" ህጻናት ፣ እናቶች፣ አሮጊቶች ፣ ሽማግሌዎች ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " - ነዋሪዎች
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።
ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።
" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።
" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።
" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።
ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።
" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።
ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።
" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።
በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።
" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።
አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።
" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።
የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።
" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።
ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።
ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ
@tikavhethiopia
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ከመቂ ከተማ 18 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ታጣቂዎች በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።
በጉዳዩ ላይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪ ፥ " ድርጊቱ የተፈጻመው በሸኔ ታጣቂዎች ነው። እጅግ በጣም አሳዛኝ ልብን የሚሰብር ነገር ነው የተፈፀመው " ብለዋል።
ቦታው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ፣ ዱግዳ ወረዳ ኩሬ፣ ጋሌ፣ ቢቂሲ የሚባሉ ቀበሌዎች እንደሆነና ቦታው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ እንደሚዋሰን ጠቁመዋል።
" ድንገት ምሽት ላይ ነው ግድያው የተፈጸመው። በወቅቱ ከባድ ዝናብ ይዘብ ነበር " ብለዋል።
" ድንገተኛ ስለነበረ ማሳ ውስጥ ሲሮጥ በተባራሪ ጥይት የተመታ አለ ፤ በቆሎ ውስጥ ያልተነሳ ሬሳ አለ፣ ተቃጥሎ መለየት ያልተቻለ ሬሳ አለ ፤ እስካሁን ባለው 44 ሰው እንደሞተ ነው የሰማነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ግድያው ምሽት በድንገት ነው የተፈጸመው። ከሟቾቹ 80% የሚሆኑ ማምለጥ የማይችሉ ህጻናት፣ አሮጊቶች ፣ ሴቶች ፣ ሽማግሌዎች ናቸው " ብለዋል።
" ህጻናት ናቸው የተገደሉት ፣ አሮጊቶች ናቸው ፤ ተነስታ መሮጥ የማትችል አራስ እናት ሳትቀር ነው የተገደለችው " ሲሉ አክለዋል።
ግድያ ብቻ ሳይሆን ማቃጠልም ሲፈጽሙ ነበር።
" በወቅቱ የመንግሥት ኃይል አልነበረም። ከምሽት 2 ሰዓት አንስቶ እስከ ለሊት 8 ሰዓት ነው የዘለቀው። አብዛኛው የመንግስት ፀጥታ ኃይል መቂ ነው ያለው " ብለዋል።
ግድያ በተፈጸመባቸው ስፍራዎች ላይ በወቅዩ ግጭት እንዳልነበረም ጠቁመዋል።
" የአካባቢው ሰው በታጣቂዎች ጥቃት ብዙ ተሰቃይቷል። መጨረሻ ሲደክመው እነሱን (ታጣቂዎቹን) ማዳመጥ አቆመ ፤ ከዛም በጎጥ እየተደራጀ ሰፈሩን መጠበቅ ጀመረ ፤ ታጣቂዎቹ ከጠፉ ከ6 ወር በኃላ አዘናግተው ነው አሁን መጥተው ግድያው ያፈጸሙት " ብለዋል።
በአጋጣሚ ከባድ ዝናብ ስለነበር ሰውም ወጥቶ አካባቢውን የሚጠብቅበት ሁኔታ እንዳልነበርና (ቤት ውስጥ እንደበር) በዚህ መሃል ሰብረው ገብተው ግድያውን እንደፈጸሙ ተናግረዋል።
" ያለ ርህራሄ ፣ ያለ ልዩነት ሲገድሉ የነበረው ነዋሪውን ነው " ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ ተጎጂ አይን እማኞች ረቡዕ ከምሽት ጀምሮ እስከ ለሊት በዘለቀ ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ እናቶች እና አረጋዊን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል ብለዋል።
አንድ ተጎጂ በሶዶ ወረዳ አዋሳኝ የደረሰው አስከፊ ጉዳት እንደሆነ ገልጸዋል።
" ሰው መግደል ፣ ማቃጠል ነው። ' የኛን ሃሳብ ለምን አልተከተላችሁም ለምን ከመንግስት ጋር ትሆናላችሁ ' የሚል ነው። ገበሬው ሸኔ ከሚባለው ብዙ ጊዜ ጥቃት ስለደረሰበት እራሱን ለመከላከል እየተደራጀ ነበር። መሳሪያም ይዞ፣ መንግሥትም እያበረታው እራሱን ለመከላከል እንቅስቃሴ ያደርግ ነበር። እየወጣም ይጠብቅ ነበር። ያንን በመቃወም ነው ጥቃቱ " ብለዋል።
" ብዙ ጊዜ ሰው ይታገታል ገንዘብ ይጠየቃል፣ ብዙ ሰው ተሰቃይቶ ከስፍራው ለቋል ፣ መንገድም ዘግተው ቆይተዋል (ታጣቂዎቹ) " ሲሉ አክለዋል።
የአሁኑ ጥቅት ግን እጅግ በጣም የከፋና ከዚህ በፊት ያልታየ እንደሆነ አክለዋል።
" በብዙ አቅጣጫ ሆነው ይገባሉ ቤት ከውጭ ይዘጋሉ እሳት ይለኩሳሉ ለማምለጥ የሚሮጠውን በጥይት ነው ሲመቱ የነበረው የተቀበረው ብቻ 40 አካባቢ ነው ፤ 4 ፣ 5 ቤተሰብ ነው ሲቀበር የነበረው " ብለዋል።
ከሰው እልቂት ባለፈም እንስሳት ተቃጥለዋል ፤ በርካታ ንብረት ወድሟል።
ነዋሪው ሌላ ጥቃት እንዳይፈጸም በመስጋት ከቦታው እየወጣ እንደሆነ የአይን እማኙ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamily #ዶቼቨለ
@tikavhethiopia
#ኢትዮጵያ
የኩላሊት እጥበት ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ በሳምንት 3 ጊዜ እጥበት የሚያደርጉ ሕሙማን ከባድ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን፣ የኩላሊት ሕክምና እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት አስታውቋል።
ከሰሞኑም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤ " መንግሥት የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ካደረገ በኋላ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም የሕክምና ተቋማት የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት አንድ ታካሚ የኩላሊት እጥበት ለአንድ ጊዜ ሲያደርግ ይፈጸም የነበረው ክፍያ 2,000 ብር እንደነበር፣ ነገር ግን የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ሲደረግ አገልግሎት የሚሰጡ የሕክምና ተቋማት ከ3,000 እስከ 4,100 ብር እያስከፈሉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ለኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶች ከውጭ ስለሚገቡ፣ የአገልግሎት ክፍያው በእጥፍ መጨመሩንና በሳምንት ሦስት ጊዜ የሚጠቀም ታካሚ አንድ ጊዜ ብቻ ለማድረግ መገደዱን አክለው ገልጸዋል፡፡
በሞት ከተለዩ ሰዎች ኩላሊት እንዲወሰድ የሚፈቅድ የሕግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ድርጅቱ ጥረት ማድረጉን፣ ጉዳዩም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን ተናግረዋል፡፡
ጉዳዩ በሕግ ማዕቀፍ ሲታገዝ በርካታ ሰዎች የኩላሊት ንቅለ ተከላ በቀላሉ እንደሚያደርጉ፣ እስከዚያው ግን ማኅበረበሰቡ ለኩላሊት ሕሙማን የተሻለ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
አሁን ላይ የሚመሩት ድርጅት ድጋፍ በዘውዲቱ፣ በምኒልክና በጳውሎስ የሕክምና ተቋማት የሚገኙ 210 ሕሙማን ነፃ የሕክምና አገልግሎት እያገኙ ናቸው።
ይሁን እንጂ በግል ሆስፒታሎች አገልግሎት የሚያገኙ ሕሙማን በ15 ቀናት ውስጥ እጥበት ሲያደርጉ፣ ከፍተኛ ወጪ እንደሚጠብቃቸው ተጠቁሟል። #ሪፖርተር
@tikvahethiopia
የኩላሊት እጥበት ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ በሳምንት 3 ጊዜ እጥበት የሚያደርጉ ሕሙማን ከባድ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን፣ የኩላሊት ሕክምና እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት አስታውቋል።
ከሰሞኑም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰለሞን አሰፋ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤ " መንግሥት የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ካደረገ በኋላ የኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚሰጡ ሁሉም የሕክምና ተቋማት የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት አንድ ታካሚ የኩላሊት እጥበት ለአንድ ጊዜ ሲያደርግ ይፈጸም የነበረው ክፍያ 2,000 ብር እንደነበር፣ ነገር ግን የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ሲደረግ አገልግሎት የሚሰጡ የሕክምና ተቋማት ከ3,000 እስከ 4,100 ብር እያስከፈሉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ለኩላሊት እጥበት አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶች ከውጭ ስለሚገቡ፣ የአገልግሎት ክፍያው በእጥፍ መጨመሩንና በሳምንት ሦስት ጊዜ የሚጠቀም ታካሚ አንድ ጊዜ ብቻ ለማድረግ መገደዱን አክለው ገልጸዋል፡፡
በሞት ከተለዩ ሰዎች ኩላሊት እንዲወሰድ የሚፈቅድ የሕግ ማዕቀፍ እንዲወጣ ድርጅቱ ጥረት ማድረጉን፣ ጉዳዩም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡን ተናግረዋል፡፡
ጉዳዩ በሕግ ማዕቀፍ ሲታገዝ በርካታ ሰዎች የኩላሊት ንቅለ ተከላ በቀላሉ እንደሚያደርጉ፣ እስከዚያው ግን ማኅበረበሰቡ ለኩላሊት ሕሙማን የተሻለ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
አሁን ላይ የሚመሩት ድርጅት ድጋፍ በዘውዲቱ፣ በምኒልክና በጳውሎስ የሕክምና ተቋማት የሚገኙ 210 ሕሙማን ነፃ የሕክምና አገልግሎት እያገኙ ናቸው።
ይሁን እንጂ በግል ሆስፒታሎች አገልግሎት የሚያገኙ ሕሙማን በ15 ቀናት ውስጥ እጥበት ሲያደርጉ፣ ከፍተኛ ወጪ እንደሚጠብቃቸው ተጠቁሟል። #ሪፖርተር
@tikvahethiopia
ፎቶ፦ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ' ማርያም ማዞሪያ ' አካባቢ በመኖሪያ ቤቶች ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ ያደረሰው ውድመት።
Via @tikvahethmagazine
Via @tikvahethmagazine
#ቦትስዋና 👏 #ዴሞክራሲ
" ለ2ኛ የስልጣን ዘመን መመረጥ ብሻም፣ ገለል ብዬ በስልጣን ሽግግሩ ተሳትፎ አደርጋለሁ " - ፕሬዝደንት ሞከዌትሲ ማሲሲ
በአህጉራችን አፍሪካ የተረጋጋ የዲሞክራሲ ስርዓት ካላቸው ሃገራት ውስጥ ግንባር ቀደሟ ቦትስዋና ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ አድርጋለች።
በርካታ የሀገሪቱ ዜጎች ለ58 ዓመታት ስልጣን ላይ የሚገኘውን ገዢ ፓርቲ ድምጻቸውን ነፍገውታል።
ፓርቲው አስደንጋጭ ነው የተባለ ሽንፈትን ተከናንቧል።
የፓርቲው መሪና የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሞከዌትሲ ማሲሲ በምርጫ መሸነፋቸውን አምነዋል።
ምንም እንኳን እስካሁን የምርጫው ውጤት በይፋ ባይታወጅም ሃገሪቱ ከእንግሊዝ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 58 ዓመታት በሥልጣን ላይ የከረመው ፓርቲያቸው ‘ የቦትስዋና ዲሞክራቲክ ፓርቲ ’ ሽንፈትን አስተናግዷል።
ዋናው ተቃዋሚ ፓርቲ ‘ አምብሬላ ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ ’ ከፍተኛ ድምጽ አግኝቷል።
የፓርቲው እጩ ዱማ ቦኮ በዓለም ከፍተኛ አልማዝ አምራች ከሆኑት ሃገራት ውስጥ አንዷ የሆነችው ቦትስዋና ፕሬዝደንት ለመሆን ተቃርበዋል።
ፕሬዜዳንት ሞከዌትሲ ማሲሲ ለተቀናቃኛቸው ቦኮ ስልክ በመደወል በምርጫው መሸነፋቸውን ነግረዋቸዋል።
" በዲሞክራሲ ሂደቱ እጅግ ኩራት ተሰምቶኛል። ለሁለተኛ የስልጣን ዘመን መመረጥ ብሻም፣ ገለል ብዬ በስልጣን ሽግግሩ ተሳትፎ አደርጋለሁ " ብለዋል ፕሬዜዳንት ማሲሲ።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ማሲሲ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ሂደት ደስ እንደተሰኙ ገልጸው " የህዝቡን ፍላጎት እና ምርጫ አከብራለሁ " ብለዋል።
ደጋፊዎቻቸውን ረጋ እንዳሉ በእርጋታቸው እንዲቀጥሉና ከአዲሱ የሀገሪቱ መንግስት ጀርባ ተሰልፈው እንዲደግፉ በይፋ ጥሪ አቅርበዋል።
ቦትስዋና በአፍሪካ የተረጋጋ ዲሞክራሲ ካላቸው ሃገራት ውስጥ ግንባር ቀደም ነች በሚል ስትሞካሽ፣ በዓለም ከሩሲያ በመቀጠል ሁለተኛ የአልማዝ አምራች ሃገር ነች፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከቪኦኤ እና ቢቢሲ ማግኘቱን ይገልጻል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" ለ2ኛ የስልጣን ዘመን መመረጥ ብሻም፣ ገለል ብዬ በስልጣን ሽግግሩ ተሳትፎ አደርጋለሁ " - ፕሬዝደንት ሞከዌትሲ ማሲሲ
በአህጉራችን አፍሪካ የተረጋጋ የዲሞክራሲ ስርዓት ካላቸው ሃገራት ውስጥ ግንባር ቀደሟ ቦትስዋና ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ አድርጋለች።
በርካታ የሀገሪቱ ዜጎች ለ58 ዓመታት ስልጣን ላይ የሚገኘውን ገዢ ፓርቲ ድምጻቸውን ነፍገውታል።
ፓርቲው አስደንጋጭ ነው የተባለ ሽንፈትን ተከናንቧል።
የፓርቲው መሪና የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሞከዌትሲ ማሲሲ በምርጫ መሸነፋቸውን አምነዋል።
ምንም እንኳን እስካሁን የምርጫው ውጤት በይፋ ባይታወጅም ሃገሪቱ ከእንግሊዝ ነፃ ከወጣችበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 58 ዓመታት በሥልጣን ላይ የከረመው ፓርቲያቸው ‘ የቦትስዋና ዲሞክራቲክ ፓርቲ ’ ሽንፈትን አስተናግዷል።
ዋናው ተቃዋሚ ፓርቲ ‘ አምብሬላ ፎር ዲሞክራቲክ ቼንጅ ’ ከፍተኛ ድምጽ አግኝቷል።
የፓርቲው እጩ ዱማ ቦኮ በዓለም ከፍተኛ አልማዝ አምራች ከሆኑት ሃገራት ውስጥ አንዷ የሆነችው ቦትስዋና ፕሬዝደንት ለመሆን ተቃርበዋል።
ፕሬዜዳንት ሞከዌትሲ ማሲሲ ለተቀናቃኛቸው ቦኮ ስልክ በመደወል በምርጫው መሸነፋቸውን ነግረዋቸዋል።
" በዲሞክራሲ ሂደቱ እጅግ ኩራት ተሰምቶኛል። ለሁለተኛ የስልጣን ዘመን መመረጥ ብሻም፣ ገለል ብዬ በስልጣን ሽግግሩ ተሳትፎ አደርጋለሁ " ብለዋል ፕሬዜዳንት ማሲሲ።
ተሰናባቹ ፕሬዜዳንት ማሲሲ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ሂደት ደስ እንደተሰኙ ገልጸው " የህዝቡን ፍላጎት እና ምርጫ አከብራለሁ " ብለዋል።
ደጋፊዎቻቸውን ረጋ እንዳሉ በእርጋታቸው እንዲቀጥሉና ከአዲሱ የሀገሪቱ መንግስት ጀርባ ተሰልፈው እንዲደግፉ በይፋ ጥሪ አቅርበዋል።
ቦትስዋና በአፍሪካ የተረጋጋ ዲሞክራሲ ካላቸው ሃገራት ውስጥ ግንባር ቀደም ነች በሚል ስትሞካሽ፣ በዓለም ከሩሲያ በመቀጠል ሁለተኛ የአልማዝ አምራች ሃገር ነች፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከቪኦኤ እና ቢቢሲ ማግኘቱን ይገልጻል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#EarthQuake " በኢትዮጵያ በስምጥ ሸለቆ ውስጥ ለ22 ቀናት ወደ መሬት ለመውጣት ተፈጥሯዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የነበረው ቅልጥ አለት የመወጠር ሁኔታ አሁን ረገብ ብሏል " ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂዮ ፊዚክስ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ኤልያስ ሊዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን/ኢቲቪ ተናግረዋል። " አሁን ባለን መረጃ ቅልጥ አለቱ ወደታች እየወረደ ነው ፤ በዚህም ምክንያት ባለፉት…
#Awash🚨
ዛሬ ምሽት 3:55 ላይ በአፋር ክልል ፣ ' አዋሽ ' አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ከነዋሪዎች የመጡት መልዕክቶች ያስረዳሉ።
አንድ የአዋሽ ነዋሪ ፤ " የዛሬውስ በጣም ያስፈራ ነበር " ሲል ሁኔታውን ገልጾታል።
ሌላ ነዋሪው ፥ " በጣም ነው ያስደነገጠን ከባለፉት አንጻር ዛሬ በጣም ነው የተሰማው አላህ ይጠብቀን " ብሏል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ ዘልቆ መሰማቱንም ከነዋሪዎች የሚመጡት መልዕክቶች ያስረዳሉ።
እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' መረጃ ከአዋሽ በምዕራብ በኩል 8 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ነበር።
በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ እንደሆነ ጠቁሟል።
ዝርዝር መረጃ ከባለሞያዎችን እንደሰማን የምናቀርብ ይሆናል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ዛሬ ምሽት 3:55 ላይ በአፋር ክልል ፣ ' አዋሽ ' አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደነበር ከነዋሪዎች የመጡት መልዕክቶች ያስረዳሉ።
አንድ የአዋሽ ነዋሪ ፤ " የዛሬውስ በጣም ያስፈራ ነበር " ሲል ሁኔታውን ገልጾታል።
ሌላ ነዋሪው ፥ " በጣም ነው ያስደነገጠን ከባለፉት አንጻር ዛሬ በጣም ነው የተሰማው አላህ ይጠብቀን " ብሏል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ ዘልቆ መሰማቱንም ከነዋሪዎች የሚመጡት መልዕክቶች ያስረዳሉ።
እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' መረጃ ከአዋሽ በምዕራብ በኩል 8 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ነበር።
በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ እንደሆነ ጠቁሟል።
ዝርዝር መረጃ ከባለሞያዎችን እንደሰማን የምናቀርብ ይሆናል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#ንጉስማልት
አፍ ላይ ቀለል ብሎ የሚጠጣ ፣ ልብን በደስታ የሚሞላ ፣ ልዩ ጣዕም!
ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.iss.one/Negus_Malt
#ደስደስበንጉስ #nonalcoholic #ከአልኮልነፃ
አፍ ላይ ቀለል ብሎ የሚጠጣ ፣ ልብን በደስታ የሚሞላ ፣ ልዩ ጣዕም!
ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.iss.one/Negus_Malt
#ደስደስበንጉስ #nonalcoholic #ከአልኮልነፃ
#MPESASafaricom
ይሄኔ እኮ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይህን አልሰሙም ፤ 5% ተመላሽ አለን ፤ መቼ ? የሃገር ዉስጥ በረራችንን በM-PESA ስናደርግ ! ይህን አጋጣሚማ እፍስ ነው እንጂ!
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
ይሄኔ እኮ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይህን አልሰሙም ፤ 5% ተመላሽ አለን ፤ መቼ ? የሃገር ዉስጥ በረራችንን በM-PESA ስናደርግ ! ይህን አጋጣሚማ እፍስ ነው እንጂ!
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
ሞሐ የለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ አክሲዮን ማህበር ፣ ለደንበኞቹ ካዘጋጃቸው በርካታ ሽልማቶች ውስጥ የመጀመርያው ቮልስ ዋገን አይዲ4 (VW ID4) የኤሌክትሪክ መኪና ዕጣ፣ በሐዋሳ ከተማ ለዕድለኛ ወጥቷል፡፡
ዕድለኛው አሸናፊ አቶ ኤርሚያስ ብርሃኑ፣ ሽልማታቸውን ጥቅምት 23 ቀን 2017ዓ.ም. በሐዋሳ ከተማ በተከናወነ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡
ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ኮተቤ 04 አካባቢ የቢዋይዲ ኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት ለባለዕድለኛ መውጣቱ ይታወሳል፡፡
አሁንም በርካታ ሽልማቶች ተረኛ ዕድለኛቸውን እየጠበቁ ነው፡፡ የፔፕሲን ምርቶች እያጣጣምን ዕድላችን እንሞክር - እናሸንፍ! ፔፕሲ፣ ሚሪንዳ እና ሰቨን አፕ ይጥማሉ - ያስሸልማሉ!
ዕድለኛው አሸናፊ አቶ ኤርሚያስ ብርሃኑ፣ ሽልማታቸውን ጥቅምት 23 ቀን 2017ዓ.ም. በሐዋሳ ከተማ በተከናወነ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም ተረክበዋል፡፡
ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ ኮተቤ 04 አካባቢ የቢዋይዲ ኤሌክትሪክ መኪና ሽልማት ለባለዕድለኛ መውጣቱ ይታወሳል፡፡
አሁንም በርካታ ሽልማቶች ተረኛ ዕድለኛቸውን እየጠበቁ ነው፡፡ የፔፕሲን ምርቶች እያጣጣምን ዕድላችን እንሞክር - እናሸንፍ! ፔፕሲ፣ ሚሪንዳ እና ሰቨን አፕ ይጥማሉ - ያስሸልማሉ!
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar #Tigray " የትግራይ ክልል ሰላም ለክልላችን ሰላም ወሳኝ ነው " - ሀጂ አወል አርባ የአፋር ክልል ፕሬዜዳንት ሀጂ አወል አርባ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ከፍተኛ አመራርን ላካተተዉ ሉዑካን ቡድን ምን አሉ ? " የአፋርና ትግራይ ህዝቦች መካከል የሰላምና ፀጥታ ችግሮችን መፍታት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን ማጠናከር አስፈላጊ ነው። በሁለቱ ክልሎች…
#አፋር #ትግራይ
የትግራይ እና የዓፋር አጎራባች ዞኖች አመራሮች ዛሬ ጥቅምት ለሁለተኛ ጊዜ በዓፋርዋ የአብዓላ ከተማ ተገናኝተዋል።
ለግማሽ ቀን በተካሄደው የሁለቱ ክልል አጎራባች ዞኖች አመራሮች ግንኙነት ፦
- የሁለቱም ክልል ህዝቦች የፊት ለፊት ግንኙነት እንዲጀመር፤
- የተከለከሉ መንገዶች ተከፈትው ነፃ የህዝቦች ግንኙነት እንዲቀጥል፤
- ተቋርጦ የነበረው የሁለቱ ክልል ህዝቦች የሰላም እና የልማት ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል፡
- ሁለቱም ክልሎች ወንጀለኞች ተላልፈው እንዲሰጣጡ፤
- ሁለቱም ክልሎች የሰላምና የፀጥታ እቅድ በማውጣት በየወሩ እየገመገሙ እንዲጓዙ፤
ተወያይተው መግባባት ላይ ደርሰዋል።
ግንኙነቱ በማስመልከት አስተያየት የሰጡት የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ሰላምና ልማት መሰረት እንዲይዝ በክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የላቀ ዝግጁነት አለው " ብሏል።
በያዝነው ጥቅምት ወር መጀመሪያ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ ዓፋር ሰመራ ድረስ በመጓዝ ከርእሰ መስተዳደር ሃጂ ኣወል ኣርባ ጋር ውጤታማ የሆነ ውይይት ማካሄዳቸው መዘገባችን ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
Photo Credit - Tigrai Television
@tikvahethiopia
የትግራይ እና የዓፋር አጎራባች ዞኖች አመራሮች ዛሬ ጥቅምት ለሁለተኛ ጊዜ በዓፋርዋ የአብዓላ ከተማ ተገናኝተዋል።
ለግማሽ ቀን በተካሄደው የሁለቱ ክልል አጎራባች ዞኖች አመራሮች ግንኙነት ፦
- የሁለቱም ክልል ህዝቦች የፊት ለፊት ግንኙነት እንዲጀመር፤
- የተከለከሉ መንገዶች ተከፈትው ነፃ የህዝቦች ግንኙነት እንዲቀጥል፤
- ተቋርጦ የነበረው የሁለቱ ክልል ህዝቦች የሰላም እና የልማት ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል፡
- ሁለቱም ክልሎች ወንጀለኞች ተላልፈው እንዲሰጣጡ፤
- ሁለቱም ክልሎች የሰላምና የፀጥታ እቅድ በማውጣት በየወሩ እየገመገሙ እንዲጓዙ፤
ተወያይተው መግባባት ላይ ደርሰዋል።
ግንኙነቱ በማስመልከት አስተያየት የሰጡት የትግራይ ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ግንኙነት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ሰላምና ልማት መሰረት እንዲይዝ በክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር የላቀ ዝግጁነት አለው " ብሏል።
በያዝነው ጥቅምት ወር መጀመሪያ በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ ዓፋር ሰመራ ድረስ በመጓዝ ከርእሰ መስተዳደር ሃጂ ኣወል ኣርባ ጋር ውጤታማ የሆነ ውይይት ማካሄዳቸው መዘገባችን ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
Photo Credit - Tigrai Television
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ ከተማ መገናኛ አካባቢ የትራንስፖርት መጫኛና ማውረጃ ተርሚናል ለውጥ መደረጉ ተገልጿል።
1. መገናኛ ውስጥ ተርሚናል ሲሰጡ የነበሩ
ከመገናኛ - ቃሊቲ
ከመገናኛ - ሳሪስ
ከመገናኛ - ጋርመንት መስመሮች
በጊዜያዊነት መገናኛ ሙሉጌታ ህንጻ ዝቅ ብሎ አምቼ ፊት ለፊት መንገድ በመዛወር በሁሉም ሞዳሊቲ አገልግሎት እየተሰጠ ነው።
2. ቦሌ ክፍለ ከተማ ፊት ለፊት ሲሰጥ የነበረው
ከመገናኛ - ቱሉ ዲምቱ እና ኮዬ ፈቼ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው መስመሮች አምቼ አጠገብ (ቀደም ሲል ከነበረበት ቦታ ትንሽ ዝቅ ብሎ)
3. ከዚህ በፊት ሙሉጌታ ህንፃ አካባቢ ይሰጡ የነበሩ መስመሮች
ከመገናኛ - ገርጂ
ከመገናኛ-ጎሮ
ከመገናኛ - አያት እና
ከመገናኛ - ሰሚት የመጫኛና መውረጃ መስመሮች ወደ ዘርፈሽዋል አካባቢ በተዘጋጀው ጊዜያዊ ተርሚናል ውስጥ ተዘዋውሮ በሁሉም ሞዳሊቲ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ገልጿል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ መገናኛ አካባቢ የትራንስፖርት መጫኛና ማውረጃ ተርሚናል ለውጥ መደረጉ ተገልጿል።
1. መገናኛ ውስጥ ተርሚናል ሲሰጡ የነበሩ
ከመገናኛ - ቃሊቲ
ከመገናኛ - ሳሪስ
ከመገናኛ - ጋርመንት መስመሮች
በጊዜያዊነት መገናኛ ሙሉጌታ ህንጻ ዝቅ ብሎ አምቼ ፊት ለፊት መንገድ በመዛወር በሁሉም ሞዳሊቲ አገልግሎት እየተሰጠ ነው።
2. ቦሌ ክፍለ ከተማ ፊት ለፊት ሲሰጥ የነበረው
ከመገናኛ - ቱሉ ዲምቱ እና ኮዬ ፈቼ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው መስመሮች አምቼ አጠገብ (ቀደም ሲል ከነበረበት ቦታ ትንሽ ዝቅ ብሎ)
3. ከዚህ በፊት ሙሉጌታ ህንፃ አካባቢ ይሰጡ የነበሩ መስመሮች
ከመገናኛ - ገርጂ
ከመገናኛ-ጎሮ
ከመገናኛ - አያት እና
ከመገናኛ - ሰሚት የመጫኛና መውረጃ መስመሮች ወደ ዘርፈሽዋል አካባቢ በተዘጋጀው ጊዜያዊ ተርሚናል ውስጥ ተዘዋውሮ በሁሉም ሞዳሊቲ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ገልጿል።
@tikvahethiopia