TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.6K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ምን ውሳኔ አሳለፈ ? የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ ውይይት አካሂዶ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል። 1. በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወስኗል። ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022)…
#Ethiopia🇪🇹

አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያው መነሳቱ ለባንኮች ምን ትርጉም አለው ?

ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ባካሔደው ሶስተኛ ስብሰባ፣ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ከውሳኔዎቹ አንዱም የንግድ ባንኮች ሲገዙት ከነበረው የግምጃ ቤት ቦንድ ጋር የሚያያዝ ነው፡፡

ኮሚቴው፣ የንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ እንዲነሳ መወሰኑን አስታውቋል፡፡

ይህም የሆነው በአሁኑ ወቅት የመንግስት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉና መንግስት የበጀት ጉድለቱን ለማሟላት የውጭና ገበያ መር ከሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡

የንግድ ባንኮች ቦንድ እንዲገዙ ሲደርግ የነበረው አስገዳጅ መመሪያ በመነሳቱ፣ ለባንኮቹ ምን ፋይዳ አለው ? በማለት ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ከፍተኛ የባንክ ባለሙያ፣ " አሰራሩ በባንኮች ዘንድ የገንዘብ እጥረት እንዲፈጠር አስተዋፅኦ ስለነበረው፣ ይህ ውሳኔ በጣም ጠቃሚ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡  

የባንክ ባለሙያው በዝርዝር ምን አሉ ?

" ቦንዱ እንኳን ተነሳ፡፡ በቦንዱ ምክንያት ለአምስት አመት ታስሮ የሚቀመጥ ገንዘብ ነበር፡፡ ባንኮቹ ቦንድ የገዙበት ገንዘብ ከአምስት አመት በኋላ ነው የሚመለስላቸው፡፡

ይህ አስገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ፣ በባንኮች የገንዘብ እጥረት/የሊኩዲቲ ችግር እንዲመጣ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ለሊኩዲቲ ችግር መከሰት አንዱ መንስኤ የነበረው እሱ ነው፡፡

የሆነ ብድር በሰጠህ ቁጥር የተወሰነ ፐርሰንት ቦንድ እድትገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ብድር በሰጠህ ቁጥር የብድሩን 20 በመቶ ቦንድ ግዛ ትባላለህ፡፡ እስከ 20 በመቶ እንድተገዛ ትገደድ ነበር፡፡ ለአንድ ሰው አምስት ጊዜ ካበደርክ ያስቀመጥከውን ገንዘብ በሙሉ ወሰደው ማለት ነው የቦንድ ግዢው፡፡ በዚህ መልኩ ባንኮች ብድር በሰጡ ቁጥር ተደራራቢ የቦንድ ግዢ ስለሚፈፅሙ እና ገንዘቡም የሚመለሰው ከአምስት አመት በኋላ ስለነበረ ለገንዘብ እጥረት አጋልጧቸዋል።

አሁን ይኼ በመቆሙ ትልቅ እፎይታ ነው የሚሰጣቸው፡፡ ለችግራቸው መፍትሔ ይሆናል፡፡ ለገንዘብ እጥረቱ ማስተንፈሻ ነው፡፡ ብሔራዊ ባንክ የወሰደው እርምጃ በእጅጉ አጋዥ ነው፣ የሚያስመሰግነው ነው፡፡

በቦንድ ግዢ ከባንኮች ሲሔድ የነበረው የገንዘብ መጠን፣ ባንኮቹ በሚሰጡት የብድር መጠን ላይ የሚመሰረት ነበር፡፡ አሁን ይሔ አሰገዳጅ የቦንድ ግዢ መመሪያ በመቅረቱ፣ የባንኮቹን የገንዘብ እጥረት በምን ያህል መጠን ሊያቃልለው እንደሚችል ማወቅ ይከብዳል፣ ግን በእጅጉ ያቃልላል፡፡

ይሔ ጥሩ እርምጃ ሆኖ፣ የንግድ ባንኮች የሚሰጡት ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያ ደግሞ አልተነሳም፡፡ ከ18 በመቶ እንዳይበልጥ የተቀመጠው የብድር ጣሪያ እስከ መስከረም ወር እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡

ብሔራዊ ባንክ በዚሁ እርምጃው ይህንንም 18 በመቶ የሚለውን የብድር ጣሪያ ቶሎ ቢያነሳው ጥሩ ነበር፡፡
የብድር ጣሪያው በባንኮች አሰራር ላይ ችግር እየፈጠረ ነው ያለው፡፡ ለምን ብትል ተበዳሪዎች ብድራቸውን ከመለሱ በኋላ በባንኮች ላይ በተጣለው የብድር ጣሪያ ምክንያት መልሰው እንደማይበደሩ ስለሚያውቁ የመጀመሪያውንም ብድራቸውን አይከፍሉም፡፡ ለባንክ የሚከፍሉትን እዳ ለሌላ አገልግሎት ያውሉታል፡፡

ይልቁንም ለባንክ መክፈል የነበረባቸውን ገንዘብ ለሌላ ንግድ እያገላበጡ ይጠቀሙበታል፡፡ ለዚህ ነው እዳ ውስጥ የሚገቡት፡፡ ባንኮቹ በተቀመጠው የ 18 በመቶ የብድር ጣሪያ ምክንያት ተጨማሪ ብድር መስጠት አይችሉም ብቻ ሳይሆን ቀድመው ያበደሩትን ገንዘብ ማስመለስ አልቻሉም፡፡

ብሔራዊ ባንክ ይህንን የብድር ጣሪያ የሚያነሳበትን ጊዜ በጉጉት ነው የምንጠብቀው፡፡ እርምጃው ለኢንቨስትመንትና ለስራ ፈጠራም አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ የግሉ ዘርፍ ከባንኮች እየተበደረ ኢንቨስት ካላደረገ ኢኮኖሚው አይንቀሳቀስም፣ የስራ እድል ሊፈጠር አይችልም፣ ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖው ብዙ ነው፡፡ " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.05K🙏67👏36🤔21😢17😭17😡15🕊13😱12🥰11
TIKVAH-ETHIOPIA
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት " ስጋት ላይ ጥሎናል " ያሉት አዲስ መመሪያ ምን ይዟል ? የኢትዮጵያ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አሰራር ስርዓት ለማስያዝ በሚል ዳግም ምዝገባ በማካሔድ ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም በሰጣቸው መግለጫዎች አስታውቋል፡፡ በዚህ ሒደት 85 የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲሱ መስፈርት መሰረት ዳግም ለመመዝገብ ፈቃደኛ ስላልሆኑ እንደሚዘጉም…
" መንግስት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የመዝጋትም ሆነ የማዳከም ፍላጎት የለውም " - የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች በዳግመ ምዝገባው ዙርያ ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ መንግስት ተቋማቱን የማጥፋት እቅድ አለው እየተባለ ለሚቀርበው ቅሬታ በሰጡት አስተያየት፣ " ይሔ አስተያየት ስህተት ነው፣ እነዚህን ተቋማት የማዳከም አላማ የለም " ብለዋል፡፡

" ይልቁንም መንግስት እነዚህን ተቋማት የማጠናከር አላማና ፍላጎት ነው ያለው፣ የዳግመ ምዝገባና ምዘና ሒደቱ ትኩረትም ይህን እውን ማድረግ ነው " ሲሉ ገልፀዋል፡፡

የዳግመ ምዝገባና ምልከታ ሒደቱ በአዲስ አበባ መጠናቀቁን ተናግረው፣ በቀጣይ የትኞቹ ተቋማት ይቀጥላሉ፣ የትኞቹ አይቀጥሉም የሚለውን ለመግለፅ ሪፖርት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የአዲስ አበባው የዳግመ ምዝገባና ምዘና ስራ በመጠናቀቁ፣ በቅርቡ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?

" አሁን እየተከናወነ ባለው ዳግመ ምዝገባና ምዘነና ሒደት የተፈለገው፣ የትምህርት ተቋማቱ መሰረታዊ በሆነ መንገድ ራሳቸውን እንዲያድሱ ነው፡፡

ባለቤትነታቸው እንኳ የማይታወቅና አጠራጣሪ የሆኑ ተቋማት አሉ፡፡ እነዚህን ችግሮች የማጥራት ስራ ነው እየተሰራ ያነው፡፡መዝጋት የምትፈልገውን ተቋም ይህን ያህል ጊዜ ማቆየት አያስፈልግም፡፡ በፖሊሲ አቅጣጫ አስቀምጠህ ከገበያ እንዲወጡ ማድረግ ይቻላል፡፡ ግን እሱ አይደለም አላማችን፡፡

የእኛ አላማ፣ ትናንሽ ቢዝነሶች ሆነው የጀመሩት ተቋማት ወደ አንድ ተደራጅተውና ተጠናክረው እንዲመጡ ነው፡፡ ካልቻሉ ደግሞ ከገበያው መውጣት አለባቸው፡፡

ክቡር ሚኒስትሩ (ፕሮፌሰር ብረሀኑ ነጋ) ከዚህ በፊት የተናገሩት ነገርም (50 ተቋማት ይበቃሉ ማለታቸው ይታወሳል) ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ ጠንከር ጠንከር ያላችሁ ተቋማት ሁኑ፡፡ ጥቂት ተቋማት ይበቃሉ፡፡ ይህ ሁሉ ተቋም አለ ማለት፣ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ የተለየ ለውጥ ይመጣል ማለት አይደለም ነው ያሉት፡፡ ጥራት ያለው ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡ የእኛም አላማ ይኸው ነው፡፡

ከዚህ በፊት ወጣ የተባለው፣ ' አብዛኞቹ ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተብለዋል ' የተባለው ዘገባ ስህተት ነው፡፡ ሚድያዎችን ለመተባበር ብለን የሰጠናቸውን መረጃ አዛብተው ዘገቡት፡፡ ከዛም፣ ሁሉም የግል ትምህርት ተቋማት መስፈርቱን አያሟሉም ተባለ ተብሎ ተስተጋባ፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡

በወቅቱ ያልነው፣ አብዛኞቹ ተቋማት ለዳግመ ምዝገባ የሚሆን የተሟላ ሰነድ አላቀረቡም ነው፡፡ ሰነድ አስገቡ ስንላቻው ስለነበር ማለት ነው፡፡ ሰነድ አላሟሉም ማለትና ያስገቡትን ሰነድ ገምግሞ መስፈርቱን አላሟሉም ማለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡

ቀደም ሲል ሒደቱ በጣም ቀላል ነበር ኮሌጅ ለመክፈት፣ ትንሽ ገንዘብ ካለህ አንድ ሁለት ክፍል ተከራይተህ መክፈት ነበር፡፡ በዚህ መሰሉ ሒደት መቀጠል አይቻልም አሁን፡፡ ይህን ቀላል አካሔድ የለመዱ ተቋማት መቀጠል አይችሉም፡፡ የተቀመጠውን መስፈርት አሟልተው በትንሹ ኮሌጅ የሚያስብል ስራ ሰርተው ነው ይህንን ቢዝነስ መጀመርና ማስኬድ ያለባቸው፡፡

አሁን በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በተቀመጠው መስፈርት መሰረት እንደ ኮሌጅ መቀጠል እችላለሁ የሚሉት ተቋማት ናቸው የተመዘገቡት፡፡ ከተመዘገቡት መካከል ደግሞ፣ አሁን ግምገማ ተደርጎ፣ ሰነዶቻቸው ተፈትሸው፣ የመስክ ምልከታም ተደርጎ፣ በትክክል መስፈርቱን ያሟላሉ የሚባሉትን ውጤት እንገልፃለን፡፡

አሁን ባለው ሁኔታ የአዲስ አበባን ተቋማት ምዝገባና ምልከታ ሙሉ በሙሉ አጠናቀናል፡፡ ውጤቱን ለመግለፅ ሪፖርቱን በማዘጋጀት ላይ ነው ያለነው፡፡ ጎን ለጎን ደግሞ በክልሎች ይህንን ስራ ለመጀመር ቅድመ ዘግጅት እያደረግን ነው፡፡ ስራው በአዲሱ የበጀት አመት የሚጀመር ይሆናል፡፡

እስካሁን ከዘርፉ የወጡ ተቋማትን በተመለከተ የተለያየ አሀዝ ይቀርባል፡፡ ለምሳሌ መጀመሪያ ላይ 84 ተቋማት ሳይመዘገቡ ቀሩ፡፡ በኋላ ላይ ግን ዘግይተው የመጡ አሉ፡፡ ከነሱ ውስጥ በቂ ምክንያት ያቀረቡትን መዝግበን እየገመገምን ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ተመዝግበው ከነበሩት ውስጥ ለመውጣት ሒደት ላይ ያሉ አሉ፣ ጎንለጎን ማለት ነው፡፡ ይህ የእነሱ ገባ ወጣ ማለት፣ ከዘርፉ የወጡ ተቋማት ብዛት በየጊዜው እንዲለያይ አድርጎታል፡፡ እንደዛም ሆኖ፣ አሁን የምዝገባና የግምገማ ሒደት ላይ ስለሆንን ትክክለኛ ቁጥሩን ማስቀመጥ ቢያስቸግርም ቢያንስ 80 የግል ትምህርት ተቋማት፣ ስራቸውን አቋርጠው ከዘርፉ ተሰናብተዋል፡፡

የዳግመ ምዝገባው መመሪያ ላይ በቂ ውይይት አልተደረገበትም፣ ከዘርፉ ተዋናዮች ግብአት አልተወሰደም የሚለውም ጉዳይ ትክክል አይደለም፡፡ ከተቋማቱ ባለቤቶች በሁለት መንገድ ግብአት ተቀብለናል፡፡ አንደኛው፣ ከውይይት መድረክ የተገኘው ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ በፅሑፍ የተቀበልነው ነው፡፡ በዚህ መንገድ በአዲስ አበባ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ከተደረገ ውይይትና በፅሑፍ ከቀረቡልን ሀሳቦች ግብአት ወስደናል፡፡አስፈላጊ የሆኑትንና ያስኬዳሉ የምንላቸውን ሀሳቦች በግብአትነት ተጠቅመንባቸዋል፡፡

ለምሳሌ ፦ ከእነሱ ተቀብለን ካካተትናቸው ሀሳቦች አንዱ፣ በመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶ ያላሳለፈ ተቋም መቀጠል የለበትም የሚለው መስፈርት መቼ ተግባራዊ መሆን ይጀምር የሚለው ላይ የእነሱን ሀሳብ ተቀብለን የእፎይታ ጊዜ እንዲሰጥ አድርገናል፡፡

ይህ መስፈርት መተግበር የሚጀምረው፣ መመሪያው በወጣበት ጊዜ ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች ላይ እንጂ፣ በነባር ተማሪዎች ላይ መሆን የለበትም የሚለው ሀሳብ ከነሱ የመጣ ነው፡፡ ይህ ሀሳባቸው አሳማኝ በመሆኑ ተቀበልነው፡፡ አሁን ለትግበራው ሁለት አመት ገደማ አላቸው፡፡ በ 2019 ዓ.ም ገደማ ነው መተግበር የሚጀምረው ይህ መመሪያ፡፡ ሌሎችም የተቀበልናቸው ሀሳቦች አሉ፡ " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
866😡111🙏30🤔24😭19🕊16🥰10😢6😱5
" በወረዳዎቹ በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያው ይመለሳሉ " - ፓርቲው

ቦሮ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ፣ " የ'ሸኔ' ታጣቂዎች በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለይ በመተከልና ካማሺ ዞኖች እያደረሱት ያለው ጥቃት ቀጥሏል " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ፓርቲው ሰሞኑንም በወንበራ ወረዳ ጥቃት መድረሱን ገልጾ፣ " የክልሉ መንግስት ለጉዳዩ በቂ ትኩረት በመስጠት በቂ የጸጥታ ኃይል በመላክና በአከባቢው የመከላከያ ካምፕ በማቋቋም የህዝቡን ሰላምና ደህንነት እንዲያስጠብቅ " ጠይቋል።

" በካማሺ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች፣ በመተከል ዞን በቡለን፣ ድባጢና ወምበራ ወረዳዎች ታጣቂዎቹ የሚያደርሱት ጥቃት ተጠናክሮ ቀጥሏል " ያለው ፓርቲው፣ " ታጣቅዎቹ ንጹሐንን እና የጸጥታ አካላትን ይገድላሉ፣ የግልና የመንግስት ሀብት፣ ንብረት፤ የመንግስት ተቋማትን ይዘርፋሉ፤ ያወድማሉ " ሲልም ከሷል።

" ባለፈው ወር ቡለን ከተማ፣ ድባጢ ወረዳ በርበር ከተማ ሁለት ጊዜ ጥቃት ያደረሱ ሲሆን፣ በቡለን ከተማ በአንድ ሌሊት ብቻ የአረፋ በዓል በማክበር ላይ የነበሩ 11 የክልሉ ልዩ ኃይል አባላትን ከመግደል ባለፈ በርካታ ንጽሐንን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ የሃይማኖት አባቶችንና የጸጥታ አካላት ገድለዋል፤ ንጽሐንን አግተዋል " ብሏል።

ታጣቂዎቹን ተቋማትን " ዘርፈዋል፤ አውድመዋል " ሲል የከሰሰው ፓርቲው፣ " ሰሞኑን በወምበራ ወረዳ ወግዲና ሌሎች ቀበሌዎች ተመሳሳይ ጥቃቶችን ፈጽመዋል። ይህ ታጣቂ ቡድን በድባጢ ወረዳ ከ60% በላይ፣ በቡለን ወረዳ ከ30% በላይ ቀበሌዎችን በራሱ ቁጥጥር ስር በማደርግ ሰሞኑን ደግሞ በወንበራ ወረዳ በወግዲ ቀበሌ ግዛቱን ለማስፋፋት እየጣረ ይገኛል " ሲል ጠቁሟል።

ፓርቲው፣ " የሸኔ ታጣቂዎች በየወረዳዎቹ በሚኖሩ በሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች ላይ ነው ጥቃት የሚያደርሱት " ብሎ፣ " በዚህ ምክንያት ነዋሪዎቹ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። በርካቶችም ተፈናቅለው ወደ አጎራባች ከተሞችና ወረዳዎች እየሄዱ ይገኛሉ " ብሏል።

" ታጣቂዎቹ በወረዳዎቹ ይህንን ሁሉ ጥቃት ሲፈጽሙና ወረዳዎች ‘ካቅማችን በላይ ነው’ እያሉ ለክልሉ መንግስት ሲያሳውቁ የክልሉ መንግስት ግን ለምን በቂ ትኩረት መስጠት እንዳልፈለገና ህዝቡን መከላከል ለምን እንዳልቻለ ለእኛ እንቆቅልሽ ሆኗል " ነው ያለው።

ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ " ህዝቡም በተደጋጋሚ ለክልሉ መንግስት የይድረሱልኝ ጥሪ ቢያቀርብም ሰሚ አላገኘም። በወረዳዎች በቂ የጸጥታ ኃይል የለም። ጥቂት የጸጥታ ኃይሎችም ታጣቅዎቹ ጥቃት ካደረሱና ዝርፊያ ከፈጸሙ በኋላ ይመጡና ወዲያውኑ ወይንም በነጋታው ይመለሳሉ " ሲል ነው የገለጸው።

" ህዝቡ ከፍተኛ ስጋት ላይ ይገኛል። ከሁሉም በላይ ይህ ሁሉ ጥቃትና በደል በህዝቡ ሲደርስ ክስተቱ በየትኛውም የመንግስት ሚዲያ አለመዘገቡና ሽፋን አለማግኘቱ ህዝቡን አሳዝኗል " በማለትም ወቅሷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
433😡51😭36🙏15🕊13💔8😢7🤔5😱5👏2
" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " - የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን

በአራት ክልሎች ኢንደሚክ የሚባሉትን ጨምሮ ወደ 54 የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳትን በውጪ ዜጎች እየታደኑ በዶላር እየተሸጡ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።

በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ባለሙያ አቶ ፋንታዬ ነጋሽ በሰጡን ገለጻ፣ ለምሳሌ " አንድ ኒያላ 15 ሺሕ ዶላር ነው የሚሸጠው፤ ይሄ ይበቃል? አይበቃም? የሚለው ገና እየታየ ነው በሕግ፤ አልጸደቀም እንጂ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድረስ ገብቷል ረቂቁ። ዋጋው በቂ አይደለም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ እንዲህ አይነት በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳት መታደናቸው ልክ አይደለም የሚሉ ቁጣዎች እየተሰነዘሩ ነው፤ ለዚህ ትችት ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? ሲል አቶ ፋንታዬን ጠይቋል።

" ኢንደሚክ እንስሳት ይታደናሉ፤ ያም ደግሞ ዝም ብሎ በዘፈቀደ ሂዶ ማደን ሳይሆን ሳይንሳዊ በሚሆን መንገድ ተጠንቶ፤ ተቆጥረው ይህን ያክል ቢገደል ተብሎ በሚሰጥ ኮታ መሠረት ነው። የእንስሳቱን የመኖር ህልውና ምንም አደጋ ላይ በማይጥል መልኩ ተጠንቶ ነው ያ የሚደረገው፤ ያም ሲደረግ ደግሞ ከፌደራል፣ ከክልል የተውጣጡ ባለሙያዎች አጥንተው ሳይንሳዊ የሆነ ሪሰርች ቀርቦ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ሁሉም የየራሳቸው ዋጋና ኮታ አላቸው። ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " ብለዋል ባለሙያው።

ይህ የሚሆነው አንድ እንስሳ ምን ያህል ቢገደል ነው የእንስሳቱን ቁጥር የማይጎዳው? ተብሎ ቀንዱ ተለክቶ እድሜው ታውቆ እንደሆነ አስረድተው፣ "ለምሳሌ ኒያላን ከ29.5 ኢንቺ በታች ቱሪስቶች በስህተት እንኳ ከገደሉ የእንስሳውን እጥፍ ነው የሚከፍሉት። ማንኛውንም ሴት እንስሳ ቢገድሉ ደግሞ የዋጋውን እጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋል " በማለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በሌሎች ሀገራት የሌሉ ኢትዮጵያ ብቻ የምትታወቅባቸው ብርቅዬ እንስሳት እየታደኑ የሚሸጡ ከሆነ በአንድ ወቅት ህልውናቸው ሊጠፋ ስለሚችል ጭራሹንም መጠሪያ ማጣትን አያስከትልም ወይ? ከጠፉ ደግሞ የቱሪስት ፍሰት አይኖርምና ከሚገደሉ ይልቅ በቱሪስት የሚያስገኙት ገቢ አይሻልም ወይ? በሚል ለሚነሳው ስጋት ምላሽ እንዲሰጡም አቶ ፋንታዬን ጠይቀናቸዋል።

ምን መለሱ?

" ያልከው ስጋት ምናልባት ስፓርታዊ ሃንቲንግ ምንድን ነው? ብለው በትክክል ካለመረዳት የመጣ ነው። መስጋታቸው ምንም ሊደንቅ አይገባም፤ ግን ደግሞ ሳይንሱን ቢያውቁት ግልጽ ይሆንላቸዋል።

ሲቀጥል እንስሳቱ የሚታደኑት ፓርክ ላይ አይደለም። ይልቁንም ለእነርሱ ተብሎ የተከለለ የአደን ቀበሌ አለ፤ ከፓርኮቻችን ቢያንስ 5 ኪሎ ሜትር የራቀ ቦታ እንጂ ብሔራዊ ፓርኮች ውስጥ አደን አይፈቀድም። ነገር ግን ዓለም አቀፍ ህግ በሚፈቅደው መልኩ የአደን ቀበሌ ተብሎ ይቋቋልማል፤ እዚያ አደን ቀበሌ ላይ ነው ኮታ የሚሰጠው።

ኒያላ ብቻ ሳይሆን ወደ 54 እንስሳትን እናሳድናለን፤ አንድ ቱሪስት ደግሞ ኒያላ ብቻ ብሎ አይመጣም። ሌሎች እንስሳትን (የምኒልክ ድኩላ፣ ተራ ድኩላ፣ የቆላ አጋዘን...) አብሮ ይገዛል። ሁሉም በሳይንሳዊ መንገድ ተጠንተው ኮታ ተሰጥቷቸው ነው የሚታደኑት " ብለዋል።

በዚሁ አደንም ከፍተኛ ገቢ እንደሚገኝ፣ 85 በመቶው ገቢ እንስሳው ለታደነበት ክልል፣ 15 በመቶው ለፌደራል መንግስት እንደሚገባ፣ አደኑ በኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሶማሌና አፋር ክልሎች እንደሚከናወን፣ የታደኑትን እንስሳትን ትክክለኛ ቁጥር ለጊዜው ባያስታውሱም በዚህ ዓመት ወደ 177 ሚሊዮን ብር ገቢ እንደተገኘ ገልዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😡887586😭40🤔22💔22🙏10🕊9👏8🥰6😱5
" ሦስት 5Lሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት ፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል " - ባለንብረቶቹ

ትላንት (ረቡዕ ለሐሙስ) ከሌሊቱ 9 ሰዓት ገደማ ፓርክ ከተደረጉበት ሦስት 5L ሚኒባሶች እንደተወሰዱባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የገለጹ ባለንብረቶች ተሽከርካሪዎቹን ያየ ሁሉ እንዲጠቁማቸው በአጽንኦት ተማጽነዋል።

ባለንብረቶቹ " ሦስት 5L ሚኒባሶች ናቸው የተወሰዱት፤ ሦስት ሆነው ነበር ያደሩት አንዱ ጥበቃ አብሮ ጠፍቷል። ሁለቱ 'ተኝተን ነበር' አሉ። ከተቀጠረ ሦስት ቀናት የማይሞላው ጥበቃ ነው ከተሽከርካሪዎቹ ጋር አብሮ የጠፋው " ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።

" ጥበቃው የተቀጠረው በኤጀንሲ ነበር። ኤጄንሲው ተመሳጥሮ እንዳይሆን የሚል ጥርጣሬ አለን። ምክንያቱም ኤጀንሲው የተሟላ ዶክሜንት አልያዘም ጥቃውን ሲቀጥረው፤ ዋስትና አልያዘም 'መጣል' በሚል" ብለዋል።

አክለው፣ "ኮሚቴዎች ደግሞ 'አይቻልም' ብለው ሲመልሱ አማላጅ ፓሊስ ጠርቶ 'ፓሊሱ እኔ ኃላፊነቱን እወስዳለሁ፤ በሦስት ቀናት ያመጣል ይስራ' እንዳላቸው ነው ኮሚቴዎቹ የነገሩን። የኤጀንሲው ሰውም፣ ፓሊሱም፣ ሁለቱ ጥበቃዎችም ተይዘዋል" ነው ያሉት።

ሦስቱም ተሽከርካሪዎች ከአንድ ፓርኪንግ ከቆሙበት እንደተወሰዱ፣ የተወሰዱትም ቃሊቲ ቶታል ጨፌ ኮንዶሚኒየም እንደሆነ፣ አንዱ መኪና ኦሮ ኮድ 03 34021 መሆኑን ተናግረዋል።

ሌላኛው የጠፋው ተሽከርካሪ ኦሮ ኮድ 03 ኦሮ 41867 እንደሆነ፣ ከጠፉት ከሦስቱ አንዱ እንደተገኘ በዚህ ዘገባ ታርጋቸው የተገለጹት እንዳልተገኙ ገልጸው፣ ተሽከርካሪዎቹን ያየ በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እንዲጠቁማቸው ተማጽነዋል።

የባለንብረቶቹ ስልክ ቁጥሮች 0912049042፤ 0965206720
ናቸው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አዲስ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
 
@tikvahethiopia
1.36K😢244🙏81😱62💔62🤔43😭37🕊22🥰21😡13
“እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” - ባለስልጣኑ

➡️ከ2015 እስከ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም በሥራ ላይ የ142 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተጠቁሟል!


የአዲስ አበባ ከተማ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከ2015 እስከ 24/10/2017 ዓ/ም ድረስ በመዲናዋ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች 121 ወንዶች፣ 21 ሴቶች በድምሩ 142 ሰዎች በህንጻ ሥራ ላይ እያሉ በተለያዩ ምክንያቶች ህይወታቸው ማለፉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል፡፡

42 ወንዶችና 10 ሴቶች በድምሩ 52 በለሚኩራ፤ 15 ወንዶችና 2 ሴቶች በድምሩ 17 በንፋስ ስልክ፤ 15 ወንዶችና 2 ሴቶች በድምሩ 17 በቦሌ፤ 13 ወንዶችና አንዲት ሴት በድምሩ 14 ሰዎች በቂርቆስ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ በሌሎቹ ክፍለ ከተሞች ህወታቸው ማለፉን የባለስልጣኑ መረጃ በዝርዝር ያስረዳል፡፡

ባለስልጣኑ ህንፃች አሁን ያሉበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ “እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” ብሏል፡፡

ባለፉት አስር አመታት በአዲስ አበባ ሰማይ ጠቀስ ህንጻዎች በስፋት እየተገነቡ እንደሚገኙ፣ ለአብነትም በ2017 ዓ/ም በከተማዋ 11 ሺሕ 748 አዳዲስና 12 ሺሕ 322 ነባር ግንጻዎች ክትትል እንደተደረገባቸው፣ ግንባታዎቹ ከ581 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት እንዳላቸው የባለሥልጣኑ መረጃ ይገልጻል፡፡

በከተማዋ በግንባታ ሳይቶች ላይ በተደጋጋሚ የሚታዩ የአደጋ መንስኤዎች እና ስጋቶች ምንድን ናቸው?

-ከከፍታ ላይ መውደቅ
-የኤሌክትሪክ አደጋ
-የእቃ መውደቅ
-የግንባታ መዋቅር ችግር
-የሠራተኞች በቂ ስልጠና አለመውሰድ
-የግል ደህንነት መጠበበቂያ መሳሪያዎች ያለመጠቀም
-የቁጥጥር ችግር፣ የበጅት እጥረት
-ህግ የማስከበር ችግር ዋና ዋናዎቹ ናቸው ተብሏል፡፡

በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ “በአስር አመት አማካኝ የኢንዱስትሪው እድገት 10%"፣ “በቀጥታና በተዘዋዋሪ በየዓመቱ በአማካኝ የሚፈጠረው የሥራ እድል 1.2 ሚሊዮን” መሆኑን የጠቀሰው ባለስልጣኑ፣ “በሌላ በኩል ደግሞ ይህ ፈጣን ኢንዱስትሪው እድገት በሠራተኞች የሥራ ላይ ደንነነት ተመሳሳይ ለውጥና መሻሻል እየታየበት አይደለም” ብሏል፡፡

“አልሚዎች ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ወጭ ለመጨረስ በሚያደርጉት ጥረት የሥራ ላይ ደህንነት ትኩረት በመሆኑ አደጋና ጉዳት እየጨመረ ይገኛል” ብሎ፣ የኮንስትራክሽን እድገት በአጭር ጊዜና በዝቅተኛ ዋጋ ግንባታዎችን ለመጨረስ የሥራ ላይ ደህንነትን አቀናጅቶ መተግበር እንደሚገባ አሳስቧል።

(ዝርዝር መረጃ ከላይ የተያያዘ ሲሆን፣ ተጣለ የተባለውን ቅጣት የተመለከተ ተጨማሪ አለን)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
510😭71👏13🕊11😡9😱6😢5🙏4🤔3💔3🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
“እስከ ወረዳ ድረስ ቡድን ተዋቅሮ ችግር ያለባቸው ግንባታዎች ተለይተዋል፡፡ ከተለዩት 2681ግንባታዎች 1157 ብቻ ናቸው ትንሹን መስፈርት የሚያሟሉት” - ባለስልጣኑ ➡️ከ2015 እስከ ሰኔ 24/2017 ዓ/ም በሥራ ላይ የ142 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተጠቁሟል! የአዲስ አበባ ከተማ አበባ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ከ2015 እስከ 24/10/2017 ዓ/ም ድረስ በመዲናዋ በ11ዱም…
ያለፈቃድ የግንባታ ዲዛይን ማስፋፊያ ለሚያደርጉ አካላት በየእርከኑ የ100 ሺሕ ብር ቅጣት ተጣለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ባደረገው የቅጣት ማሻሻያ በሕንፃ ግንባታ ህግጋት መሰረት በተጣለው የህንፃ ደህንነትና ተያያዥ ቅጣት በተለያዩ ተግባራት ከ15 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን ገልጿል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው የባለስልጣኑ መረጃ እንዲሚያስረዳው፥ የማስፋፊያ ሥራ የዲዛይን ማሻሻያን ስለሚፈልግ፣ ያልተፈቀደ ግንባታ የዲዛይን ጥራት ስለሚጎድለው የመደርመስ አደጋ ስለሚያስከትል ያለፈቃድ የማስፋፋት ሥራ ማከናወን (በየእርከኑ) 100 ሺሕ ብር ያስቀጣል።

እንዲሁም፣ ጥራት ያለው ስካፎልዲንግ፣ ሾርኒንግና መሰል መሳሪያዎችን አለመጠቀም ለአደጋ የሚያጋልጥ መሆኑን የጠቀሰው ባለስልጣኑ፣ በግንባታ ወቅት እነዚህን መስፈርቶች ለማያሟሉ አካላት (በእርከን) 50 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን አመልክቷል።

ቅጣቱ "በየእርከኑ" ሲባል ምን ማለት እንደሆነ ባለስልጣኑ ሲያስረዳም፣ "ለምሳሌ አንድ G+10 ህንጻ 26 የክትትል እርከኖች ይኖሩታል፤ 26*50,000=1,300,000 ይሆናል" ሲልም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ያለተቆጣጣሪ ማሰራት ለአደጋ አጋላጭ በመሆኑ የግንባታ ስራዎችን ያለተቆጣጣሪ የሚያሰሩ አካላት (በየእርከኑ) 25 ሺሕ ብር እንደሚቀጡም ተጠቁሟል።

ስቶር፣ ልብስ መሸጫ፣ መመገቢያና ሌሎች የቅድመ ግንባታ መስፈርቶችን ሳያዘጋጁ ሥራ ለሚጀምሩ አካላት የ15 ሺሕ ብር፤ በሚሰጥ የማስታወቂያ ትዕዛዝ መሰረት ተረፈ ምርትን በወቅቱ ለማያነሱ 15 ሺሕ ብር ቅጣት መጣሉን የደረሰን የባለስልጣኑ መረጃ ያሳያል።

ሕጋዊ ተጠያቂነትን በተመለከተ የማማከር ኃላፊነትን በአግበባቡ አለመወጣት ከ5 እስከ 15 ዓመታት የእስራትና ከ30 እስከ 50 ሺሕ የገንዘብ፤ ደረጃውን ያልጠበቀ ግንባታ ማከናወን ከ5 እስከ 15 ዓመታት የእስራትና ከ50 እስከ 100 ሺሕ የገንዘብ ቅጣቶች መጣላቸው ተመልክቷል፡፡

እንዲሁም፣ ግባታውን በህዝብ ደህንነት አደጋ በሚጥል ሁኔታ ያከናወነ ከ5 እስከ 10 ዓመታት የእስራት እና ከ20 እስከ 50 ሺሕ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት የተገለጸ ሲሆን፣ ጥፈተኛ ሆኖ የተገኘ አማካሪ/ሥራ ተቋራጭ ከ15 ዓመት እስከ ከፍተኛ የእስር ጊዜው ፈቃዱ ይታገዳል ተብሏል፡፡

(የቀድሞው እና የተሻሻለውን ቅጣት፤ የመፍትሄ ሀሳቦችን የያዘው የባለስልጣኑ መረጃ ከላይ ተያይዟል)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
634😡114👏44🙏14😢13🕊12🤔10🥰9💔1😭1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ጥቆማ
(ለሚመለከተው አካል - አዲስ አበባ)

" በሰውና መኪና ላይ ወድቆ ጉዳት እንዳይደርስ መፍትሄ ይፈለግለት ! "

" ይህ በቪድዮው ላይ የምትመለከቱት የመብራት ኮንክሪት ፖል ታቹ ተበልቶ አልቆ ለመውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከጎኑ ትራንስፎርመርንም አለ።

ቦታው ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር ነው ሲሆን ብዙ ሰው የሚመላለስበት መኪናም የሚንቀሳቀስበት ነው።

ፖሉ ወድቆ በሰው እና በመኪና ጉዳት ሳያደርስ በፊት መፍትሄ ይፈለግለት። ወቅቱም ክረምት በመሆኑ ዝናቡና ንፋሱ ኃይለኛነውና ፈጣን መፍትሄ ይፈለግለት። " - ዮሴፍ (ከአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
752🙏235👏46😭41🕊20😱16🤔4😡1
TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል። አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር  እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና…
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው  መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚያስገነባው ግዙፉ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 2,500 አባወራዎች እንደሚነሱ መገለጹ ይታወሳል።

3,500 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈው አዲሱ የአየር ማረፊያ ስራ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አየር መንገዱ አሳውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአሁኑ ሰአት ለ2,500 አባውራዎች መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን እና በመስከረም ወር ለማስረከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ስለ አዲሱ አየር መንገድ እና በሃገር ውስጥ ያሉ መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰራ ስላለው ስራ በዝርዝር ምን አሉ ?

" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው እንደተጠናቀቀ ወደ ተሰራላቸው ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ይዘዋወራሉ ስራቸውንም በአዲስ መልክ ይጀምራሉ።

ቦታው ሲለቀቅልን የግንባታ ስራ እንጀምራለን የአየር መንገዱ ዲዛይንም በብዙ አድቫንስ አድርጓል እየቆራረጥን በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው የመጀመሪያውን ዙር ስራ ህዳር ውስጥ ለመጀመር እቅድ ይዘናል።

የሃገር ውስጥ በረራን ለማስፋት እና የአገልግሎት ጥራቱን ከፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ጥቂት አመታት በርካታ ስራ ሲሰራ ቆይቷል።

ከስራዎቹ  መሃል ዛሬ ላይ ያሉን የአውሮፕላን ጣቢያዎች ማሻሻል ነው የአውሮፕላን መንደርደሪያው ጥሩ ካልሆነ እሱን በአዲስ መልክ መስራት።

መንገደኞች የሚስተናገዱባቸው ተርሚናሎችም አንዳንዶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና አሮጌ ፣ ወይም በቆርቆሮ የተሰሩ ነበሩ እነሱን እያፈረስን በዘመናዊ መንገድ እየሰራን ነው ሁሉንም በአንድ ጊዜ ስለማይቻል በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው።

ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ብቻ እንደ ጎዴ እና ጂንካ ያሉ 3 ተርሚናሎችን ሰርተን ስራ ላይ አውለናል።

አገልግሎቱን ለማስፋትም አዳዲስ ኤርፖርቶችን በመስራት ላይ እንገኛለን በአሁኑ ሰአት ስድስት ተርሚናሎች እየተሰሩ ይገኛሉ አንዳንዶቹ ለምረቃ ደርሰዋል።

ለምሳሌ ፦ ያቤሎ መንደርደሪያው አልቋል በሁለት ወር ውስጥ በረራ እምጀምራለን እሱ 23ኛው የሃገር ውስጥ መዳረሻችን ይሆናል ማለት ነው።

ነገሌ ቦረና፣ መቱ ፣ሚዛን አማን እና ደብረ ማርቆስም በመገንባት ላይ ናቸው በሚመጡት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
1.57K😡172👏98😭38🙏35🥰34🕊22🤔17😢13💔4
#ዙሪያ

ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ ያስችላቸዋል የተባለ ሲስተም ይፋ ተደርጓል።

ኢትዮ ቴሌኮም፣ ከዳሽን ባንክ እና ኤታ ሶሉሽንስ በአጋርነት በጋራ በመሆን የቀረበው "ዙሪያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲስተም  በአስመጪና ላኪ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና ችርቻሮ ንግድ ዘርፍ ለተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን ያግዛቸዋል ተብሏል።

"ዙሪያ" የኢ.አር.ፒ (ERP)፣ የፒ.ኦ.ኤስ (POS) እና ካሽ ሬጂስተር (Cash Register) አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለመስጠት የሚያስችል የቢዝነስ አውቶሜሽ ሶሉሽን የያዘ ሲስተም ነው፡፡

መተግበሪያው የተለያየ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ የሚያስችል ነው።

"ዙሪያ" ሁሉንም የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ካርዶች መቀበል እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና እንደተሰጠው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ተገልጿል።

ይህ ሲስተም የሂሳብ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ነጋዴዎች የሚያንቀሳቅሱትን ሃብት ለማስተዳደር እና ማንኛውንም የክፍያ መረጃዎች በአንድ ያካተተ ደረሰኝ ለማግኘት ያስችላል ነው የተባለው፡፡

አገልግሎቱን ለማቅረብ ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌክላውድ (TeleCloud) መሠረተ ልማት በማቅረብ የተሳተፈ ሲሆን ለዚህ አገልግሎት የሚውለውን ማሽን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በማመቻቸት ዳሽን ባንክ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተነግሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
798👏50😡48🕊37😭20🙏13🤔12🥰9😢7😱6
TIKVAH-ETHIOPIA
" የግፍ አገዳደል ነው የተፈጸመው ፤ የሟቹን ወንድም ቤትም ታጣቂዎቹ አቃጥለውታል ፤ የአካባቢው ነዋሪም ወደ አጎራባች ቦታዎች ተፈናቅሏል " - የሟች የቅርብ ሰው በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የሰባት ልጆች አባት ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ በ "ሸኔ" በታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ግድያው አሰቃቂ…
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ሰዎች ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " - የወረዳው ቤተ ክህነት

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ የ"ሸኔ" ታጣቂ ቡድን በአንድ ቤተሰብ አባላት የግድያ እና እገታ ጥቃት መፈጸሙን የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ቤተ ክህነቱ የሆነውን ሲያስረዳ፣ " ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ትላንት 3 ሰዓት ከሩብ ላይ ነው ጥቃቱ የተፈጸመው ዛሬ የሟች አባትና ልጅ ቀብር ተፈጽሟል። ካህንና ምዕመን ወንድማማቾች ታግተው ተወስደዋል፤ የተወሰዱትም የሟች ወንድም ናቸው " ሲል ተናግሯል።

" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " ብሎ፣ ታጋች ካህን የሰኮራ ኪዳነ ምህረት አገልጋይ መሆናቸውን ገልጿል።

ቤተ ክህነቱ፣ " ህዝቡ ሁሌም በልቅሶ ነው፤ ሁሌ መገደል ነው ማን ይደርስለታል " ሲልም በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚፈጸምን ጥቃት አስከፊነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።

" ታጣቂ ቡድኑ 3 ሰዓት ይመጣል፤ ምሽት 11 ሰዓት ይመለሳል፤ በሌሊትም የፈለገውን ይፈጸሰማል" ብሎ " መንግስት የህዝቡ ድምጽ እንዲሰማና ህዝቡን እንዲጠብቅ አሳስቧል።

" መንግስት ቢደርስ ጥሩ ነው በወረዳው ከ2014 ዓ/ም ጀሞሮ ያለማቋረጥ ነው ግድያ እየተፈጸመ ያለው። ህዝቡ እየተፈናቀለ ነው፤ ተፈናቅሎም የሚገባበት የለም። ይህ የሆነው መንግስት ሃይ ባለማለቱ ነው " ሲልም ወቅሷል።

እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ በበዞኑ ሶኮራ ቀበሌ ሐምሌ 4/2017 ዓ/ም አባትና ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ገልጾ፣ " የሟች ወንድሞችና የአጥቢያው  አገልጋይ ካህን ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወገኔ ጌታነህ ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን፣ የደረሱበት አልታወቀም " ሲል አስታውቋል።

" ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል በዞኑ በሁሉም አካባቢ በሚባል ደረጃ እየተንቀሳቀሰ ከፍተኛ ሰቆቃ የሚፈጽም ሲሆን፣ ከፌዴራሉም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በኩል ነገሩን ከማድበስበስ ያለፈ እስካሁን ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስዱ አልታየም። ይህም ለሌላ ጥርጣሬ የሚጋብዝ ነው " ብሏል።

" ፓርቲያችን ግድያውን በጽኑ ያወግዛል፤ ታፍነው የተወሰዱ ካህንና ወንድማቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ይጠይቃል " ሲል ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😡652424😭259🕊28😢26💔23🙏19👏7🤔6🥰2😱2
በአዲስ አበባ በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ በዲኤስቲቪ ሲመለከቱ የነበሩ ደጋፊዎች በነበሩበት ሆቴል በተፈጠረ ግጭት የሰው ህይወት አለፈ።

ትላንት ምሽት በአሜርካ ኒው ጀርሲ በሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም በፒኤስጂ እና ቼልሲ መካከል የተደረገውን የዓለም የክለቦች ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ " ለቡ " አካባቢ በሚገኝ ሆቴል ውስጥ በዲኤስቲቪ እየተመለከቱ በነበሩ ተመልካቾች መካከል በተፈጠረ ግጭት የአንድ ለጋ ወጣት ህይወት አልፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በለቡ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በመገኘት የሟቹ ወጣት የቀብር ስነስርዓት ሲፈፀም ተመልክቷል።

በቀብር ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ የሟቹ ወዳጆች ፣ ጓደኞች " አሟሟቱ እጅግ የሚያሳዝን ነው " ያሉ ሲሆን " ግለሰቡም ተይዟል " ብለዋል።

" እስከ ምሽት 3:00 ሰአት ድረስ ከቤተሰቦቹ ጋር ካመሸ በኋላ ከጓደኞቼ ጋር ትንሽ ልዝናና ብሎ ሆቴሉ እንደገባ ነው ክስተቱ የተፈጠረው " ሲሉ ተናግረዋል።

በአሟሟቱ ቤተሰቦቹ እጅግ ከፍተኛ ሀዘን ውስጥ እንደሚገኙ ለመመልከት ችለናል።

" ወጣቱ ከኳስ ስሜታዊነት መቆጠብ ወይም የእግር ኳስ ጨዎታዎችን ተሰባስቦ ከማየት መቆጠብ አለበት ካልሆነ ግን የቤተሰብን ሀዘን ማብዛት ነው " ሲሉ ያነጋገርናቸው ለቀስተኞች ተናግረዋል።

" ወጣቶች እባካችሁ ለቤተሰቦቻችሁ ሀዘን አታብዙ፣ ሁሉን በማስተዋል አድርጉ፣ ማታ ማታ አታምሹ፣ በአጭሩ እየተቀጫችሁ ሃዘናችንን አታብዙት " የሚሉ እና ሌሎች ልብ የሚነኩ ሃሳቦች ሲሰነዘሩ እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ በስፍራው ተገኝቶ ተመልክቷል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በስልክ ቃላቸውን የሰጡ አንድ እናት ሟቹን ወጣት እንደሚያውቁት ገና በ22 ዓመቱ በተፈጠረው ፀብ እንደተቀጠፈ ገልጸዋል።

" በውጭ ኳስ ምክንያት የለጋ ወጣት ህይወት መጥፋቱ እጅግ ያሳዝናል። ሁሉም ወጣቱ ከስሜታዊነት መራቅ አለበት፣ የሚመለከታቸው አካላትም እንዲህ ያለው ነገር እንዳይፈጠር የራሳቸውን ድርሻ መወጣት አለባቸው " ሲሉ እናታዊ መልዕክታቸውን በሀዘን ስሜት አስተላልፈዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭1.38K761😡113😢70💔57🤔49🕊43🙏21😱18🥰13👏4
TIKVAH-ETHIOPIA
" መንግስት የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የመዝጋትም ሆነ የማዳከም ፍላጎት የለውም " - የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተዋናዮች በዳግመ ምዝገባው ዙርያ ላቀረቡት ቅሬታ ምላሽ ሰጥቷል፡፡ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ መንግስት ተቋማቱን የማጥፋት እቅድ…
" የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲያሟሉዋቸው የተቀመጡት መስፈርቶች በጣም ዝቅተኛ ናቸው ! "  - ባለስልጣኑ

" የግል ትምህርት ተቋማትን ስጋት ላይ የጣለው አዲሱ መመሪያ ምን ይላል " በሚለው ከዚህ ቀደም በቀረበው ዘገባችን፣ የዘርፉ ተዋናዮችን ቅሬታዎች አቅርበናል፡፡

የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ደግሞ ለቅሬታዎቹ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በትምህርት ተቋማቱ የዳግመ ምዝገባና የመስክ ምልከታው የሚታዩት ዋና ዋና የሚባሉት መስፈርቶች ናቸው ብለዋል፡፡ የትምህርት ተቋማቱ፣ ትውልድን ለማስተማር በትንሹ ምን ማሟላት አለባቸው የሚለውን ነው የምናየው በማለትም ተናግረዋል፡፡

አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን መለሱ ?

" አንድ የትምህርት ተቋም ስናስብ የራሱ የሆነ ድባብ ሊኖረው ይገባል፡፡ አንዳንዶቹ ተቋማት የሆነ ህንፃ ላይ አንድና ሁለት ወለል ብቻ ተከራይተው ከቡቲኩና ከካፌው ጋር እየተጋፉ ነው የሚሰሩት፡፡ ይህ ትክክል አይደለም፡፡ የኮሌጅነት ቅርፅ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ መስፈርቶች መቀመጥ አለባቸው፡፡ ግን ደግሞ የተቀመጡትን ሁሉንም መስፈርቶች በሙሉ እንተግብር አላልንም፡፡ በጣም መሰረታዊ የሚባሉትን ብቻ እንዲያሟሉ ነው እያደረግን ያለነው፡፡ በጣም በዝቅተኛ መስፈርት ነው እየተመዘኑ ያሉት፡፡ እነዚህን ዝቅተኛ መስፈርቶችስ ምን ያህሎቹ ተቋማት ያሟላሉ የሚለውን ደግሞ ሪፖርቱ ሲለቀቅ የምናየው ይሆናል፡፡   

መስፈርቶቹ ምንድናቸው ካልን አንደኛው የመማሪያ ህንፃን የሚመለከት ነው፡፡ ከአምስት ፕሮግራሞች በላይ ያላቸው ተቋማት የራሳቸው ግቢና ህንፃ እንዲኖራቸው ተደንግጓል፡፡ ተከራይተውም ቢሆን፣ የራሳቸው ግቢና ህንፃ ይኑራቸው፣ ከሌሎች የንግድ ስራዎች ጋር ሊዳበሉ አይገባም ነው፣ ይህ አንድ መሰረታዊ መስፈርት ነው፡፡

ግን ደግሞ በአብዛኞቹ ኮሌጆች ዘንድ መስፈርቶቹን ለማሟላት ስለሚቸገሩ ለድርድር እያቀረብናቸው ነው፡፡ ለምሳሌ ከአምስት ፕሮግራሞች በታች የሚሰጡ ጀማሪ ባለሀብቶች፣ የራሳቸው ህንፃና ግቢ እንዲኖራቸው አናስገድድም፡፡ እነሱ ከሌሎች ቢዝነሶች ጋር ተዳብለው መስራት ይችላሉ ብለናል፣ እስኪጠናከሩ ድረስ፡፡ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ተረድተን ነው በዚህ ደረጃ መስፈርቱን አውርደን እየሰራን ያለነው፡፡ መስፈርቶቹ በምንም መልኩ ሊሟሉና ሊተገበሩ አይችሉም የሚባሉ አይደሉም፡፡ 

ሁለተኛው መስፈርት ለማስያዣነት የሚያስቀምጡት ገንዘብ ነው፡፡ ከዚህ ቀደም በነበረው አሰራር፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ መቼ ገብተው መቼ እንደሚወጡ አይታወቅም ነበር፡፡ በተለይም አወጣጣቸው ስርዓት ስላልነበረው፣ መቼ እንደወጡ እንኳን ማወቅ አይቻልም ነበር፡፡ ይህን ስርዓት ለማስያዝ ነው 500 ሺህ ብር ማስያዣ እንዲያስቀምጡ የጠደነገገው፡፡ ከእንግዲህ፣ ማንኛውም ተቋም ከገበያው ሲወጣ፣ አወጣጡ ስርዓት ያለው ይሆናል፣ የጠራ መረጃም ይኖረናል ማለት ነው፡፡

ሶስተኛው መስፈርት የሰው ሀይሉን የሚመለከት ነው፡፡ ከበፊቱ መመሪያ ብዙም የተጨመረ ነገር የለውም፡፡ አንድ ነገር ነው ብቻ ነው ያሻሻልነው፡፡ የማስተርስ ተማሪ ፒኤችዲ ዲግሪ በሌለው ረዳት ፕሮፌሰር መሰልጠን የለበትም የሚል ነው፡፡ የአስተማሪው የትምህርት ደረጃ ከሚያሰለጥነው የትምህርት ደረጃ አንድ እርከን ከፍ ይበል ነው፡፡ ለምሳሌ የዲግሪ ተማሪ ማስተርስ ዲግሪ በያዘ መምህር፣ የማስተርስ ዲግሪ ተማሪ ደግሞ የዶክትሬት/ፒኤችዲ ዲግሪ ባለው መምህር መሰልጠን አለባቸው፡፡ አሁን ግን ፒኤችዲ ዲግሪ ሳይኖራቸው ረዳት ፕሮፌሰር የሚል ማዕረግ ያላቸው አስተማሪዎች ናቸው ከነሱ ጋር አቻ የሆነን የማስተርስ ዲግሪ ስልጠና የሚሰጡት፡፡ ማስተርን በማስተር ማለት ነው፡፡ ይህ ሊሆን አይችልም ብለናል በመስፈርቱ፡፡

ከዚያ ውጭ፣ በግል ኮሌጆች ድጋፍ ሰጪ ሰራተኛውም፣ የአስተዳደር ሐላፊዎችም ፒኤችዲ ዲግሪ ይኑራቸው አልተባለም፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ ዲኖቻቸው/ የተቋማቱ ሐላፊዎች እንኳን ፒኤችዲ ከሌላቸው ብለን ጥብቅ ቁጥጥር አናደርግም፣ እውነት ለመናገር፡፡ ትኩረታችን አስተማሪዎቹና ትምህርቱ ላይ ነው፡፡ በሒደት ደግሞ ወደ ስታንዳርዱ እናስገባቸዋለን የሚል እሳቤ ነው ያለን፡፡

አራተኛው መስፈርት መምህራንን መዋዋስ በተመለከተ ነው፡፡ ሁሉንም ትምህርቶች በትርፍ ሰዓት/ፓርታይም መምህር አታስተምሩ ነው እንጂ ሁሉም አስተማሪዎቻችሁ የሙሉ ሰዓት ተቀጣሪዎች/ፉልታይም መምህራን ይሁኑ አላልንም፡፡ ትምህርት ብዙ ማንበብ፣ መጣርና ማማከር የሚያስፈልገው፣ የምርምር ስራ የሚያስፈልገው ስራ ነው፡፡ ይህንን ሁሉ ስራ የሆነች ሰዓት ላይ ብቻ አስተምሮ በሚሔድ በትርፍ ሰዓት ብቻ በሚሰራ መምህር ልታስኬደው አትችልም፡፡ መምህሩ ሶስት አራት ቦታ ላይ ከተጠመደ እንዴት ነው የምርምር ስራውን የሚሰራውና የሚያሰራው፡፡ የተወሰኑ የራሳችሁ ቋሚ መምህራን ይኑሩዋችሁ፣ ሌሎችን ደግሞ በፓርታይም መምህራን መሸፈን ትችላላችሁ ነው ያልነው፡፡ 

አምስተኛው መስፈርት፣ አንድ ተቋም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ቢያንስ 25 በመቶ ካላሳለፈ ይዘጋል የሚል ነው፡፡ አንድ ተቋም አራት አመት ካስተማራቸው 100 ተማሪዎች ቢያንስ 25ቱን ማሳለፍ ካልቻለ መዘጋት ነው ያለበት፡፡ ተማሪዎችን ካላሳለፈ እኮ እያስተማረ አይደለም፣ የሀገር ሀብት እያባከነ ነው ያለው፡፡

አራት አመት ሙሉ ካስተማራቸው ተማሪዎች 75 ከመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ከወደቁ፣ ያንን ሁሉ ሀብት ያባከነው ለምንም ነው ማለት ነው፡፡ ያ ተቋም ለምን ይቀጥላል፡፡እንዳይዘጋ ከፈለገ በደንብ አሰልጥኖ ተማሪዎቹን አብቅቶ የመውጫ ፈተናን ማሳለፍ ነው ያለበት፡፡ እንደገና ደግሞ 25 በመቶ ካላሳለፈ የሚባለው በኮሌጅ ደረጃ ሳይሆን በፕሮግራም ደረጃ ነው፡፡ ለምሳሌ 25 በመቶ ያላሳለፈው የአካውንቲን ትምህርት ከሆነ፣ ያ ትምህርት ነው የሚዘጋው እንጂ ተቋሙ አይደለም የሚዘጋው፡፡

ይህንን አሰራር ደግሞ በአንዴ ተግብሩ አላልንም፡፡ የእፎይታ ጊዜ ሰጥተናቸዋል፡፡ ይህ አሰራር የሚተገበረው መመሪያው በፀደቀበት በ 2015 ዓ.ም ትምህርት በጀመሩ ተማሪዎች ላይ ነው፡፡ ያኔ አንደኛ አመት የነበሩ ተማሪዎች በ 2019 ዓ.ም የሚመረቁ ናቸው፣ በነዚህ ላይ ህጉ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ድንገት ተነስተን ዘንድሮ ቢያንስ 25 በመቶ አስመርቅ አላልንም፡፡ ለ 2019 ዓ.ም ካስተማርካቸው ተማሪዎች 25 በመቶውን ለማሳለፍ ተዘጋጅ ብሎ የቤት ስራ መስጠት የተጋነነ አይደለም፡፡ "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
1.49K👏174🕊34😡34🙏21🤔16😭14😢13🥰7
" እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው " - ሰመራ ዩኒቨርሲቲ

በአፋር ክልል የኤርታሌ እሳተ ገሞራ እየፈነዳ መሆኑን ሰመራ ዩኒቨርሲቲና አንድ የዘርፉ ባለሙያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የጂዖሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ኖራ ያኒሚኦ በሰጡን ገለጻ፣ እሳተ ገሞራው መፈንዳቱን ከአካባቢው ማህበረሰብ ማረጋገጣቸውን ገልጸው፣ ለነዋሪዎቹ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።

" እሳተ ገሞራው እንደፈነዳ መረጃው ደርሶናል፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ በጣም ከፍተኛ አቧራ እየወጣ ነው " ያሉት ተመራማሪው፣ " በአካባቢው በሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ቢያንስ እዛ አካባቢ ያለውን ህዝብ ማራቅ የሚቻልበት መንገድ ቢፈጠር ጥሩ ነው " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" ኤርታሌ በቀን በጣም ብዙ ሰው የሚጎበኘው ቦታ ስለሆነ ወደዚያ የሚሄዱ ጎብኝዎች ጥንቃቄ ያድርጉ፣ ምክንያቱም የሚፈጠረው ነገር አይታወቅም " ሲሉም ተናግረዋል።

" ከዚህ በፊት ኤርታሌ ላይ እንደዚህ አይነት ነገር የተለመደ አልነበረም፣ እሳት ገሞራ ከመፍሰስ ውጭ፣ አሁን ግን ብናኞቹ ወደሰማይ እየወጡ ስለሆነ ጉዳትም ሊያስከትል ይችላል " ያሉት አቶ ኖራ፣ ክስተቱ እስከሚረጋጋ ድረስ ወደ አካባቢው ቀርበው ፎቶ የሚያነሱ ሰዎች እየተስተዋሉ በመሆኑ ከዚህ ተግባር እንዲታቀቡ አሳስበዋል።

አክለው፣ " አንድ ልጅ በጣም ተጠባብሶ ፎቶ እያነሳ ነበር " ሲሉ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው አንድ የዘርፉ ባለሙያ በበኩላቸው፣ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታው እንደተከሰተ ገልጸው፣ ጉዳዩን ይበልጥ ለማጣራት በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ባለሙያዎች ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነ፣ መረጃውን አጣርተውም ተጨማሪ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ነግረውናል።

ግን እሳተ ገሞራው ተከስቷል መባሉ ትክክል ነው ? ስንል  ላቀረብንላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽም "እውነት ነው። እየፈነዳ እንደሆነ ሰምቻለሁ፣ ፎቶግራፎችም ደርሰውኛል " ብለዋል።

" ዛሬ ምሳ ሰዓት አካባቢ እንደተከሰተ ነግረውኛል፤ ከአፋር ክልልም ደውየ አጣርቻለሁ " ብለው፣ " የሳተላይት መረጃዎችን እያጠናከርን ነው " ሲሉም ተናግረል።

በአካባቢው ላለፉት በርካታ ዓመታት ተደጋጋሚ የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ያስተናገደ ሲሆን፣ በተለይም ከ2017 ዓ/ም ጀምሮ ከፍተኛ ፍንዳታዎችን እንደታዩ፣ የመሬት መንቀጥቀጥ በስፋት እንደተከሰተ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
1.53K😱211🙏128🕊87😭59😢33💔31🤔30👏15🥰10😡9
TIKVAH-ETHIOPIA
" ጦርነት ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል !! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በነበረው የህ/ተ/ም/ቤት ጉባኤን አንድ አባል " በትግራይ ክልል ዳግም ጦርንት እንዳይነሳ ስጋት አለ " በማለት በክልሉ ስላለው አሁናዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራርያ እና ምላሽ ጠይቀዋል። " ህወሓት ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ እያደረገ ነው "  በማለት " ከሰላም…
#Tigray

ከሁሉም የሃይማኖት የቋማት የተወጣጡ እና በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተመሩ አባቶች መቐለ ከተማ ይገኛሉ።

የኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባውን ከሁለት ሳምንት በፊት ባካሄደበት ወቅት የተገኙት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ የሚያደርጉ አካላት ስለመኖራቸው ያመላከተ መላሽ መስጠታቸው ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ለተነሳላቸው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ በፌደራሉ መንግስት እና ማንነታቸውን ባልጠቀሷቸው በክልሉ የሚንቀሳቀሱ አካላት መካከል መቃቃር ስለመኖሩ አመላካች ሆኗል።

ለጥያቄው በሰጡት ምላሽም " የሁሉም እምነት አባቶች እዚህ ተወካዮች አላችሁ፣ ሌላ ምንም ስራ የላችሁም በፍጥነት ትግራይ ወደ ግጭት፣ ወደ ጦርነት እንዳይገባ ስራችሁን አሁን ጀምሩ፣ ከተጀመረ ወዲያ ብትናገሩ ዋጋ የለውም " ብለው ነበር።

" ባለሃብቶች፣ ምሁራን፣ ኤምባሲዎች ውጊያ እንዳይጀመር አሁን ሚናችሁን ተወጡ ምክንያቱም ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል " ማለታቸውም የሚታወስ ነው።

የጠቅላይ ሚኒስትሩን መልእክት ተከትሎ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በማግስቱ ለአስቸኳይ ስብሰባ ተቀመጦ እንደነበር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

በወቅቱ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ፓስተር ይታገሱ ሃይለ ሚካኤል ተቋሙ እያደረገ ስላለው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል " በቅርብ ጊዜ የሚደረጉ ነገሮች እንደሚኖሩ ተስፋ እናደርጋለን አሁን በውይይት ደረጃ ላይ ነው ያሉት ምን ይደረግ፣ እንዴት እናድርግ ውጤታማ የምንሆነው እንዴት ነው በሚለው ላይ መክረዋል በቅርብ ጊዜ ተግባራዊ የሆነ እንቅስቃሴ ውስጥ ይገባሉ " ብለው ነበር።

የስብሰባው አላማም የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልእክት ነገሩን በአጽንዖት መያዝ እንደሚያስፈልግ ጠቋሚ በመሆኑ መሆኑን ፓስተር ይታገሱ አስታውቀዋል።

መደረግ ባለባቸው ጉዳዮች ላይ ተከታታይ ውይይት ያደረጉት አባቶች በዛሬው ዕለት ወደ መቀሌ አቅንተዋል።

በመቐለ የሚገኙት አባቶች በምን በምን ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ተጨማሪ መረጃ ከተቋሙ እንዳገኘን የምናጋራቹ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

ፎቶ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia
656🕊147😡59🤔25🙏23😭11👏6😢4😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
" የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲያሟሉዋቸው የተቀመጡት መስፈርቶች በጣም ዝቅተኛ ናቸው ! "  - ባለስልጣኑ " የግል ትምህርት ተቋማትን ስጋት ላይ የጣለው አዲሱ መመሪያ ምን ይላል " በሚለው ከዚህ ቀደም በቀረበው ዘገባችን፣ የዘርፉ ተዋናዮችን ቅሬታዎች አቅርበናል፡፡ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ደግሞ ለቅሬታዎቹ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት…
በ2018 ዓ.ም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀመር ታውቋል።

የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን፣ በመጪው አመት 2018 ዓ.ም በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የጥራት ቁጥጥር እንደሚጀምር አስታወቀ፡፡

የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ውብሸት ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃለመጠይቅ፣ በአሁን ወቅት በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እየተካወነ ያለው ዳግም ምዝገባና ምዘና ስራ ሲጠናቀቅ ይኸው እንቅስቃሴ በመንግስት ኮሌጆች፣ የማሰልጠኛ ተቋማትና ዩኒቨርሲቲዎች ላይም በቀጣዩ አመት እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

አቶ ውብሸት ታደለ በዝርዝር ምን አሉ ?

" አሁን እየተከናወነ ያለውን የመጀመሪያው ዙር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ምዝገባና ግምገማ እንደጨረስን፣ በሁለተኛውና በሶስተኛው ዙር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን እንመዘግባለን፣ እንገመግማለን፡፡ በፌደራልና በክልሎች የተከፈቱ ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማት አሉ፡፡ መጀመሪያ የምናየው እነሱን ነው፡፡ ቀጥለን ደግሞ ሁሉንም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን እናያለን፡፡

እስካሁን የግል ተቋማት ላይ ያተኮርነው፣ እዚህ ዘርፍ ላይ የነበረው ችግር ሰፊ ስለሆነ ነው፡፡ ያለንን የሰው ሀይልና ሀብት ወደዚህ ዘርፍ በማዞር ቅድሚያ ሰጥተናል፡፡ ሁሉንም አንድ ላይ ማየት አንችልም፡፡ አሁን የግሎቹን ተቋማት ካጠናቀቅን በኋላ፣ ወደ መንግስት ትምህርት ተቋማት ግምገማ እንገባለን፡፡

የመንግስት የትምህርት ተቋማት በመሰረተልማት በኩል ችግር የለባቸውም፡፡ የራሳቸው ህንፃና ግቢ አላቸው፡፡ ስለዚህ እነሱ ጋ ትኩረት የምናደርገው ጥራት ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ፕሮግራሞቹ/ትምህርቱ በበቂ መምህራንና አኳሀን መሰጠቱን እናያለን፡፡ አካዳሚያዊ የድርጊት መርሀግብራቸው ትክክል መሆኑን እንፈትሻለን፡፡

የተገቢነትና አስፈላጊነት ጥያቄ የሚነሳባቸው፣ ዝም ብለው ያለ በቂ ጥናት የሚከፈቱ ፕሮግራሞች አሉ፡፡ የትምህርት ግብአት እና የላቦራቶሪ ቁሳቁሶች፣ እንዲሁም የዳታ ማዕከላቸው ይታያል፡፡ ለተማሪዎችና ለአስተማሪዎች የሚቀርቡት አገልግሎቶች ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው ወይ የሚለውን እናያለን፡፡

ቀደም ብለው የተቋቋሙት ነባሮቹ ዩኒቨርሲቲዎች የዚህ አይነት ችግር ላይኖርባቸው ይችላል፡፡ አዳዲሶቹ ዩኒቨርሲቲዎች ግን በነዚህ መስፈርቶች በኩል ክፍተት ይኖሩባቸዋል፡፡

በአጠቃላይ ግን ጥራትን እናምጣ ካልን፣ ሁሉንም የመንግስት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎችን መፈተሽ አለብን፡፡ በዳግመ ምዝገባችን፣ በተቋማቱ የሚሰጡትን ሁሉንም ፕሮግራሞቻቸውን እናያለን፡፡ ፋይሎቻቸውን እንዲያስገቡ አድርገን እያንዳንዱን ፕሮግራም እንመዝናለን፡፡ አያስፈልጉም የምንላቸውን ፕሮግራሞች እንዲዘጉ፣ ያስኬዳሉ የምንላቸውን ደግሞ እንዲያስቀጥሉ እናደርጋለን፡፡

የመንግስት ተቋማትን ከግሎቹ በበለጠ ጠንከር ያለ ምዘና እናደርጋለን፡፡ ጠበቅ አድርገን ለማየት እንሞክራለን፡፡ የግሎቹን እንደጨረስን፣ በየክልሉ ያሉትንና በፌደራል ደረጃም ያሉትን ኮሌጆችና የማሰልጠኛ ተቋማትን እናያለን፡፡ ከዛም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች እንሔዳለን፡፡ ይህ ስራ በ 2018 ዓ.ም የሚጀመር ይመስለኛል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
967👏103😭31🙏30🕊21🤔15😡14🥰13😱10😢5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ፀደቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ። ረቂቅ አዋጁ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው። ረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ክርክር ሲነሳበት እንደነበር ይታወቃል። በተለይ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማሕበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ረቂቅ አዋጁ ላይ የደመወዝ ገቢ ግብር መነሻ ተብሎ የተቀመጠው 2,000 ብር ወደ 8…
#ግብር

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱም የገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅን በ5 ተቃውሞ፣ በ12 ድምጸ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው ያፀደቀው።

በሕዝብ ተወካዮች ምር ቤት የፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያው ከግብር ነጻ የሆነው ከመቀጠር የሚገኘ ገቢ ከፍ እንዲል የተደረገ በመሆኑ ፦
- ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ተቀጣሪዎች ላይ የግብር ጫናው እንደሚቀንስ፤
- የግብር መሰረቱ እንዲሰፋ፤
- መንግስት ከገቢ ግብር የሚያገኘው ገቢ በአንጻራዊ ሁኔታ ከፍ እንዲል አጋዥ መሆኑን አመልክተዋል።

በማሻሻያው ላይ ከበርካታ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንደተደረገበት እና እንደ ቋሚ ኮሚቴም ሰፊ ጊዜ ተወስዶበት የተዘጋጀ ማሻሻያ ነው ብለዋል።

የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ " ማሻሻያው ለረጅም ጊዜ ውይይት የተደረሀበት እና የሀገራት ልምድ የተወሰደበት ነው። ማሻሻያው ዘመኑን የዋጀ ነው " ሲሉ ተናገረዋል።

አዋጁን የተቃወሙ የምክር ቤት አባላት የገቢ ግብር ማሻሻያው የመንግስት ሠራተኛውን የኑሮ ሁኔታ ታሳቢ ያላደረገ ማሻሻያ በመሆኑ ምክር ቤቱ ማሻሻያውን በድጋሚ እንዲፈትሸው ጠይቀዋል፡፡

የገቢ ግብር አዋጁ ከዚህ ቀደም ሰፊ የክርክር ነጥቦች የተነሳባቸው ጉዳዮች ላይ ማስተካከያ ሳይደረግበት ነው በ5 ተቃውሞ ፣ በ12 ድምጸ ተዓቅዶ በአብላጫ ድምጽ የፀደቀው።

#HoPR🇪🇹
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😡1.96K767😭281💔86🤔25🕊24🥰13👏13😱8🙏7
“ ለውጪ አገር ዜጋ ቦታ ለመስጠት ብለው በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ለማፈናቀል እየተሯሯጡ ነው ” - 1400 አባላትን ያቀፈው ማኀበር

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ' አጣና ተራ ' በተሰኘ ቦታ 1400 የሚሆኑ ሰዎች በተለያዩ ስራዎች የሚንቀሳቀስበትን ቦታ ያለ ምትክ “ ልቀቁ ” መባላቸውን ማኀበራቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቤቱታውን አሰማ።

“ ዜድቲኤም ማኀበር ” ከተመሰረተ 20 ዓመታትን እንዳስቆጠረ ገልጾ፣ “ ቦታው የሚሰጠው ለቻይናዊ ነው ተብሏል፤ ‘ለባለሃብት ተሰጥቷል ከቦታው ላይ ተነሱ’ ተብለናል ” ሲል ገልጿል።

“ ካሳም ሆነ ምትክ ቦታ አልተሰጠንም ” ያለው ማኀበሩ፣ “ መንግስት በሐምሌ ጨለማ ሜዳ ላይ አይጣለን፤ በሦስት ቀናት ውስጥ ወጥተን የት እንወድቃለን ? ” ሲል ጠይቆ፣ መንግስት አካባቢውን ለማልማት ጊዜ፣ ወይም ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸው አሳስቧል።

ማኀበሩ በዝርዝር ምን አለ ?

“ ለውጪ አገር ዜጋ ቦታ ለመስጠት ብለው በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ለማፈናቀል እየተሯሯጡ ነው። የበላይ የመንግስት አካልም የሚያውቀው አይመስለንም። ከታች ያሉት አካላት አሻጥር እየሰሩ ህዝቡን በዚህ በሐምሌ ጨለማ ‘በሦስት ቀናት እቃህን ይዘህ ውጣ’ የሚል አሳዛኝ ድርጊት ነው እየተፈጸመ ያለው ” ብሏል።

ማኀበሩ፣ “ ትልቅ በደል ነው በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው። ህዝቡ እያለቀሰ ነው፤ ምሳውን በልቶ እራቱን የማይደግም ህዝብ ነው ችግር ላይ እየወደቀ ያለው ” ሲልም ወቅሷል።

ቦታውን ከ50 ዓመት በፊት ጀምሮ ይሰሩበት እንደነበር የገለጸው ማኀበሩ፣ “ ነባር ቦታ ነው፤ ቤት ንብረት ተመስርቶ፣ በግለሰብም ተከራይቶ የሚኖርበት ቦታ ነው ” ብሏል።

“ አካባቢው ነባር መዘጋጃ ቤት ነው፤ በኃይለ ሥላሴ ጊዜ ተሰርቶ ለግለሰቦች የተከራየ ቤት ነው። በ1960 ዓ/ም የተያዘ ቦታ ነው። ከሱ ቤት ውስጥ ነው ውጡና ሜዳ ላይ ውደቁ የተባለው ” ሲልም አክሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ ምላሽ የጠየቃቸው አንድ የክፍለ ከተማው አካል፣ “ ጉዳዩ አይመለከተኝም ” ብለው ስልክ ዘግተዋል፤ በድጋሚ ሲደወልም ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም፣ ተጨማሪ ጥረት ይደረጋል።
 
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭887567😡158🕊24🤔23💔17👏10🙏9😢8🥰1
“ በሰው የደረሰ የሞት አደጋ የለም፡፡ ሁለት ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ እንስሳት ተጎድተዋል፤ ንግድ ሱቆችም ተቃጥለዋል ” - አፋር ክልል

በአፋር ክልል ዳሎል ወረዳ የተከሰተው፣ እስካሁን “መንስዔው ገና እየተጣራ ነው” የተባለው የእሳት አደጋ ከፍተኛ የንብረት ውድመት መከሰቱን የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተገልጿል፡፡

የክልሉ መንግስት ኮሚዩኒኬሽ ኃላፊ አቶ መሐመድ አሊ፣ “ የእሳት አደጋው መንስዔ ገና እየተጣራ ነው፡፡ በሰው የደረሰ የሞት አደጋ የለም። ሁለት ሰዎች ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ እንስሳት ተጎድተዋል፤ ንግድ ሱቆችም ተቃጥለዋል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

አደጋው የተነሳው ትላንት 11 ሰዓት ተኩል ገደማ መሆኑን፣ የአካባቢው ማህበረሰብ ጭምር እሳቱን ለማጥፋት ርብርብ እናዳደረገ የገለጹት ኃላፊው፣ “እሳቱ በቁጥጥር ሥር ውሏል” ብለዋል፡፡

በቃጠሎው የደረሰው የጉዳት መጠን ምን ያክል እንደሆነ ሲጠየቁም፣ “ ጉዳቱ ከፍተኛ ነው ከፍተኛ እሳት ነው የነበረው፡፡ አካባቢው ሞቃታማ ነው ቶሎ መቆጣጠር አይቻልም፡፡ ቦታውም ከሰመራ በጣም ሩቅና ገጠራማ አካካቢ ስለሆነ የእሳት አደጋ ተሸከርካሪ ቶሎ የሚደርስበት አይደለም፡፡ በባህላዊ መንገድ ነው እሳቱን ያጠፉት ” ሲሉ አስረድተዋል፡፡

የጉዳት መጠኑን ለማወቅ ባለሙያዎች በጥናት መሰረት የሚያቀርቡትን መረጃ መጠበቅ የተሻለ እንደሆነና ሪፖርቱ ሲደርስ እንደሚገልጹ ጠቁመዋል፡፡

በጥቅሉ በአደጋው ሱቆች፣ ንግድ ቤቶች፣ የግለሰብ መኖሪያ ቤቶች በእሳቱ እንደተቃጠሉ፣ በአካባው የክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን እንደደረሰና የጉዳቱ መጠን እየተጣራ መሆኑም ገልጸዋል፡፡

“ሞት ባይኖርም በእሳት አደጋ ምክንያት የተፈናቀሉ አሉ፡፡ የስነ ልቦና ችግር ለደረሰባቸው ወገኖችንም የክልል ጤና ቢሮ የህክምና ባለሙያዎች ልዑካን ቡድን ተልኳል። የእሳር አደጋውን መነሻ ለማወቅ ፖሊስም እያጣራ ነው” ብለዋል።

“በዳሎል ለደረሰው የእሳት እና በአፍዴራ ለደረሰው ሰሞንኛ የንፋስ አደጋ ክልሉ ለተጎጅዎች የእለት ደራሽ ምግብ በማቅረብ፣ የህክምና አገልግሎት በመስጠት፣ ጊዜያዊም ቢሆን የመጠለያ ቁሳቁስ በመቅረብ ባለው አቅም በቦታው ደርሶ ህዝቡን የመታደግ ሥራ እየሰራ ነው፡፡ በቀጣይ የፌደራሉም የክሉም መንግስት የሚሰሩበት ይሆናል” ብለዋል አቶ መሐመድ።

ቲክቫህ ኢተዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
380😢109🙏16💔10🕊9😡7😭6🥰4
TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ሰዎች ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " - የወረዳው ቤተ ክህነት በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ የ"ሸኔ" ታጣቂ ቡድን በአንድ ቤተሰብ አባላት የግድያ እና እገታ ጥቃት መፈጸሙን የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። ቤተ ክህነቱ የሆነውን ሲያስረዳ፣ " ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ትላንት 3 ሰዓት ከሩብ ላይ…
" ታግተው ተወስደው የነበሩት ሁለቱም ዛሬ ተገድለዋል፡፡ ገንዘብ ተሰብሶ የተወሰነውን ከወሰዱ በኋላ መልሰው ገደሏቸው " - የወረዳው ቤተ ክህነት

በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ/ም የ "ሸኔ" ታጣቂ ቡድን ባደረሱት ጥቃት አባትና ልጅ በተገደሉበት ወቅት " ታግተው ተወስደዋል " ተብለው የነበሩ ሁለቱ ሰዎች የሚለቀቁበት ገንዘብ ተሰብሰቦ የተወሰነው ከተሰጠ በኋላ " ገድለዋቸዋል " ሲል የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡

ታጣቂ ቡድኑ በወቅቱ በአንድ ቤተሰብ አባላት ስላደረሰው ጥቃት ቤተ ክህነቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ " አንድ ካህንና ወንድሙ ሁለት ሰዎች ናቸው ታግተው የተወሰዱት፡፡ አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " ብሎ ነበር፡፡

ዛሬ ለቲክቫህ ኢትየጵያ በሰጠው ቃል ደግሞ፣ " ታግተው ተወስደው የነበሩት ሁለቱም ሰዎች ዛሬ ተገድለዋል፡፡ አምጥተው በአካባቢያቸው ገድለው ጥለዋቸው ሂደዋል " ብሏል፡፡

" ገንዘብ ተሰብሶ የተወሰነውን ከወሰዱ በኋላ መልሰው ገደሏቸው፡፡ ዛሬ ሌሊት ተገድለው አደሩ፤ ሜዳ ላይ አምጥተው ገድለው ጥለዋቸው ነው የሄዱት፡፡ ዛሬ ቀብራቸው ተፈጽሟል " ያለው ቤተ ክህነቱ፣ ሟቾቹ ካህንኑና ወንድሙ ከሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ/ም ጅምሮ ታግተው እንደቆዩ፣ አጋቾቹ ታጋቾቹን ለመልቀቅ ገንዘብ ጠይቀው እንደነበርና የተወሰነው ተሰብስቦ ከወሰዱ በኋላ የግድያ ጥቃቱን ማድረሳቸውን አስረድቷል፡፡

" የተገደሉትም ካህኑና ወንድሙ ናቸው፡፡ ስማቸውም ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወገኔ ጌታነህ ነው የሚባለው " ሲል አስረድቶ፣ አሁንም በአካባቢው ያለው የታጣቂ ቡድኑ እንቅስቃሴ አስጊና አሳሳቢ መሆኑን ጠቁሞ፣ ከለላ እንዲደረግ አሳስቧል።

ተደጋጋሚ ጥቃቱን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው የኦሮሚያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ ጥቃት ደረሰበት የተባለው ወረዳ ምላሽ እንዲሰጥ በመጠቆም ማብራሪያ ከመስጠት የተቆጠበ ሲሆን፣ ወደ ወረዳው የተደረገው ሙከራም ለጊዜው አልተሳካም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭1.31K497😡176💔59😢30🕊17🙏7🥰4😱4🤔2