TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " 4 ሚሊዮን ብር ለማስለቀቂያ ከፍለናል ሰነዱ በእጄ አለ፤ ከለቀቋቸው በኃላ ድጋሜ በመያዝ 6 ሚሊዮን ብር ጠይቀዋል " - ቀጣሪ ድርጅቱ ወደ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለደን ምንጣሮ ስራ በግል ድርጅት ተመልምለው ወደ ስፍራው በአማራ ክልል፣ በምስቅው ጎጃም ፣ ጎዛመን በኩል አቋርጠው ሲጓዙ የካቲት 18/2016 ዓ/ም " በፋኖ ታጣቂዎች " ታገቱ የተባሉ ሠራተኞች እስካሁን ከእገታ አልተለቀቁም ሲል…
#Update

" ታጋቾቹ ተለቀው በሰላም #አዲስ_አበባ ገብተዋል " - የጋርዱላ ዞን አስተዳደር

" ለማስለቀቂያ መጀመሪያ ከከፈልነው 4 ሚሊዮን ብር በተጨማሪ በእያንዳንዱ መኪና (4 መኪናዎች) 500 ሺህ ብር ከፍለናል " - ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን

" አንድም ገንዘብ አልተቀበልንም " - ፋኖ ማርሸት ፀሀይ

በአማራ ክልል ፣ ምስራቅ ጎጃም ታግተዋል የተባሉ የቀን ሰራተኞች ከእገታው ተለቀው በሰላም አዲስ አበባ መግባታቸው ተነግሯል።

የጋርዱላ ዞን አስተዳደር ፤ " በኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ሐይቅ የሚያርፍበት ስፍራን ለመመንጠር ከዞኑ 246 ተመልምለው ሲጓዙ የነበሩና በአማራ ክልል የታገቱ ሠላማዊ ዜግች ተለቀዋል " ብሏል።

ታጋቾቹ ትላትን ምሽት መለቀቃቸውን ያሳወቀው የዞኑ አስተዳደር ዛሬ በሠላም ተጉዘው አዲስ አበባ መድረሳቸውን አሳውቋል።

ወደ ህዳሴው ግድብ ለደን ምንጣሮ ስራ ሲሄዱ የታገቱት 272 ሰራተኞች እንደሆኑ ገልጾ የነበረው ቀጣሪ ድርጅቱ ኒኮቲካ ኮንስትራሽን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል ታጋቾች መለቀቃቸውን አረጋግጧል።

የተለቀቁት ግን 271 ሰራተኞች እንደሆኑና 1 ሰው ሾልኮ መጥፋቱን ነገር ግን ከቤተሰብ ጋር መደዋወሉን አመልክቷል።

ድርጅቱ በመጀመሪያ #ለማስለቀቂያ 4 ሚሊዮን ብር ከፍሎ እንደነበር ተለቀው ሲሄዱ አማኑኤል አካባቢ ድጋሚ በሌላ የቡድኑ ክንፍ ተይዘው ለማስለቀቂያ 6 ሚሊዮን ብር መጠየቁን በኃልም በእያንዳንዱ መኪና 500 ሺህ ብር ተከፍሎ ሰራተኞቹ መለቃቃቸውን አሳውቋል።

' የአማራ ፋኖ ምስራቅ ጎጃም ቃል አቀባይ ' ፋኖ ማርሸት ፀሀይ " ' ሰራተኞች ' የተባሉት ወደ ብርሸለቆ ሲያመሩ የነበሩ ምልምል ወታደሮች ናቸው ፤ ይመሯቸው የነበሩትም ማዕረግ ያላቸው ወታደሮች ነበሩ ፤ ምርኮኞች እንጂ ታጋቾች አይደሉም፤ ቁጥራቸውም 246 ነው " ብለው ነበር።

ትላንትና በሰጡት ቃል ፤ የግለሰቦቹን መለቀቀ አረጋግጠው ፤ " የተለቀቁት 240 ናቸው። አንድም ብር አልተቀበልንም " ብለዋል።

"ልጆቹን እንዲረከበን የቀይ መስቀል ማህበረን ጠይቀን ቀርቷል ፤ ሊቀበለንም አልቻለም። እኛ ከልጆቹ ጋር ባደረግነው ስምምነት የትራንስፖርት ወጪያቸውን ብንሸፍን በቀጥታ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንደሚሄዱ ስለተነጋገርን እነሱም ስላመኑበት ወደ ቤተሰቦቻቸው ሸኝተናቸዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም ፤ " ፋኖ ገንዘብ አይቀበልም። ገንዘብ መቀበል ብንፈልግ ኖሮ እኮ ከሁሉም እንቀበል ነበር። ከአንዱ ተቀብለን ከአንዱ የማንቀበልበት ምክንያት የለም። በስነስርዓት ለመከላከያ ስልጠና የሚመጡ ቤተሰብ ያላቸው ሰዎች ገንዘብ ተጠይቀናል ወደ ሚል ስም ማጥፋት ገብተዋል ምክንያቱም አላማቸው ስለተስተጓጎለ " ብለዋል።

" ገንዘብ ከማንም አልጠየቅንም " የሚሉት ማርሸት " እንደውም ለተሽከርካሪ ነዳጅ ሞልተናል፣ የሹፌሮች አበል ሰጥተናል እውነቱ ይሄ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን ግን ታግተው የነበሩ ሰራተኞች ለማስቅለቅ በቅድሚያ 4 ሚሊያን ብር በሶስት ሰዎች ስም የገባበት ማስረጃ በእጁ እንዳለና በቀመጠልም በእያንዳንዱ መኪና 500 ሺህ ብር በድምሩ 6 ሚሊዮን ብር መክፈሉን አሳውቋል።

የጋርዱላ ዞን እንዳሳወቀው 246 ታጋቾች ተለቀው ዛሬ አዲስ አበባ ደርሰዋል። ታጋቾቹ እንዲለቀቁ የፌዴራል መንግሥት መ/ቤቶች፣ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ፣ የአማራ ክልል የመንግስት አካላት በየደረጃው ያሉ ኃላፊዎች የሃይማኖት ተቋማት ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ጋር በመተባበር ትልቅ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን መረጃ ከጋርዱላ ዞን ኮሚኒኬሽን እንዲሁም ከቪኦኤ ሬድዮ ማግኘቱን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ታጋቾቹ ተለቀው በሰላም #አዲስ_አበባ ገብተዋል " - የጋርዱላ ዞን አስተዳደር " ለማስለቀቂያ መጀመሪያ ከከፈልነው 4 ሚሊዮን ብር በተጨማሪ በእያንዳንዱ መኪና (4 መኪናዎች) 500 ሺህ ብር ከፍለናል " - ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን " አንድም ገንዘብ አልተቀበልንም " - ፋኖ ማርሸት ፀሀይ በአማራ ክልል ፣ ምስራቅ ጎጃም ታግተዋል የተባሉ የቀን ሰራተኞች ከእገታው ተለቀው በሰላም…
" 271 ዜጎችን ከእገታ አስለቅቄያለሁ " - ኮማንድ ፖስት

ላለፉት 25 ቀናት በአማራ ክልል ፣ ምስራቅ ጎጃም ውስጥ በታጣቂዎች እገታ ላይ እንደነበሩ የተነገረላቸው የቀን ሰራተኞች ከእገታ ተለቀው ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል።

በሀገር መከላከያ ሠራዊት የጎጃም ኮማንድ ፖስት አንድ ኮር ፤ ታግተው የነበሩ 271 ዜጎችን ማስለቀቁን አሳውቋል።

ኮማንድ ፖስቱ በአራት አውቶብስ ተጭነው ሲጓዙ የነበሩት 273 ዜጎች እንደሆኑ እና " በምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ማርቆስ እና በኤሊያስ ከተማ መካከል ሲደርሱ ነው በጽንፈኛኞች ታግተዋል " ብሏል።

ታጣቂ ቡድኑ ከ3 ሰዓት በላይ ወደማይታወቅ ቦታ አስገድዶ ከወሰዳቸው በኋላ ሁለቱን #በመረሸን ለቀናት ደብቆ ሲያሰቃያቸው መቆየቱን ገልጿል።

በኃላም " ኮሩ ወደ አካባቢው በመሠማራት ከበባ በማድረግ ምቹ ሁኔታ ሲጠባበቅ መከበቡን የተረዳው ፅንፈኛ ለቋቸው ሊሸሽ ችላል " ሲል አመልክቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋርዱላ ዞን ባገኘው መረጃ በእገታ ላይ የነበሩና ከዞኑ ተመልምለው ለደን ምንጣሮ ስራ ወደ ህዳሴው ግድብ ሲያቀኑ የነበሩ 246 ሰራተኞች ትላንት ምሽት ተለቀው በሰላም አዲስ አበባ ገብተዋል።

ዞኑ ለሰራተኞቹ ከእገታ መለቀቅ ላለፉት ቀናት የፌዴራል መንግሥት ፣ የአማራ ክልል በየደረጃው ያሉ የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ ቀይ መስቀል ትብብር ማድረጋቸውን እና የባለሃብቶች ጥረት እንዳለበትም ጠቁሟል።

የኧሌ ዞንም ፤ " ለጉልበት ስራ ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ሲሄዱ በአማራ ክልል በታጣቂዎች የታገቱ ዜጎች ተለቀዋል " ብሏል።

ዞኑ ፤ መንግሥት እና ባለሃብቱ አድርገዋል ባለው ጥረት ነው ታጋቾች ነፃ የወጡት።

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል አማካኝነትም ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸውን ነው ያመለከተው።

ከዞኑ ተመልምለው የሄዱት 38 የቀን ሰራተኞች ናቸው።

ከላይ ያሉት የሰራተኞች ቁጥር ድምር 284 ሲሆን ቀጣሪው ድርጅቱ ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን ግን ይህን ቁጥር አይቀበለውም ታግተው የነበሩትም 272 ናቸው ነው የሚለው። ለዚህም በቂ የሰነድ ማስረጃ እንዳለው ይገልጻል።

ላለፉት ቀናት ወደ ስፍራው ከፍተኛ የድርጅቱን ኃላፊ በመላክ ሰራተኞቹ ደህንነታቸው ተጠብቆ ምንም ሳይሆኑ እንዲለቀቁ ጥረት ሲያደርግ የቆየው ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን ታጣቂዎቹ በድምሩ 6 ሚሊዮን ብር ወስደው ልጆቹን እንደለቀቋቸው ገልጿል።

መጀመሪያ 4 ሚሊዮን ብር ለማስለቀቂያ በሶስት ሰው ስም ከተከፈለ በኃላ ሰራተኞቹ ተለቀው በ4 መኪና ጉዞ ጀምረው ለዋናው አስፓልት ትንሽ ሲቀራቸው አማኑኤል አቅራቢያ ሌላ የቡድኑ ክንፍ ይዟቸው 6 ሚሊዮን ብር ሲጠይቅ እንደነበር ድርጅቱ ገልጿል።

በኃላ ግን ለእያንዳንዱ መኪና 500 ሺህ ብር በመክፈል በድምሩ አጠቃላይ በ6 ሚሊዮን ብር እንዲለቀቁ መደረጉን ተናግሯል።

እንደድርጅቱ መረጀ ከተለቀቁት 271 ሰዎች አንዱ ሾልኮ የጠፋ ሲሆን በኃላም በስልክ ከቤተሰቦቹ ጋር መነጋገሩ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ትላንት ታጣቂዎች በሩስያ ፣ #ሞስኮ በሚገኘው የክሮከስ አዳራሽ የሙዚቃ ዝግጅት ለመታደም በተሰበሰቡ በርካታ ሰዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ የተገደሉ ሰዎች 115 የደረሱ ሲሆን 100 ሰዎች መቁሰላቸውን የሩሲያ የደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል። ከተገደሉት ውስጥ ህፃናትም እንደሚገኙበት ተነግሯል። 4 ታጣቂዎችን ጨምሮ 11 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሩስያ ባለስልጣናት አሳውቀዋል። የሩሲያ…
#ሩስያ

" ሽብርተኞችን የሚጠብቀው የበቀል እርምጃ ብቻ ነው " - ቭላድሚር ፑቲን

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከትላንትና የሽብር ጥቃት በኃላ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚህም ነገ መጋቢት 15 በመላው ሩሲያ የሀዘን ቀን እንደሚሆን ተናግረዋል። " የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ዜጎቻችን ይዘከሩበታል " ብለዋል።

አሁን ላይ በጥቃቱ ላይ ቀጥታ ተሳትፎ የነበራቸው ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች በቁጥጠር ስር መዋላቸውን ያስታወቁት ፕሬዝዳንቱ፤ ሌላ የጅምላ ግድያ እንዳይፈጸም የጸጥታ ኃሎች ሰፊ ስራ እየሰሩ ነው ብለዋል።

" በትናንትናው የሽብር ጥቃት ላይ የተሳተፈ እና ያገዛቸው የትኛውም አካል ለህግ ይቅርባል " ሲሉ ዝተዋል።

ፕሬዜዳንቱ በትናንትናው የሽብር ጥቃት ላይ የተሳተፉ 4 ወንጀለኞች ወደ ዩክሬን ሊያመልጡ ሲሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጸዋል።

" አሁን ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት እንደሚያመላክተው በዩክሬን በኩል ሽብርተኞች ለማስመለጥ የሚያስችል መንገድ በድንበር በኩል ተዘጋጅቶ እንደነበረ ነው "  ብለዋል።

" ሩሲያ በዚህ የሽብር ጥቃት ላይ የተሳተፉ ሁሉንም አካላት ለይታ ትቀጣለች " ያሉት ፑቲን፤ " ሽብርተኞችን የሚጠብቀው የበቀል እርምጃ ብቻ ነው፤ ከዚህ ውጪ ምንም አማራጭ እና ተስፋ የላቸውም " ሲሉ ዝተዋል። #አልአይን

@tikvahethiopia
" ከእንግዲህ በሽፍትነት / rebel በመሆን መንግሥትን መጣል አይደለም ፤ መነቅነቅ አይቻልም " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " ከእንግዲህ በኃላ በሽፍትነት / rebels በሚመስል ነገር መንግስትን መጣል አይደለም መነቅነቅ እንኳን አይቻልም " አሉ።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ይህን ያሉት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ከፍተኛ እና ታማኝ ግብር ከፋይ ባለሀብቶችን ሰብሰበው በመከሩበት ወቅት ነው።

ታማኝ ከፍተኛ ግብር ከፋዮቹ ለጠ/ ሚኒስትሩ በዛ ያሉ ጥያቄዎችን ያቀረቡላቸው ሲሆን በየአካባቢው ከሚታየው ሁኔታ አንፃር #የሰላም ጉዳይ ከጥያቄዎቹ አንዱ ነበር።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " እኛ የምንፈልገው ሰላም ነው " ብለዋል።

ሰላምን በተመለከተ ያነሷቸው ሃሳቦች ሁሉ ጥሩ እንደሆነ ገልጸው " ሽማግሌ ነን እድሜያችን ልምዳችን ያላችሁ #ሸምግሉ " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

" እኔ የማረጋግጥላችሁ ግን በሽፍትነት / rebels በሚመስል ነገር ከእንግዲህ በኃላ የኢትዮጵያን መንግስት መጣል ሳይሆን መነቅነቅ አይቻልም። በጣም የተለያየን ነን ብቃታችን አይደለም የሚለያየው ያለን conviction ይለያያል እሱ ብር ነው የሚሰበስበው እኛ ስራ ነው የምንሰራውን እናውቃለን እያደረግን ያለነውን በቀላሉ የሚሆን አይመስለኝም " ሲሉ ተደምጠዋል።

" እነሱ ሰዎች ልብ ገዝተው ከመጡ በጣም በጣም በደስታ ነው የምንቀበለው ፤ እናተም ሞክሩ በሁሉም በምትችሉት መንገድ ሞክሩ " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከእንግዲህ በሽፍትነት / rebel በመሆን መንግሥትን መጣል አይደለም ፤ መነቅነቅ አይቻልም " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ " ከእንግዲህ በኃላ በሽፍትነት / rebels በሚመስል ነገር መንግስትን መጣል አይደለም መነቅነቅ እንኳን አይቻልም " አሉ። ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ይህን ያሉት በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ከፍተኛ እና ታማኝ ግብር ከፋይ ባለሀብቶችን ሰብሰበው በመከሩበት ወቅት ነው።…
" በቅርቡ 5 ሚሊዮን ዶላር ከውጭ በአንድ ባንክ ተልኮ ይዘናል " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ሁለት ቦታ (ከመንግስት ጋር እና ጫካ መንግስትን ለመጣል ከሚታገሉ ጋር) የሚጫወቱ አንዳንድ ባለሃብቶች አሉ ሲሉ ተናገሩ።

ይህን የተናገሩት ከታማኝ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ጋር ምክክር ባደረጉበት ወቅት ነው።

ባለሃብቶቹ በምክክር መድረኩ ስለ #ሰላም ጉዳይ ያነሱ ሲሆን ጠ/ሚስትሩም ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ፤ " ሰላም ተብሏል እውነት ነው አስፈላጊ ነው " ብለዋል።

" ድሮ ሀብታሞች አዝማሪ ቀጥረው ያጫውቱ ፣ ይገጠምላቸው ነበር ድሃው እራት እየበላ በግጥም ይተባበራል ፤ አሁን ድገሞ ሀብታሞች #ዩትዩበር ይቀጥራሉ ድሃው በላይክ እና ሼር ይተባበራቸዋል እነዚህ ሰዎች እንደፈለጉ ሲያተረማምሱ ይውላሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ዩትዩበሮቹን ባንቀልብ ወደ ስራ ወደ ኢንድስትሪ ይገቡ ነበር ፤ ለዚህ አስተዋጽኦአችን ምንድነው ብሎ ስራ ፈጣሪው ባለሃብቱ ግብር ከፋዩ ቢያስብ ጥሩ ነው " ብለዋል።

" እኛ እና እናተ ከተባበርን ሙስና ይቀንሳል፣ አገልግሎት ሊሻሻል ይችላል " ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ " ጫካ ላሉ ሰዎች ብር ባለመላክ ብትተባበሩም እንዲሁ ይቀንሳል " ሲሉ ተናግረዋል።

" አንዳንድ በተለያየ ቦታ ሚታገሉን ሰዎች እስከ 10 ቤት በአባቱ፣ በወንድሙ  ያለው ሰው አለ፤ በረሃ ታጋይ አታጋይ የሚባል ሰው። በጣም ሃብታሞች ናቸው እዛ ተቀምጠው መነገድ የሚቻል ከሆነ ሰላም ጋር ምን አመጣቸው ሰላም ከመጣ ንግድ የለም ማለት ነው " ብለዋል።

" ቤት አላቸው፣ በተለያየ አካውንት ባንክ ውስጥ ገንዘብ አላቸው በቅርቡ እንኳን 5 ሚሊዮን ዶላር ከውጭ መጥቶ ይዘናል በአንድ #ባንክ ፣ ከፍተኛ ብር ይንቀሳቀሳል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሃብታሞች ማወቅ ፣ መብለጥ ፣ መላቅ ስለሚመስላቸው እዚህም ይጫወታሉ እዚያም ይጫወታሉ፤ እዚህ እኛን ' የተከበራችሁ ' ይላሉ እዛ ሄደው ' እንደናተ ጀግና የለም ' ይላሉ በዚህ ሰዎቹ እየተታለሉ እንደ ስራ መስክ ይዘውት ሀገር ያምሳሉ ወጣቶች ያልቃሉ ... ችግር አለ " ብለዋል።

" እናተም ልክ የድሃ ቤት እንደምትገነቡት ሁሉ በዚህም በኩል ችግሮች እንዲፈቱ ከልባችሁ ብታግዙ ያለው ነገር ይቀንሳል " ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ምንም እንኳን ስም ባይጠቅሱም ከሀገር የወጡ ባለሃብቶች እንዳሉ ገልጸዋል።

" የሆኑ የሆኑ ሰዎች ጠፍተው ይሄዳሉ ከዚህ። ከቆየ በኃላ ስንሰማ ለምንድነው የጠፋው ሚስተር X ጥሩት ወደሀገሩ ይመለስ ሲባል ሚስተር X አይፈልግም ያደረጋቸው ትራዛክሽኖች ሁሉ ይታወቃሉ ብሎ ስለሚያስብ አይፈልግም " ብለዋል።

" እኛ እንደ መንግስት አንድም ባለሃብት ከሆነ ክልል ጋር ግጭት ስላለ ከሀገር ውጣ ያልነው የለም " ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ከመጋቢት 22 ቀን 2015 ዓ/ም በፊት የባንክ ፈቃድ የተሰጠባቸው ተሽከርካሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ተፈቀደ። ተሽከርካሪዎቹ እና እቃዎች ወደ ሀገር ቤት እንዲገቡ የተፈቀደው በጉምሩክ ኮሚሽን በኩል የሚቀርቡ ሠነዶች አስፈላጊው ማጣራት ተደርጎባቸው ነው ተብሏል። ይህም የሚሆነው ለመጨረሻ ጊዜ  መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ለጉምሩክ ኮሚሸን ከፃፈው ደብዳቤ አሳውቋል። የውጪ ምንዛሬ…
#Update

በጂቡቲ ወደብ ላይ የቆይታ ጊዜያቸው ያለፈ ተሸከርካሪዎች በባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ተጓጉዘው ወደ አገር ከገቡ በኋላ ድሬዳዋ ደረቅ ወደብ እንዲቆዩ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ማስታወቁን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ሚኒስቴሩ ፦
➡️ ለባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት
➡️ ለጉምሩክ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ፣ የተሽከርካሪዎቹ አስመጪዎች በሚያቀርቡት መረጃ መሠረት፣ በየወቅቱ በጂቡቲ ወደብ የተከማቹ ተሽከርካሪዎችን መጠንና የቆይታ ጊዜ ከጂቡቲ ወደብ ባለሥልጣንና ከጉሙሩክ ኮሚሽን እንዲሰበሰብ አዟል፡፡

የባህር ትራንስፖርት የሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የወደብ ፎርማሊቲ አሟልቶ ተገቢ ክፍያ በመፈጸምና በድሬዳዋ ደረቅ ወደብ ማከማቻ ሥፍራ በማዘጋጀት ተለዋጭ ውሳኔ እስኪሰጥ በራሱ ኃላፊነት እና በራሱ ወጪ ተሽከርካሪዎቹን እንዲያቆይ ተወስኗል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን በበኩሉ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በሚሰጠው የደብዳቤ ዋስትና፣ ተሽከርካሪዎቹ ቀረጥና ታክስ ሳይከፈልባቸው እንዲጓጓዙ የትራንዚት ፈቃድ እንዲሰጥ የገንዘብ ሚኒስቴር አሳስቧል፡፡ 

የገቢዎች ሚኒስቴር ለጉምሩክ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ፣ በጂቡቲ ወደብ ተከማችተው የሚገኙ ተሽከርካሪዎች ድሬዳዋ ደረቅ ወደብ እንዲጓጓዙ መወሰኑን አስታውቆ፣ በውሳኔው መሠረትም አስመጪዎች ንብረቶቻቸውን ወደ ደረቅ ወደብ እንዲያስገቡ አሳስቧል፡፡

ነዳጅ ለማስመጣት የሚወጣውን የውጭ ምንዛሪ ጫና ለመቀነስ በሚል በነዳጅ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር እንዳይገቡ ውሳኔ መተላለፉን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ከዚህ ቀደም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ወደ አገር በስፋት እንዲገቡ የኤክሳይስ ታክስ አዋጅ ማሻሻያ መደረጉን መግለጹ አይዘነጋም፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ከባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት ምንጭ አገኘሁት ባለው መረጃ፣ አሁን ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ የተባሉት የነዳጅ ተሽከርካሪዎች ከዕግዱ በፊት የተገዙ ናቸው።

በውጭ ምንዛሪና በፍራንኮ ቫሉታ ምክንያት በጂቡቲ ወደብ እንዲቆዩ የተደረጉ መሆናቸውን፣ ውሳኔው የተላለፈው ለተሽከርካሪዎቹ የሚከፈለው የወደብ ኪራይ እየጨመረ በመምጣቱ መሆኑ ተመላክቷል።

ተሸከርካሪዎቹ ድሬዳዋ ደረቅ ወደብ እንዲገቡ ከተደረገ በኋላ፣ ሰነድ ያላቸው የተሽከርካሪ አስመጭዎች ድርጅቱ ያወጣውን የታክስና የመጓጓዣ ወጪ በመክፈል መረከብ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።

ስማቸውን እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የተሽከርካሪ አስመጪ " የአንድ ዓመት የወደብ ኪራይና የመጓጓዣ ወጪዎችን በመክፈል ተሽከርካሪዎቹን ቢረከቡ ገበያ ውስጥ ዋጋቸው ስለሚንር ሥጋት ገብቶናል " ብለዋል፡፡

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ምዕመናን #ክርስቲያናዊ_አለባበስ ለብሳችሁ እንድትገኙ እና የአቅማችሁን ያህል እድትለግሱ ጥሪ እናቀርባለን " - ማህበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን " ኑ ቸርነትን  እናድርግ " በሚል መሪ ቃል ነገ እሁድ ከቀኑ 7:00 ላይ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል። ገቢ ማሰባሰቢያው…
#Update

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን " ኑ ቸርነትን  እናድርግ " በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃግብር በሚሊኒየም አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል።

ገቢ ማሰባሰቢያው በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ባጋጠመው ማኅበራዊ ቀውስና ድርቅ የተጎዱ ወገኖቻችንን ፣ ገዳማትና አብነት ት/ቤቶችን ለመደገፍ የሚውል እንደሆነ ተገልጿል።

በመርሃግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት  የማኅበሩ ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም ፤ " የመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማ ባለን አቅም ሁሉ ለወገን መድረስ ነው " ብለዋል።

" ረሃብ ጊዜ አይሰጥም " ያሉት የማህበሩ ሰብሳቢ " በውጭ ድርጅቶች ፣ በመንግስትና በሌሎችም የተለያዩ አካላት ብዙ እርዳታዎች ይደረጋሉ (የምግብም የአይነትም) በተለይ ግን ገዳማትና አብነት ት/ቤቶች ብዙ ጊዜ ትኩረት አያገኙም " ብለዋል።

" እነዚህን ክፍተቶች እና ጉድለቶች መሙላት አለብን " ሲሉ አስገንዝበዋል።

" አሁን ላይ በየቦታው ያሉት መፈናቀሎች ፣ በየቦታው ያሉ የረሃብ ችግሮችን በማሰብ ማህበረ ቅዱሳን ሌሎች አገልግሎቶችን ገቶ መጀመሪያ ነፍስን የማዳን፤ ህይወትን የመታደግ ስራ ይቀድማል ብሎ እየሰራ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሁሉን ማድረግ የምንችለው ስንኖር ነው " ያሉት ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ " እኛ በልተን እያደርን ሌሎች ወገኖቻችን በረሃብ እና ጥማት መሞት ስለሌለባቸው ' ኑ ቸርነትን እናድርግ ! ' በሚል በዚህ በታላቁ ዐብይ ጾም ወቅት ዝግጅቱ መዘጋጀቱን ጠቁመዋል።

ዛሬ ሚሊኒየም አዳራሽ መገኘት ያልቻሉ ምዕመናን በየቤታቸው ሆነው በማህበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም የሂሳብ ቁጥሮች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 ፣ አሃዱ ባንክ 0025393810901 ፣ ወጋገን ባንክ 0837331610101 ፣ አቢሲንያ ባንክ 37235458 ፣ አዋሽ ባንክ 01329817420400 ድጋፍ ማድረግ ይቻላሉ ተብሏል።

ፎቶ ፦ ከማኅበረ ቅዱሳ ቴሌቪዥን

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia