲያሌሲስ ካቋረጡ ደግሞ የሚጠብቃቸው ሞት ነው።
ከፕሪቶሪያ ስምምነቱ በኋላ ብዙ ሰዎች ሞተውብናል። ሦስት ጊዜ ማድረግ ሲጠበቅባቸው በገንዘብ እጦት በሳንምት አንድ ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርጉ አሉ። በዚሁ ምክንያት ብቻ እኔኳ የማውቃቸው ወደ 5፣ 6 ሰዎች ሞተዋል።
ኮስቱ እንዳለ ታካሚው ላይ ነው ያረፈው። ታካሚው ካለው ይከፍላል ከሌለው ያው የሚጠብቀው ሞት ነው። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ለዲያሌሲሱ ድጋፍ ያድርግልን።
ለምሳሌ ፦ እነ ጳውሎስ፣ እነ ሚኒሊክ ሆስፒታሎች ኮስታቸው በጣም ፌር ነው መንግስት ስለሚደግፋቸው።
እኛ ግን የግል ሆስፒታሎች ከሚከፍሉት በላይ ነው እየከፈልን ያለነው በመንግስት ሆስፒታል ላይ ሆነን። መንግስት መደገፍ ያለበትን ራሳችን ወጪ እያደረግን ነው የምናደርገው።
ጳውሎስ ሆስፒታል 400 ብር የሚሸጠውን መድኃኒት እኛ 1200 ብር ነው የምንገዛው። በመንግስት ሆስፒታሎች የሚገኙትን መድኃኒቶች መንግስት ያቅርብልን” ሲሉ ተናግረዋል።
ከሰሜኑ ጦርነት በፊት የመድኃኒት ድጋፍ ሲያደርግላቸው የነበረው ሱዳናዊ ድርጅት በጦርቱ ሳቢያ ውሉና ድጋፉ እንደተቋረጠ፣ ከሁለት አመታት በላይ የህክምና የሚደረገው ከህሙማኑ በሚሰባሰብ ገንዘብ መሆኑን ማኀበሩና ሆስፒታሉ አስረድተዋል።
እስከ ጥር 2017 ዓ/ም መጀመሪያ ድረስ መድኃኒት የሚገዛው ከህሙማኑ በሚዋጣ ገንዘብ እንደነበር፣ አሁን አንድ መድኃኒት አቅራቢ ድርጅት ውል ገብቶ በሆፒታሉ በኩል የመድኃኒት አቅርቦት እንደጀመረ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” - ምክትል ኮሚሽነር ሒሩት ገብረ ሥላሴ
ከቀናት በፊት አንድ አመት ተጨማሪ የሥራ ጊዜ በፓርላማ የተሰጠው የ3 አመታት የሥራ ዘመኑን ነገ ይጠናቅቅ የነበረው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ3 አመታት ክንውንና የቀጣይ አቅጣጫውን በተመለከተ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህም ኮሚሽኑ የተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በቂ ነው? አጠቃላይ ሥራውስ መቼ ይጠናቀቃል? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረላቸው ጥያቄ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ፣ “ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
"ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ” ያሉት፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን ይበሉ እንጂ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆኑ ነገሮችን በዝርዝር አልገለጹም።
11 ኮሚሽነሮች እንዳሉና ሥራውን ተባብሮ ለመስራት እንደሚቻል ገልጸው፣ "ተጨማሪ አንዳንድ ሥራዎችን የሚያቃልሉ ነገሮች በመንግስትም ሆነ በሌሎች ከተፈጠሩልን ስራችንን ያጣድፋል" ብለዋል።
“ምክክር በዚህ ሰዓት ውስጥ ተመካክራችሁ በዚህ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ስጡ የሚባልበት አይደለም። ህዝቦች ቁጭ ብለው ጊዜ ውስደው ተመካክረው የሚወሰኑት ሂደት ስለሆነ በቀላሉ የሚወሰኑ አጀንዳዎች ይኖራሉ። ጊዜ የሚፈጁም ሊኖሩ ይችላሉ” ሲሉም አስረድተዋል።
አክለው፣ “በዚህ ምክንያት በትክክል በዚህ ጊዜ ውስጥ ያልቃል ለማለት ያስቸግራል” ብለው፣ ሆኖም ግን ኮሚሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለመጨረስ ጥረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የተወሰኑ ፓርቲዎች ባልተሳተፉበት የምክክሩ ሂደቱ ሙሉ ይሆናል? በሚል ለቀረበው ጥያቄም፣ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን ገልጸው፣ “ዳተኛ ሆነው” ያልገቡት እንዲገቡ ደግሞ ንግግር እንደተደረገ፣ አሁንም ጥረቱ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ በመግለጫው ባደረጉት ንግግር በሕጋዊ ከተመዘገቡ ወደ 70 ፓርቲዎች 57 የሚሆኑት ከኮሚሽኑ ጋር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ከታጣቂዎች ጋር ንግግር ተደርጎ እንደሆን ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ማብራሪያ ዋና ኮሚሽነሩ፣ የፋኖ ታጣቂዎችን እንዳነጋገሩ፣ “ሊከፋፍለን ነው” በሚል ስማቸው እንደሚነሳ አስታውሰው ተከታዩን ብለዋል።
ምን አሉ?
“ሀገራዊ ምክክሩ ማንንም መከፋፈል አይመኝም። የሚመኘው፣ መደረግ አለበት ብሎ የሚያምነውም ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ነው።
እኔ ፋኖ መሆናቸውን አላውቅም አንድ ታጣቂ ቡድን ራሳቸው ደውለውልኝ ‘የምክክር ኮሚሽኑን ሥራ ተገንዝበናል። ‘በዚህ መሠረት ወደ ትግሉ የገባንበትን አጀንዳ ወደ እናንተ አምጥተን ወደ ውይይት የሚቀርብ ከሆነ መሳሪያችንን ለማስቀመጥ ዝግጁ ነን’ የሚል በቀጥታ በግሌ አቅርበውልኛል። ይሄን ሰው በተደጋጋሚ አግኝተዋለሁ።
እዛ ላሉትም የደኅንነት፣ አካላት በስልክ አግኝቼ እነዚህ ሰዎች በአግባቡ መሠረት ሰላማዊ ጥበቃ ተደርጎላቸው አጀንዳቸውን የሚያመጡበት መንገድ እንዲመቻች ይሄን አስተላልፌያለሁ።
ይህን ሳደርግ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በማሳወቅ ነው። እንጂ የፋኖ ናቸው ብዬ የተናገርኩት አንድም የለም” ብለዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው መግለጫ የኮሚሽኑ የ3 አመታት ክንውኖች በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን፣ ይህንኑ ሪፓርት ከቀናት በፊት አድርሰናችሁ ነበር።
(ተጨማሪ ዘገባ በቀጣይ የምናቀርብ ይህናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከቀናት በፊት አንድ አመት ተጨማሪ የሥራ ጊዜ በፓርላማ የተሰጠው የ3 አመታት የሥራ ዘመኑን ነገ ይጠናቅቅ የነበረው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የ3 አመታት ክንውንና የቀጣይ አቅጣጫውን በተመለከተ ዛሬ በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ ሰጥቷል።
በዚህም ኮሚሽኑ የተሰጠው ተጨማሪ ጊዜ በቂ ነው? አጠቃላይ ሥራውስ መቼ ይጠናቀቃል? በሚል ከጋዜጠኞች ለቀረላቸው ጥያቄ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ ስላሴ፣ “ብዙ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች ይኖራሉ። ነገር ግን ሁሉም ነገር በትክክል ከተካሄደ ሊበቃን ይችላል” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
"ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ” ያሉት፣ ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ ይህን ይበሉ እንጂ ከቁጥጥር ውጪ ስለሆኑ ነገሮችን በዝርዝር አልገለጹም።
11 ኮሚሽነሮች እንዳሉና ሥራውን ተባብሮ ለመስራት እንደሚቻል ገልጸው፣ "ተጨማሪ አንዳንድ ሥራዎችን የሚያቃልሉ ነገሮች በመንግስትም ሆነ በሌሎች ከተፈጠሩልን ስራችንን ያጣድፋል" ብለዋል።
“ምክክር በዚህ ሰዓት ውስጥ ተመካክራችሁ በዚህ ጊዜ ውስጥ ውሳኔ ስጡ የሚባልበት አይደለም። ህዝቦች ቁጭ ብለው ጊዜ ውስደው ተመካክረው የሚወሰኑት ሂደት ስለሆነ በቀላሉ የሚወሰኑ አጀንዳዎች ይኖራሉ። ጊዜ የሚፈጁም ሊኖሩ ይችላሉ” ሲሉም አስረድተዋል።
አክለው፣ “በዚህ ምክንያት በትክክል በዚህ ጊዜ ውስጥ ያልቃል ለማለት ያስቸግራል” ብለው፣ ሆኖም ግን ኮሚሽኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን ለመጨረስ ጥረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የተወሰኑ ፓርቲዎች ባልተሳተፉበት የምክክሩ ሂደቱ ሙሉ ይሆናል? በሚል ለቀረበው ጥያቄም፣ ፓርቲዎች በምክክሩ እንዲሳተፉ ጥረት መደረጉን ገልጸው፣ “ዳተኛ ሆነው” ያልገቡት እንዲገቡ ደግሞ ንግግር እንደተደረገ፣ አሁንም ጥረቱ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።
ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በበኩላቸው፣ በመግለጫው ባደረጉት ንግግር በሕጋዊ ከተመዘገቡ ወደ 70 ፓርቲዎች 57 የሚሆኑት ከኮሚሽኑ ጋር እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ከታጣቂዎች ጋር ንግግር ተደርጎ እንደሆን ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ማብራሪያ ዋና ኮሚሽነሩ፣ የፋኖ ታጣቂዎችን እንዳነጋገሩ፣ “ሊከፋፍለን ነው” በሚል ስማቸው እንደሚነሳ አስታውሰው ተከታዩን ብለዋል።
ምን አሉ?
“ሀገራዊ ምክክሩ ማንንም መከፋፈል አይመኝም። የሚመኘው፣ መደረግ አለበት ብሎ የሚያምነውም ሁሉም ተሳታፊ እንዲሆን ነው።
እኔ ፋኖ መሆናቸውን አላውቅም አንድ ታጣቂ ቡድን ራሳቸው ደውለውልኝ ‘የምክክር ኮሚሽኑን ሥራ ተገንዝበናል። ‘በዚህ መሠረት ወደ ትግሉ የገባንበትን አጀንዳ ወደ እናንተ አምጥተን ወደ ውይይት የሚቀርብ ከሆነ መሳሪያችንን ለማስቀመጥ ዝግጁ ነን’ የሚል በቀጥታ በግሌ አቅርበውልኛል። ይሄን ሰው በተደጋጋሚ አግኝተዋለሁ።
እዛ ላሉትም የደኅንነት፣ አካላት በስልክ አግኝቼ እነዚህ ሰዎች በአግባቡ መሠረት ሰላማዊ ጥበቃ ተደርጎላቸው አጀንዳቸውን የሚያመጡበት መንገድ እንዲመቻች ይሄን አስተላልፌያለሁ።
ይህን ሳደርግ ለሀገራዊ ምክክር ጉባዔ በማሳወቅ ነው። እንጂ የፋኖ ናቸው ብዬ የተናገርኩት አንድም የለም” ብለዋል።
በሌላ በኩል በዛሬው መግለጫ የኮሚሽኑ የ3 አመታት ክንውኖች በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር) በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን፣ ይህንኑ ሪፓርት ከቀናት በፊት አድርሰናችሁ ነበር።
(ተጨማሪ ዘገባ በቀጣይ የምናቀርብ ይህናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba 🚨" ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ1 ሚሊየን 293 ሺህ በላይ አሽከርካሪዎች በትራፊክ ፖሊስ አባላት ብቻ ተቀጥተዋል !! " እንደ ሸገር ሬድዮ ዘገባ ፥ በአዲስ አበባ በየቀኑ በአማካይ 7,183 አሽከርካሪዎች በትራፊክ ደንብ መተላለፍ በትራፊክ ፖሊስ ብቻ ይቀጣሉ። ይህ በሌሎች የትራፊክ ደንብ ታላፊዎችን የሚቀጡትን አይጨምርም። ባለፉት በ6 ወራት ውስጥ በተለያዩ የደምብ መተላለፍ…
" አንዳንዴ ቀን ሙሉ የሰራነውን ገንዘብ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን ! " - አሽከርካሪዎች
በአዲስ አበባ በርካታ አሸከርካሪዎች ከትራፊክ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ ወቀሳ እና ቅሬታ ያቀርባሉ።
ለአብነትም ፤ አንዳንድ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ያለ አንዳች ምክንያት እየሄደ ያለን ተሽከርካሪ ማስቆም ፤ ጥፋት ሲያጡ ጥፋት ወደ መፈለግ መግባት ከዛ የቅጣት ወረቀት ላይ መፃፍ ስራቸው ያደረጉ አሉ።
ከዚህ ባለፈ ለዜጎች ክብርን ያለመስጠት ፤ ዝቅ ብሎ አለማገልገል፣ አሽከርካሪዎችን መናቅ ፣ ምንም የምታመጡት ነገር የለም ማለት፣ በስርዓት አለማናገር፣ ጥፋትን አለማስረዳት ... የመሳሰሉ ባህሪዎችም ይታይባቸዋል።
አንዳንድ ትራፊክ ፖሊስ አባላት የትራፊክ ሁኔታውን ማሳለጥ ሲገባቸው እንቅፋትም ይሆናሉ።
መሃል መንገድ ላይ፣ አደባባይ ላይ ሳይቀር የትራፊክ እንቅስቃሴን በሚያውክ መልኩ ተሽከርካሪ አስቁመው መንገድ እንዲዘጋጋም ያደርጋላ።
በተለያየ ጊዜ ቃላቸውን አሽከርካሪዎች ቁጥጥር መኖሩን ግዴታ ቢሆንም በአግባቡ እና በስርዓት መሄን እንዳሚገባው ያነሳሉ።
" ቅጣቱ ለተላለፈ ደንብ መቅጫ ሳይሆን ከዜጎች ገንዘብ መሰብሰቢያ ሆኗል " የሚሉት የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች " ቀን ሙሉ የሰራነውን አንዳንዴ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን " ብለዋል።
" በተለይ የቅጣት ብሩ ከጨመረ ወዲህ በሆነው ባልሆነው መኪና እያስቆሙ መቅጣት ተበራክቷል " ሲሉም ገልጸዋል።
በተላይ አዳዲስ በተሰሩ የመንገድ ዳሮች ማቆም ስላማይቻል ስራቸውን ለመስራት እንደተቸገሩ ሆኖ ሳለ ያለ አግባብ በትራፊክ ፖሊስ እና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚጣለው ቅጣት ቀን ሙሉ ለፍተው ማታ ባዶ እጃቸውን ወደ ቤት እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑን አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በርካታ አሸከርካሪዎች ከትራፊክ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ ወቀሳ እና ቅሬታ ያቀርባሉ።
ለአብነትም ፤ አንዳንድ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ያለ አንዳች ምክንያት እየሄደ ያለን ተሽከርካሪ ማስቆም ፤ ጥፋት ሲያጡ ጥፋት ወደ መፈለግ መግባት ከዛ የቅጣት ወረቀት ላይ መፃፍ ስራቸው ያደረጉ አሉ።
ከዚህ ባለፈ ለዜጎች ክብርን ያለመስጠት ፤ ዝቅ ብሎ አለማገልገል፣ አሽከርካሪዎችን መናቅ ፣ ምንም የምታመጡት ነገር የለም ማለት፣ በስርዓት አለማናገር፣ ጥፋትን አለማስረዳት ... የመሳሰሉ ባህሪዎችም ይታይባቸዋል።
አንዳንድ ትራፊክ ፖሊስ አባላት የትራፊክ ሁኔታውን ማሳለጥ ሲገባቸው እንቅፋትም ይሆናሉ።
መሃል መንገድ ላይ፣ አደባባይ ላይ ሳይቀር የትራፊክ እንቅስቃሴን በሚያውክ መልኩ ተሽከርካሪ አስቁመው መንገድ እንዲዘጋጋም ያደርጋላ።
በተለያየ ጊዜ ቃላቸውን አሽከርካሪዎች ቁጥጥር መኖሩን ግዴታ ቢሆንም በአግባቡ እና በስርዓት መሄን እንዳሚገባው ያነሳሉ።
" ቅጣቱ ለተላለፈ ደንብ መቅጫ ሳይሆን ከዜጎች ገንዘብ መሰብሰቢያ ሆኗል " የሚሉት የሜትር ታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ አሽከርካሪዎች " ቀን ሙሉ የሰራነውን አንዳንዴ ያለ አንዳች ጥፋት ተቀጥተን ባዶ እጃችንን ቤታችን እንገባለን " ብለዋል።
" በተለይ የቅጣት ብሩ ከጨመረ ወዲህ በሆነው ባልሆነው መኪና እያስቆሙ መቅጣት ተበራክቷል " ሲሉም ገልጸዋል።
በተላይ አዳዲስ በተሰሩ የመንገድ ዳሮች ማቆም ስላማይቻል ስራቸውን ለመስራት እንደተቸገሩ ሆኖ ሳለ ያለ አግባብ በትራፊክ ፖሊስ እና የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚጣለው ቅጣት ቀን ሙሉ ለፍተው ማታ ባዶ እጃቸውን ወደ ቤት እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑን አመልክተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ
🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች
➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።
የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።
በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።
አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።
የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?
“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡
እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡
በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።
ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።
ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።
እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።
አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡
እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።
“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡
(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች
➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።
የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።
በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።
አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።
የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?
“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡
እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡
በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።
ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።
ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።
እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።
አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡
እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።
“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡
(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአደጋ_ደህንነት_ደንብ_ቁ_132_2014_የጸደቀ_250222_210150.pdf
327.8 KB
“ ማንኛውም ሰው በተቋሙ ውስጥ አስፈላጊ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶች ካላሟላ ከ10 ሺሕ ያላነሰ ከ100 ሺሕ ያልበለጠ ቅጣት ይጣልበታል ” - ኮሚሽኑ
የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ አካላት የገንዘብና የሥራ ፈቃድን እስከማሳገድ ቅጣትን የሚደነግግ ደንብ ማውጣቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና ስጋት ሥራ አመራር አስታወቀ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደንቡ፣ “ማንኛውም ሰው በተቋሙ አስፈላጊ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶች ሳያሟላ የቀረ እንደሆነ እንደ ደረጃው ከ10 ሺሕ ያላነሰና ከ100 ሺሕ ያልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ይጣልበታል” ይላል።
በኮሚሽኑ ደንብ መሠረት፦
ደንቡ፣ የህንፃዎችና የግንባታዎች ዲዛይን፣ ስለህንፃ፣ ግንባታና የግንባታ ሂደት መሟላት ያለባቸው የአደጋ ስጋት ደኅንነት መስፈርቶችንና የህንፃ አጠቃቀምን የተመለከቱ ግዴታዎችን አካቶ ይዟል።
የህንፃዎች ዲዛይን የሌሎች ሰዎችን ንብረቶች ለአደጋ በሚያጋልጥ መልኩ መሆን እንደሌለባቸው፣ በዲዛይኑ የእሳትና ሌሎች አደጋዎችን መከላከያና መቆጣጠሪያ መስፈርቶች መሟላት እንዳለባቸውም ደንቡ ያትታል።
ነባር ህንፃዎች ጥገና ወይም ለውጥ በሚደረግባቸው ጊዜ አደጋን ለመቆጣጠር/ለመከላከል የተገጠሙ ሲስተሞች ስለመሟላታቸው ፍተሻ ተደርጎ የአደጋ ደኅንነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መውሰድ ግዴታ መሆኑ ተመልክቷል።
በግንባታ ሂደት ያለ ህንፃ ሲጠናቀቅ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለሚያዙ ክፍሎች አስፈላጊ የደኅንነት ተግባራት መሟላታቸው ካልተረጋገጠ ለተጠቃሚዎች መተላለፍ እንደማይችልም በድንጋጌው ተጠቅሷል።
ህንፃ ተከራዮች አደጋን አስቀድሞ ለመከላከል ወይም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአደጋ ደኀንነት መስፈርቶችን እንዲያሟሉ፣ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ያላሟላ ነባር ህንፃ ባለቤት ለማሟላት የሚጠበቅበትን የማድረግ ግዴታ እንዳለበት በደንቡ ተገልጿል።
“ማንኛውም የጅምር ህንፃ ተጠቃሚ ከሚመለከተው አካል የመጠቀሚያ ፈቃድ መያዝ ይኖርበታል”ም ብሏል ደንቡ።
በተጨማሪም፣ አደገኛ ንጥረ ነገሮች የሚያከማቹ የሚያጎጉዙ፣ የሚጠቀሙ የደኀንነት የደኅንነት ብቃት ማረጋገጫ ሊኖራቸው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ የተከማቹ አደገኛ ንጥረ ነገሮችን እንደሚያስወግድ አትቷል።
እንዲሁም የተከለከሉ ድርጊቶችን ዝርዝር ያስቀመጠው ደንቡ የንግድ/የሥራ ፈቃድ እስከማሳገድ የሚደርስ እርምጃ እንደሚያስወስድ ገልጾ፣ እርምጃ አወሳሰድና አስተዳደራዊ ቅጣት ዝርዝር ድንጋጌዎችን ደንቡ አስቀምጧል።
ኮሚሽኑ ይህንኑ ደንብና ለማህበረሰቡ ሊቀርብ ስለሚገባ ግንዛቤ በተመለከተ ከሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ ትላንት በሳሬም ሆቴል ያካሄደ ሲሆን፣ ተጨማሪ ይኖረናል።
(ሙሉ ድንጋጌ የያዘው ደንቡ ከላይ ተያይዟል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ባላሟሉ አካላት የገንዘብና የሥራ ፈቃድን እስከማሳገድ ቅጣትን የሚደነግግ ደንብ ማውጣቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና ስጋት ሥራ አመራር አስታወቀ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው ደንቡ፣ “ማንኛውም ሰው በተቋሙ አስፈላጊ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶች ሳያሟላ የቀረ እንደሆነ እንደ ደረጃው ከ10 ሺሕ ያላነሰና ከ100 ሺሕ ያልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ይጣልበታል” ይላል።
በኮሚሽኑ ደንብ መሠረት፦
ደንቡ፣ የህንፃዎችና የግንባታዎች ዲዛይን፣ ስለህንፃ፣ ግንባታና የግንባታ ሂደት መሟላት ያለባቸው የአደጋ ስጋት ደኅንነት መስፈርቶችንና የህንፃ አጠቃቀምን የተመለከቱ ግዴታዎችን አካቶ ይዟል።
የህንፃዎች ዲዛይን የሌሎች ሰዎችን ንብረቶች ለአደጋ በሚያጋልጥ መልኩ መሆን እንደሌለባቸው፣ በዲዛይኑ የእሳትና ሌሎች አደጋዎችን መከላከያና መቆጣጠሪያ መስፈርቶች መሟላት እንዳለባቸውም ደንቡ ያትታል።
ነባር ህንፃዎች ጥገና ወይም ለውጥ በሚደረግባቸው ጊዜ አደጋን ለመቆጣጠር/ለመከላከል የተገጠሙ ሲስተሞች ስለመሟላታቸው ፍተሻ ተደርጎ የአደጋ ደኅንነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት መውሰድ ግዴታ መሆኑ ተመልክቷል።
በግንባታ ሂደት ያለ ህንፃ ሲጠናቀቅ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ለሚያዙ ክፍሎች አስፈላጊ የደኅንነት ተግባራት መሟላታቸው ካልተረጋገጠ ለተጠቃሚዎች መተላለፍ እንደማይችልም በድንጋጌው ተጠቅሷል።
ህንፃ ተከራዮች አደጋን አስቀድሞ ለመከላከል ወይም ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የአደጋ ደኀንነት መስፈርቶችን እንዲያሟሉ፣ የአደጋ ደኅንነት መስፈርቶችን ያላሟላ ነባር ህንፃ ባለቤት ለማሟላት የሚጠበቅበትን የማድረግ ግዴታ እንዳለበት በደንቡ ተገልጿል።
“ማንኛውም የጅምር ህንፃ ተጠቃሚ ከሚመለከተው አካል የመጠቀሚያ ፈቃድ መያዝ ይኖርበታል”ም ብሏል ደንቡ።
በተጨማሪም፣ አደገኛ ንጥረ ነገሮች የሚያከማቹ የሚያጎጉዙ፣ የሚጠቀሙ የደኀንነት የደኅንነት ብቃት ማረጋገጫ ሊኖራቸው እንደሚገባ፣ ኮሚሽኑ የተከማቹ አደገኛ ንጥረ ነገሮችን እንደሚያስወግድ አትቷል።
እንዲሁም የተከለከሉ ድርጊቶችን ዝርዝር ያስቀመጠው ደንቡ የንግድ/የሥራ ፈቃድ እስከማሳገድ የሚደርስ እርምጃ እንደሚያስወስድ ገልጾ፣ እርምጃ አወሳሰድና አስተዳደራዊ ቅጣት ዝርዝር ድንጋጌዎችን ደንቡ አስቀምጧል።
ኮሚሽኑ ይህንኑ ደንብና ለማህበረሰቡ ሊቀርብ ስለሚገባ ግንዛቤ በተመለከተ ከሚዲያ ተቋማት የምክክር መድረክ ትላንት በሳሬም ሆቴል ያካሄደ ሲሆን፣ ተጨማሪ ይኖረናል።
(ሙሉ ድንጋጌ የያዘው ደንቡ ከላይ ተያይዟል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ከ3,000 ወጣቶች ወደ 130 የሚሆኑት ወጡ ተብሎ ዝም የሚባል ከሆነ ለቀሪዎቹ አደጋ ነው " - የወላጆች ኮሚቴ ሰርተው ለመለወጥ በሚል ከኢትዮጵያ የተሰደዱ ዜጎች በማይናማር በአጋቾች የከፋ ስቃይ እያሳለፉ በመሆኑ መንግስት ከስቃይ እንዲታደጋቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ አይዘነጋም። የወላጆች ኮሚቴ፣ ኢትዮጵያዊያኑ በታገቱበት የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው፣ አጋቾች ልጆቹን ዶላር ማጭበርበር…
#Update
🔴 “ መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ ከእገታው የወጡት ኢትዮጵያዊያንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል ” - ቤተሰብ
🔵 “ እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም? ” - ኢትዮጵያዊ በታይላንድ
➡️ “ ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው ” - የወላጆች ኮሚቴ
ሰርተው ለመለወጥ ሲሉ ተታለው ወደ ታይላንድ የተሰደዱና በታጣቂዎች በማይናማር ታግተው ቆይተው የወጡና አሁንም በእገታ ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስት እንዲደርስላቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል።
በሺዎች ከሚቆጠሩት ኢትዮጵያዊያን ታጋቾች ውስጥ 13ዐ የሚሆኑት ከሳምንታት በፊት ከእገታ እንደተለቀቁ፣ ሌሎች በርካቶች ደግሞ ገና ከእገታው እንዳልወጡ፣ የወጡትም ሆኑ ያልወጡት የመንግስትን ድጋፍ እየተጠባበቁ መሆኑን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።
በታይላንድ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ አሁንስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ ከመግደል ያላነሰ ድብድባ ነው የሚካሄደውኮ። እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታይላንድ በረራ እንዳለው እያየን ነው። እሺ ገበያውም አይዘጋበት ቢያንስ ሰው ይዞ ወደ ታይላንድ መጥቶ ሲመለስ የተወሰኑ ሰዎችን እየቀላቀለ ቢመልሰን ማቃለል አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኛ አይደለም እንዴ ? ለሥራ ብለን ነው የመጣነዎኮ ስለተቸገርን ገንዘብ ለማግኘት። ገንዘብ ይዘን ደግሞ ወደ ሀገራችን ለመመለስ።
‘መንግስት አላችሁ?’ ተብለን እስከምንጠየቅ መድረሳችን በጣም ያሳፍራል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሌላ አገር ‘ገንዘብ ረዳሁ’ ብሎ ከሚያወራ እዚህ ያሉትን ዜጓቹን አያስወጣም እንዴ ?
እኛስ መቼም ምግብ ባይቀርብልም ከነበርንበት ሁኔታ አንጻር ምንም አይመስለንም። ትኩረት የሚሹት በማይናማር ከእገታ ያልወጡት እኛ ባለን መረጃ ብቻ እንኳ ከ400 በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያዊያን ነው። እነርሱ የሚወጡት ደግሞ እኛ ቦታውን ስንለቅላቸው ነው።
እኛ ማይናማር ቦርደር ላይ ነው ያለነው። ሞኤ የሚባል ወንዝ እንደተሻገን። በጣም ሐበሻዎች አሉ። ከአንድ ካምፓኒ ብቻ እስከ 500 የሚደርሱ ሐበሻዎች አሉ።
አብዛኛው ኢትዮጵያ ያለበት አንዱ ካምፓኒ ‘ወደ ሌላ ቦታ እንስዳችኋለሁ’ እያለን ነው። ሌላ ቦታ የሚወስደን ሁሉንም ነገሮች ቁጥጥሩ ለማድረግ ነው። አሁን ያለንበት ቦታ ላይ ደኀንነታችን የተጠበቀ ነው።
ማይናማር ግን ብዙ ሰው እየተጎዳ፣ እየተሰቃዬ ያለበት ፎረይን ፓሊሶች የሌሉበት አካባቢ ነው። ያለንበትን ካምፓኒ አቋርጠን ለመውጣት 2,500 ዶላር ይከፈላል። ያለንበት ግቢ እስከ 25 ካምፓኒዎች አሉ። ወደ ሌላ ግቢ ላለመሄድ ነው ጥረት እያደረግን ያለነው።
ሐበሾችን እየጠበቅን ነው ገና ከእገታ ያልወጡ ስላሉ። አመት ድረስ የቆዩ አሉ። በራሳችን ፈቃድ ስለማያስወጡን።
እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ ያልመጣንበት ዋነኛው ምክንያት ሙሉ ወጪ መሸፈን ስላማይችል ነው።
ምክንያቱም ወደ ኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልከው ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኙ ነው መረጃ የሰጡን። የታይላንድ መንግስት ለኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልኳል። ግን እስከ ሳምንት ምላሽ አልተሰጠም።
ካለንበት ካምፕ ወጥተን ወደ ታይላንድ/ሜኢሶት ኤርፓርት ነው መሄድ ያለብን። ከታይላንድ መንግስት ጋር በመነጋገር ወንዝ ያሻግሩናል። ፓስፓርት የሌለው አንድ ወር መቆየት እንደሚችል ነው የተነገረው።
የተጎዱ ሀበሿች፣ ጀርባቸው ላይ ለምጥ ያለ፣ የታመሙ፣ የተደበደቡ በሙሉ ካምፕ ነው ያሉት። እኛን ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ነው ያልጠየቁን እንጂ ህንዶችን፣ ቻይናዎችን ‘አለንላችሁ’ የሚሉ አሉ።
ምን እያደረጉ እንደሆነ የምናውቀው ነገር የለም። የምናውቀው ዘገባ እያደረጉና ዜግነታችንን ለይተው ብዙ ነገር እየጠየቁ እንደሆነ ነው።
የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው የቀሩት። ከኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ ስላላገኙ። ምላሽ ቢያገኙ ይወጡ ነበር የሚቆዩበት ምክንያት የለም። ለኛም ስጋት የሆነው እነርሱ ባለመሄዳቸው የተነሳ ምናልባት የታይላንድ መንግስት ላይቀበለን ይችላል ” ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያዊያኑ ቤተሰቦችስ በሰጡን ቃል ምን አሉ ?
“ ከእገታው ያልወጡ ኢትዮጵያዋያን ስቃይ ላይ ናቸው። ከእገታ ከወጡት 261 ዜጎች 138 ኢትዮጵያዊያ ናቸው። ከማይናማር ተነስተው ታክ በሚባል ካምፕ ነው ያሉት፤ ከቦርደሩ 82፣ ለባንኮክ 377 ኪሎ ሜትር ርቀት።
ቦታው አሁን ለደኀንነታቸው አስተማማኝ እየሆነ አይደለም። ምክንያቱም ከወጡት 261 የ18 ሀገራት ዜጎች በስምንት ቀናት ሁሉም ወደ ሀገራቸው ሂደዋል። የቀሩት የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው።
ከእገታው እንደወጡ ኢንተርቪው ተደገው ነበር በዛው አካባቢው አካላት፣ የደረሰባቸውን ስቃይ ተናግረው ነበር። ቃለመጠይቁን የሰሙ የታይላንድ ፓሊሶችም መልሰው ወስደዋቸዋል። መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ የወጡት ኢትዮጵያዊንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል። የተመለሰ የለም።
የሌሎቹ ሀገሪት ዜጎችም ኢንተርቪው ተደርገው የነበር፤ ነገር ግን ኤምባሲዎች ሂደው በቀናት ውስጥ ነው የወሰዷቸው። 138ቱ ኢትዮጵያዊን ከእገታው ቢወጡም ወደ ኢትዮጵያ ስላልወጡ አደጋ ላይ ናቸው።
በታይላንድ ካምፕ ላይ ያሉት 138፣ በሌላ ጉዳይ ምክንያት በታይላንድ ፓሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ፣ ገና ቦርደር ላይ እየጠበበቁ ያሉ 100 በአጠቃላይ 259 ኢትዮጵያዊያን ስም ዝርዝራቸው እንደተላከለት ውጪ ጉዳይ ነግሮናል።
በስም ዝርዝራቸው መሠረት መረጃዎችን እያደራጀ እንደሆነ ቢገልጽልንም እስካሁን ድረስ ግን ምንም አይነት ተጨባጭ የሆነ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የተሰራ ነገር የለም።
የወጡት ኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ መንግስት የሚጠብቁት ምን እንደሆነ፥ የአገልግሎት ጊዜው ያለቀ ፓርፓርት ያላቸው ልጆች ስላሉ ማንንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ወደ ታይላንድ መንግስት እንዲልክላቸው፣ የበረራ ትኬቶች እንዲስተካክልላቸው ነው” ብለዋል።
የወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ ፦
“ የታይላንድ መንግስት ‘ዜጎቻችሁን ውሰዱ’ ካለ በኋላ ብዙ ሀገራት ልጆቻቸውን አስወጥተዋል። የኢትዮጵያ ልጆች ግን እየተሰቃዩ ነው ያሉት።
የተወሰኑት አምልጠው ሲወጡ ተከትለው ለወጣት የምከሩ ኢትዮጵያዊያን ማይናማር በወታደሮች ካምፕ ታጉረዋል። ከእገታ የወጡት ወደ ሀገቸው ስላልመጡ ሌሎች ያልወጡት ታጋቾችም እየተሰቃዩ ነው።
አሁንም ወታደራዊ ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ ብቻ ናቸው። ምግብም እየተሰጣቸው አይደለም። ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው። ልጆቹ ያልወጡበት ምክንያት ያገራችን መንግስት ባለመቀበሉ ብቻ ነው” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን ከእገታ የማጡት ኢትዮጵያዊንን በአፋጣኝ ማምጣትና የታገቱትን ወገኖች ለማስለቀቅ ለምን እንዳልተቻለ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥያቄ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አላገኘም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ ከእገታው የወጡት ኢትዮጵያዊያንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል ” - ቤተሰብ
🔵 “ እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም? ” - ኢትዮጵያዊ በታይላንድ
➡️ “ ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው ” - የወላጆች ኮሚቴ
ሰርተው ለመለወጥ ሲሉ ተታለው ወደ ታይላንድ የተሰደዱና በታጣቂዎች በማይናማር ታግተው ቆይተው የወጡና አሁንም በእገታ ያሉ ኢትዮጵያዊያን መንግስት እንዲደርስላቸው በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል።
በሺዎች ከሚቆጠሩት ኢትዮጵያዊያን ታጋቾች ውስጥ 13ዐ የሚሆኑት ከሳምንታት በፊት ከእገታ እንደተለቀቁ፣ ሌሎች በርካቶች ደግሞ ገና ከእገታው እንዳልወጡ፣ የወጡትም ሆኑ ያልወጡት የመንግስትን ድጋፍ እየተጠባበቁ መሆኑን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።
በታይላንድ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ አሁንስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ ከመግደል ያላነሰ ድብድባ ነው የሚካሄደውኮ። እኛ ዜጎች አይደለንም እንዴ? መንግስት ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ትዕዛዝ መስጠት አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታይላንድ በረራ እንዳለው እያየን ነው። እሺ ገበያውም አይዘጋበት ቢያንስ ሰው ይዞ ወደ ታይላንድ መጥቶ ሲመለስ የተወሰኑ ሰዎችን እየቀላቀለ ቢመልሰን ማቃለል አይችልም ?
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኛ አይደለም እንዴ ? ለሥራ ብለን ነው የመጣነዎኮ ስለተቸገርን ገንዘብ ለማግኘት። ገንዘብ ይዘን ደግሞ ወደ ሀገራችን ለመመለስ።
‘መንግስት አላችሁ?’ ተብለን እስከምንጠየቅ መድረሳችን በጣም ያሳፍራል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሌላ አገር ‘ገንዘብ ረዳሁ’ ብሎ ከሚያወራ እዚህ ያሉትን ዜጓቹን አያስወጣም እንዴ ?
እኛስ መቼም ምግብ ባይቀርብልም ከነበርንበት ሁኔታ አንጻር ምንም አይመስለንም። ትኩረት የሚሹት በማይናማር ከእገታ ያልወጡት እኛ ባለን መረጃ ብቻ እንኳ ከ400 በላይ ለሆኑ ኢትዮጵያዊያን ነው። እነርሱ የሚወጡት ደግሞ እኛ ቦታውን ስንለቅላቸው ነው።
እኛ ማይናማር ቦርደር ላይ ነው ያለነው። ሞኤ የሚባል ወንዝ እንደተሻገን። በጣም ሐበሻዎች አሉ። ከአንድ ካምፓኒ ብቻ እስከ 500 የሚደርሱ ሐበሻዎች አሉ።
አብዛኛው ኢትዮጵያ ያለበት አንዱ ካምፓኒ ‘ወደ ሌላ ቦታ እንስዳችኋለሁ’ እያለን ነው። ሌላ ቦታ የሚወስደን ሁሉንም ነገሮች ቁጥጥሩ ለማድረግ ነው። አሁን ያለንበት ቦታ ላይ ደኀንነታችን የተጠበቀ ነው።
ማይናማር ግን ብዙ ሰው እየተጎዳ፣ እየተሰቃዬ ያለበት ፎረይን ፓሊሶች የሌሉበት አካባቢ ነው። ያለንበትን ካምፓኒ አቋርጠን ለመውጣት 2,500 ዶላር ይከፈላል። ያለንበት ግቢ እስከ 25 ካምፓኒዎች አሉ። ወደ ሌላ ግቢ ላለመሄድ ነው ጥረት እያደረግን ያለነው።
ሐበሾችን እየጠበቅን ነው ገና ከእገታ ያልወጡ ስላሉ። አመት ድረስ የቆዩ አሉ። በራሳችን ፈቃድ ስለማያስወጡን።
እስካሁን ወደ ኢትዮጵያ ያልመጣንበት ዋነኛው ምክንያት ሙሉ ወጪ መሸፈን ስላማይችል ነው።
ምክንያቱም ወደ ኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልከው ከኢትዮጵያ መንግስት ምንም አይነት ምላሽ እንዳላገኙ ነው መረጃ የሰጡን። የታይላንድ መንግስት ለኢትዮጵያ መንግስት ደብዳቤ ልኳል። ግን እስከ ሳምንት ምላሽ አልተሰጠም።
ካለንበት ካምፕ ወጥተን ወደ ታይላንድ/ሜኢሶት ኤርፓርት ነው መሄድ ያለብን። ከታይላንድ መንግስት ጋር በመነጋገር ወንዝ ያሻግሩናል። ፓስፓርት የሌለው አንድ ወር መቆየት እንደሚችል ነው የተነገረው።
የተጎዱ ሀበሿች፣ ጀርባቸው ላይ ለምጥ ያለ፣ የታመሙ፣ የተደበደቡ በሙሉ ካምፕ ነው ያሉት። እኛን ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ነው ያልጠየቁን እንጂ ህንዶችን፣ ቻይናዎችን ‘አለንላችሁ’ የሚሉ አሉ።
ምን እያደረጉ እንደሆነ የምናውቀው ነገር የለም። የምናውቀው ዘገባ እያደረጉና ዜግነታችንን ለይተው ብዙ ነገር እየጠየቁ እንደሆነ ነው።
የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው የቀሩት። ከኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ ስላላገኙ። ምላሽ ቢያገኙ ይወጡ ነበር የሚቆዩበት ምክንያት የለም። ለኛም ስጋት የሆነው እነርሱ ባለመሄዳቸው የተነሳ ምናልባት የታይላንድ መንግስት ላይቀበለን ይችላል ” ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያዊያኑ ቤተሰቦችስ በሰጡን ቃል ምን አሉ ?
“ ከእገታው ያልወጡ ኢትዮጵያዋያን ስቃይ ላይ ናቸው። ከእገታ ከወጡት 261 ዜጎች 138 ኢትዮጵያዊያ ናቸው። ከማይናማር ተነስተው ታክ በሚባል ካምፕ ነው ያሉት፤ ከቦርደሩ 82፣ ለባንኮክ 377 ኪሎ ሜትር ርቀት።
ቦታው አሁን ለደኀንነታቸው አስተማማኝ እየሆነ አይደለም። ምክንያቱም ከወጡት 261 የ18 ሀገራት ዜጎች በስምንት ቀናት ሁሉም ወደ ሀገራቸው ሂደዋል። የቀሩት የኢትዮጵያ ዜጎች ብቻ ናቸው።
ከእገታው እንደወጡ ኢንተርቪው ተደገው ነበር በዛው አካባቢው አካላት፣ የደረሰባቸውን ስቃይ ተናግረው ነበር። ቃለመጠይቁን የሰሙ የታይላንድ ፓሊሶችም መልሰው ወስደዋቸዋል። መንግስት እንዲመጡ ስላላደረገ የወጡት ኢትዮጵያዊንም በፓሊስ ተመልሰው እየተወሰዱ ነው። እስካሁን ሰባት ልጆች ተወስደዋል። የተመለሰ የለም።
የሌሎቹ ሀገሪት ዜጎችም ኢንተርቪው ተደርገው የነበር፤ ነገር ግን ኤምባሲዎች ሂደው በቀናት ውስጥ ነው የወሰዷቸው። 138ቱ ኢትዮጵያዊን ከእገታው ቢወጡም ወደ ኢትዮጵያ ስላልወጡ አደጋ ላይ ናቸው።
በታይላንድ ካምፕ ላይ ያሉት 138፣ በሌላ ጉዳይ ምክንያት በታይላንድ ፓሊስ ቁጥጥር ስር የሚገኙ፣ ገና ቦርደር ላይ እየጠበበቁ ያሉ 100 በአጠቃላይ 259 ኢትዮጵያዊያን ስም ዝርዝራቸው እንደተላከለት ውጪ ጉዳይ ነግሮናል።
በስም ዝርዝራቸው መሠረት መረጃዎችን እያደራጀ እንደሆነ ቢገልጽልንም እስካሁን ድረስ ግን ምንም አይነት ተጨባጭ የሆነ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የተሰራ ነገር የለም።
የወጡት ኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ መንግስት የሚጠብቁት ምን እንደሆነ፥ የአገልግሎት ጊዜው ያለቀ ፓርፓርት ያላቸው ልጆች ስላሉ ማንንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ወደ ታይላንድ መንግስት እንዲልክላቸው፣ የበረራ ትኬቶች እንዲስተካክልላቸው ነው” ብለዋል።
የወላጆች ኮሚቴ በበኩሉ ፦
“ የታይላንድ መንግስት ‘ዜጎቻችሁን ውሰዱ’ ካለ በኋላ ብዙ ሀገራት ልጆቻቸውን አስወጥተዋል። የኢትዮጵያ ልጆች ግን እየተሰቃዩ ነው ያሉት።
የተወሰኑት አምልጠው ሲወጡ ተከትለው ለወጣት የምከሩ ኢትዮጵያዊያን ማይናማር በወታደሮች ካምፕ ታጉረዋል። ከእገታ የወጡት ወደ ሀገቸው ስላልመጡ ሌሎች ያልወጡት ታጋቾችም እየተሰቃዩ ነው።
አሁንም ወታደራዊ ካምፕ ያሉ ኢትዮጵያዊያኑ ብቻ ናቸው። ምግብም እየተሰጣቸው አይደለም። ልጆቻችን በረሃብ ሊያልቁብን ነው። ልጆቹ ያልወጡበት ምክንያት ያገራችን መንግስት ባለመቀበሉ ብቻ ነው” ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለምን ከእገታ የማጡት ኢትዮጵያዊንን በአፋጣኝ ማምጣትና የታገቱትን ወገኖች ለማስለቀቅ ለምን እንዳልተቻለ ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥያቄ ቢያቀርብም እስካሁን ምላሽ አላገኘም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939 ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር ” - ኮሚሽኑ
ዛሬ አዲስ አበባ ፤ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ወረዳ 2 በተለምዶ ካሬ ቆሬ ብቄላ መናፈሻ አካባቢ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በሰው ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡን ቃል፣ “ እሳቱ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
“ የፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ (ቁርጥራጭ ጨርቅ) የመሳሰሉ ግብዓቶች መጋዘን ላይ ነው የእሳት አደጋው ያጋጠመው ” ያሉት አቶ ንጋቱ፣ የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ ህብረተሰቡ ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ መስጊድና መኖሪያ ቤት ሳይዛመት መቆጣጠር መቻሉን አስረድተዋል።
“ በእሳት አደጋው ሰው ላይ ጉዳት አልደሰም። የቀረው መረጃ በኢኮኖሚ ላይ የደረሰው ጉዳትና የአደጋ መንስኤ ነው። እሱን ከፓሊሶች ጋር ሆነን እያጣራን ነው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የእሳት አደጋ እየተደጋገመ ያለበት ሁኔታ እየተስተዋለ ነው፤ ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ስንል ሳቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ ንጋቱ፣ “ ትክክል ነው እሳት አደጋ የተደጋገመመበት ሁኔታ አለ። አሁን ያለንበት ወቅት ነፋሻማና ደረቅ አየር ነው ” የሚል ምላሽ ስጥተዋል።
“ እሳት እንዲከሰት ከሚያደርጉ ሦስት መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ ሁለቱን አሁን ካለው የአየር ፀባይ እናገኛለንና መዘናጋትና ቸልተኝነት ዋጋ የሚያስከፍልበት ሂደት ስላለ ህብረተሰቡ በመኖሪያ፣ በስራ አካባቢ እሳትና የኤለክትሪክ ኃይል ምንጮችን ሲጠቀም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ አክለዋል።
“ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ያድርግ። ከዚህ አልፎ ለሚያጋጥም አደጋ፥ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939ኝን ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር” ሲሉ አሳስበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዛሬ አዲስ አበባ ፤ ኮልፌ ቀራኒዮ፣ ወረዳ 2 በተለምዶ ካሬ ቆሬ ብቄላ መናፈሻ አካባቢ ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በሰው ላይ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡን ቃል፣ “ እሳቱ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
“ የፍራሽ መስሪያ የሚሆኑ (ቁርጥራጭ ጨርቅ) የመሳሰሉ ግብዓቶች መጋዘን ላይ ነው የእሳት አደጋው ያጋጠመው ” ያሉት አቶ ንጋቱ፣ የኮሚሽኑ ሰራተኞች፣ ህብረተሰቡ ባደረጉት ርብርብ እሳቱ ወደ መስጊድና መኖሪያ ቤት ሳይዛመት መቆጣጠር መቻሉን አስረድተዋል።
“ በእሳት አደጋው ሰው ላይ ጉዳት አልደሰም። የቀረው መረጃ በኢኮኖሚ ላይ የደረሰው ጉዳትና የአደጋ መንስኤ ነው። እሱን ከፓሊሶች ጋር ሆነን እያጣራን ነው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የእሳት አደጋ እየተደጋገመ ያለበት ሁኔታ እየተስተዋለ ነው፤ ማህበረሰቡ ምን አይነት ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ? ስንል ሳቀረብንላቸው ጥያቄ አቶ ንጋቱ፣ “ ትክክል ነው እሳት አደጋ የተደጋገመመበት ሁኔታ አለ። አሁን ያለንበት ወቅት ነፋሻማና ደረቅ አየር ነው ” የሚል ምላሽ ስጥተዋል።
“ እሳት እንዲከሰት ከሚያደርጉ ሦስት መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ ሁለቱን አሁን ካለው የአየር ፀባይ እናገኛለንና መዘናጋትና ቸልተኝነት ዋጋ የሚያስከፍልበት ሂደት ስላለ ህብረተሰቡ በመኖሪያ፣ በስራ አካባቢ እሳትና የኤለክትሪክ ኃይል ምንጮችን ሲጠቀም ከወትሮው በተለዬ ሁኔታ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ አክለዋል።
“ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ያድርግ። ከዚህ አልፎ ለሚያጋጥም አደጋ፥ አንዳንድ ጊዜ አደጋዎች ከተስፋፉ በኋላ የመደወል ሁኔታ አለ። በ939ኝን ፈጥኖ መደወልም ያስፈልጋል ቶሎ ደርሰን እንድንቆጣጠር” ሲሉ አሳስበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በአደራ የሰበሰብነውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለተለያዩ አገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ለግሰናል " - ዳሽን ባንክ
ዳሽን ባንክ ዛሬ “ ሸሪክ ” የተሰኘውን ከወለድ ነፃ አገልግሎት የ7ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በዋና መስሪያ ቤቱ አክብሯል።
በዚህም ከደንበኞቹ በአደራ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለተለያዩ አገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች መለገሱን አስታውቋል፡፡
በዛሬው ዕለትም ለ31 ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ መደረጉ ነው የተገለጸው።
በከወለድ ነፃ አገልግሎት ብቻ ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራት መቻሉ የተገለጸ ሲሆን፣ የአገልግሎቱ ቺፍ ኦፊሰር አቶ መስፍን በዙ ባደረጉት ንግግር አመኔታቸውን ለሰጡ ደንበኞች ምስጋና አቅርበዋል።
የካቲት 26/2010 ዓ/ም በአንድ መስኮት የተጀመረው አገልግሎት አድጎ ከ80 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ ቅርንጫፎችና ከ800 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች በመስኮት ለደንበኞቹ የተሟላ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።
በሱማሌ ክልል ለሚገኙ ሴት ስራ ፈጣሪዎች ከወለድ ነጻ በሆነ መንገድ 100 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ ብድር ማቅረቡን አስታውሷል።
" ሸሪክ " እ.ኤ.አ ህዳር 28/ 2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ “ጠንካራ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሚሰጥ ባንክ” በሚል አይ ኤፍ ኤ ከተሰኘው ድርጅት ዕውቅና ማግኘቱ ተገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ዳሽን ባንክ ዛሬ “ ሸሪክ ” የተሰኘውን ከወለድ ነፃ አገልግሎት የ7ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በዋና መስሪያ ቤቱ አክብሯል።
በዚህም ከደንበኞቹ በአደራ የሰበሰበውን ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ለተለያዩ አገር በቀል ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች መለገሱን አስታውቋል፡፡
በዛሬው ዕለትም ለ31 ሀገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የገንዘብ ድጋፍ መደረጉ ነው የተገለጸው።
በከወለድ ነፃ አገልግሎት ብቻ ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ማፍራት መቻሉ የተገለጸ ሲሆን፣ የአገልግሎቱ ቺፍ ኦፊሰር አቶ መስፍን በዙ ባደረጉት ንግግር አመኔታቸውን ለሰጡ ደንበኞች ምስጋና አቅርበዋል።
የካቲት 26/2010 ዓ/ም በአንድ መስኮት የተጀመረው አገልግሎት አድጎ ከ80 በላይ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት የሚሰጡ ቅርንጫፎችና ከ800 በላይ በሆኑ ቅርንጫፎች በመስኮት ለደንበኞቹ የተሟላ የባንክ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ተጠቁሟል።
በሱማሌ ክልል ለሚገኙ ሴት ስራ ፈጣሪዎች ከወለድ ነጻ በሆነ መንገድ 100 ሚሊዮን ብር ተዘዋዋሪ ብድር ማቅረቡን አስታውሷል።
" ሸሪክ " እ.ኤ.አ ህዳር 28/ 2023 በባህሬን ማናማ በተካሄደው 9ኛው የኢስላሚክ ሪቴል ባንክ ሽልማት ላይ “ጠንካራ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በኢትዮጵያ የሚሰጥ ባንክ” በሚል አይ ኤፍ ኤ ከተሰኘው ድርጅት ዕውቅና ማግኘቱ ተገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ 🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች ➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ…
#Update
🔴 “ ወደ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” - ቤተሰቦች
➡️ “ ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የተያዙት ” - ጤና ባለሙያ
የአራት ወራት አዲሱ ደወመዝ ክፍያ ስላልተፈጸመላቸው የሥራ ማቆም አድማ በመምታታቸው ከታሰሩት የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች መካከል አራቱ እንዳልተፈቱ ቤተሰቦቻቸውና የጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
መጀመሪያ የታሰሩት ዘጠኝ እንደነበሩ ሠራተኞቹ ከቀናት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ እስራቱ ቀጥሎ በአጠቃላይ 12 ሰዎች ታስረው እንደነበርና አራቱ እንዳልተፈቱ ነግረውናል።
የታሳሪ ቤተሰቦችና ጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
አንድ ጤና ባለሙያ በሰጡን ቃል፤ “ የተፈቱና ሌሎቹም በሥራ ገበታ ላይ ናቸው። የነዚህ የአራቱ አለመፈታት ግን እስካሁን ምስጢር ሆኖብናል። ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የታሰሩት ” ሲሉ ተናግረዋል።
የታሳሪ ቤተሰቦች በበኩላቸው “ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” ብለዋል።
“ ጥያቄው የሆስፒታሉ አካላት ሁሉ ነው። የፓለቲካ ጉዳይ የሌለበት የደመወዝ ጥያቄም ነው። ከደመወዝ ይከፈለን ውጪ ያነሱት ጥያቄ የለሞ ” ሲሉም ሞግተዋል።
አንዲት የታሳሪ ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ ባለቤታቸው ከታሰሩ ቀናት እንዳስቆጠሩ፣ እስካሁንም እንዳልተፈቱ፣ ያሉበትን ሁኔታም እንደማያውቁ ገልጸዋል።
ሌላኛው የታሳሪዋ የቅርብ ሰው የ10 ወር ጨቅላ ህፃን ያላት ጤና ባለሙያ እንደታሰረች ገልጸው፣ በዋስ እንደትለቀቅ እንኳ ቢሞከር ፈቃደኛ አካል አለመኖሩን ጠቁመዋል።
“ አጥቢ ከመሆኗ አንፃር ቀነ ገደብ ተጠይቆ ነበር። ፍርድ ቤት ዋስትና እንዲሰጣት ውሳኔ ቢያስተላልፍም እንዳትወጣ በፓሊስ ተከልክላለች ” ሲሉ ነው የወቀሱት።
የታሳሪ ቤተሰቦች፣ የታሰሩት የጤና ባለሙያዎች እንደሆኑ፣ ብዙ የህክምና ተገልጋዮች መጉላላታቸውም ከግምት ሊገባ እንደሚገባ አሳስበው፣ በፍጥነት እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
የታሰሩት ለምን እንዳልተፈቱ ምላሽ ለማግኘት የጸጥታ አካላትን ለማካተት የተደረገው መከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለሆናቸው ለጊዜው አልተሳካም።
የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ከዚህ ቀደም ጠይቀነው፣ በሌሎች ሆስፒታሎችም ጭምር ከ2000 በላይ ሠራተኞች ክፍያው እንዳልተፈጸመላቸው፣ የታሰሩትን ለማስፈታትም እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ ወደ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” - ቤተሰቦች
➡️ “ ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የተያዙት ” - ጤና ባለሙያ
የአራት ወራት አዲሱ ደወመዝ ክፍያ ስላልተፈጸመላቸው የሥራ ማቆም አድማ በመምታታቸው ከታሰሩት የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች መካከል አራቱ እንዳልተፈቱ ቤተሰቦቻቸውና የጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
መጀመሪያ የታሰሩት ዘጠኝ እንደነበሩ ሠራተኞቹ ከቀናት በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ እስራቱ ቀጥሎ በአጠቃላይ 12 ሰዎች ታስረው እንደነበርና አራቱ እንዳልተፈቱ ነግረውናል።
የታሳሪ ቤተሰቦችና ጤና ባለሙያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
አንድ ጤና ባለሙያ በሰጡን ቃል፤ “ የተፈቱና ሌሎቹም በሥራ ገበታ ላይ ናቸው። የነዚህ የአራቱ አለመፈታት ግን እስካሁን ምስጢር ሆኖብናል። ሰልፍ ላይ ስለተገኙ ብቻ ነው የታሰሩት ” ሲሉ ተናግረዋል።
የታሳሪ ቤተሰቦች በበኩላቸው “ አራት ጤና ባለሙያዎች ገና አልተፈቱም። የጠየቁት መብታቸውን ስለሆነ ሊፈቱ ይገባል ” ብለዋል።
“ ጥያቄው የሆስፒታሉ አካላት ሁሉ ነው። የፓለቲካ ጉዳይ የሌለበት የደመወዝ ጥያቄም ነው። ከደመወዝ ይከፈለን ውጪ ያነሱት ጥያቄ የለሞ ” ሲሉም ሞግተዋል።
አንዲት የታሳሪ ቤተሰብ በሰጡን ቃል፣ ባለቤታቸው ከታሰሩ ቀናት እንዳስቆጠሩ፣ እስካሁንም እንዳልተፈቱ፣ ያሉበትን ሁኔታም እንደማያውቁ ገልጸዋል።
ሌላኛው የታሳሪዋ የቅርብ ሰው የ10 ወር ጨቅላ ህፃን ያላት ጤና ባለሙያ እንደታሰረች ገልጸው፣ በዋስ እንደትለቀቅ እንኳ ቢሞከር ፈቃደኛ አካል አለመኖሩን ጠቁመዋል።
“ አጥቢ ከመሆኗ አንፃር ቀነ ገደብ ተጠይቆ ነበር። ፍርድ ቤት ዋስትና እንዲሰጣት ውሳኔ ቢያስተላልፍም እንዳትወጣ በፓሊስ ተከልክላለች ” ሲሉ ነው የወቀሱት።
የታሳሪ ቤተሰቦች፣ የታሰሩት የጤና ባለሙያዎች እንደሆኑ፣ ብዙ የህክምና ተገልጋዮች መጉላላታቸውም ከግምት ሊገባ እንደሚገባ አሳስበው፣ በፍጥነት እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
የታሰሩት ለምን እንዳልተፈቱ ምላሽ ለማግኘት የጸጥታ አካላትን ለማካተት የተደረገው መከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለሆናቸው ለጊዜው አልተሳካም።
የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ከዚህ ቀደም ጠይቀነው፣ በሌሎች ሆስፒታሎችም ጭምር ከ2000 በላይ ሠራተኞች ክፍያው እንዳልተፈጸመላቸው፣ የታሰሩትን ለማስፈታትም እየተሰራ መሆኑን ገልጸው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ከየካቲት 24 በኋላ የፋይዳ መታወቂያ የሌለው ደንበኛ የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር ትኬት መቁረጥ አይችልም " - የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር አክስዮን ማህበር
የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ለመንገደኞች የጉዞ ትኬት የሚያገኙበትን መንገድ ከሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረጉን ገልጿል።
ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረውን በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ ሂደት አገልግሎቱን ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ መደረጉን የኢትዮጵያ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር የኮምዩኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ወ/ሮ እስራኤል ወልደ መስቀል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ወ/ሮ እስራኤል " ማስታወቂያዎችን ስንሰራ የቆየን በመሆኑ የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ ነው ነገር ግን ይሄንን ሳምንት ልዩ በሆነ መንገድ እና ሰውም የአጠቃቀም ጉድለት ስላለ የጉዞ ትኬት እየቆረጥን እንገኛለን ከሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ በኃላ ግን ያለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የባቡሩን ትኬት ማግኘት አይቻልም " ብለዋል።
ክፍያው የሚፈጸመው በቴሌ ብር ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች የፋይዳ የምዝገባ ቁጥራቸውን ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ደግሞ ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል።
ባለሞያዋ በትኬት ዋጋ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ አለመኖሩን አንስተው በነባሩ ዋጋ ዲጂታላይዝ ብቻ መደረጉን ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ፉሪ የሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎች አሰራሩ ዲጂታላይዝ ስለሆነ የመንገደኞችን የአገልግሎት ትኬት የመቁረጥ ስራ እንደማይሰሩ ወ/ሮ እስራኤል ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር ለመንገደኞች የጉዞ ትኬት የሚያገኙበትን መንገድ ከሰኞ የካቲት 17/2017 ዓ/ም ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ ማድረጉን ገልጿል።
ከሁለት ቀን በፊት የተጀመረውን በኦንላይን ትኬት የመቁረጥ ሂደት አገልግሎቱን ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ መደረጉን የኢትዮጵያ ጅቡቲ የባቡር መንገድ አክስዮን ማህበር የኮምዩኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ወ/ሮ እስራኤል ወልደ መስቀል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ወ/ሮ እስራኤል " ማስታወቂያዎችን ስንሰራ የቆየን በመሆኑ የፋይዳ መታወቂያ ግዴታ ነው ነገር ግን ይሄንን ሳምንት ልዩ በሆነ መንገድ እና ሰውም የአጠቃቀም ጉድለት ስላለ የጉዞ ትኬት እየቆረጥን እንገኛለን ከሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ በኃላ ግን ያለ ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የባቡሩን ትኬት ማግኘት አይቻልም " ብለዋል።
ክፍያው የሚፈጸመው በቴሌ ብር ሲሆን አገልግሎቱን ለማግኘት ለሃገር ውስጥ ተጠቃሚዎች የፋይዳ የምዝገባ ቁጥራቸውን ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ተጠቃሚዎች ደግሞ ፓስፖርታቸውን በመጠቀም ትኬት ማግኘት እንደሚችሉ አሳውቀዋል።
ባለሞያዋ በትኬት ዋጋ ላይ ምንም አይነት ጭማሪ አለመኖሩን አንስተው በነባሩ ዋጋ ዲጂታላይዝ ብቻ መደረጉን ጠቁመዋል።
ከዚህ ቀደም አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ ፉሪ የሚገኙ የትኬት ሽያጭ ቢሮዎች አሰራሩ ዲጂታላይዝ ስለሆነ የመንገደኞችን የአገልግሎት ትኬት የመቁረጥ ስራ እንደማይሰሩ ወ/ሮ እስራኤል ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia