TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ ፦ የ2016 ዓ/ም የሆራ አርሰዲ ኢሬቻ በዓል በቢሾፍቱ እየተከበረ ይገኛል።

#TikvahFamilyBishoftu / #ENA

@tikvahethiopia
" ለባለቤቷ ለቅሶ የተቀመጠችው በዚሁ አደጋ ወላጅ እናቷንም አጥታለች " - የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

ትላንት በአዲስ አበባ ሸጎሌ አካባቢ አንድ የከተማ አውቶብስ ለለቅሶ የተጣለ ድንኳን ጥሶ በመግባት ባደረሰው ጉዳት የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ።

አደጋው ከምሽቱ 1 ሰዓት የደረሰ ሲሆን በአደጋውን እስከ ትናንት ምሽት ድረስ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ከ20 በላይ ሰዎች ላይም ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በአደጋው ጉዳት  ከደረሰባቸው ተጎጂዎች መካከል የተወሰኑትን የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የቅድመ ሆስፒታልና አምቡላንስ አገልግሎት ባለሞያዎች ሕክምና እያደረጉላቸው ወደ-ሆስፒታል አድርሰዋቸዋል።

የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ፤ በድንኳን ውስጥ ለባለቤቷ ለቅሶ የተቀመጠችው በዚሁ አደጋ ወላጅ እናቷንም አጥታለች ሲል ገልጿል።

ህይወታቸውን ያጡትና ጉዳት የደረሰባቸውም ሀዘንተኛዋን ለማጽናናት በድንኳን ውስጥ የተቀመጡ ናቸው ብሏል።

ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል በአስጊ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ያሉ ሲሆን ተጎጂዎቹ በአቤትና በራስ ደስታ ሆስፒታል ሕክምና እየተደረገላቸው ነው ተብሏል፡፡

መረጃው የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ነው።

@tikvahethiopia
#Update #MoE #Result

ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል።

ሚኒስቴሩ ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:30 ጀምሮ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን በተመለከተ በሚኒስቴሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል።

በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል ተፈርሞ ለተለያዩ የመገናኛ ብዙሃን ደብዳቤ ተልኳል።

ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ (@tikvahuniversity) ለመገናኛ ብዙሃን የተላከውን ደብዳቤ ትክክለኛነት #አረጋግጧል

በሐምሌ 2015 ዓ.ም መጨረሻ በሁለት ዙር የተሰጠውን የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ 840 ሺህ በላይ ተፈታኞች መውሰዳቸው ይታወሳል።

More Tikvah Ethiopia University 👇
https://t.iss.one/+RYD_4tbNBwRoKR2h

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #MoE #Result ትምህርት ሚኒስቴር በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል። ሚኒስቴሩ ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:30 ጀምሮ የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን በተመለከተ በሚኒስቴሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣል። በሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል ተፈርሞ ለተለያዩ…
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ  ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጿል።

@tikvahethiopia
ልገሳዎን ቀጥታ ያድርሱ!
EthioDirect
***********
በኢትዮ-ዳይሬክት ለተቸገረ ወገንዎ ወይም ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች ልገሳዎን ቀጥታ ወደ ሂሳባቸው ይላኩ!
#ቀላል #ፈጣን #አስተማማኝ #ነፃ
=============
የEthioDirect የሞባይል መተግበሪያ ከPlay Store ወይም  App Store በማውረድ  አገልግሎቱን ይጠቀሙ።
• ለአንድሮይድ ስልኮች
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.combanketh.ethiodirect
• ለአፕል ስልኮች
https://apps.apple.com/us/app/ethiodirect/id1602064491
#SouthWestEthiopia

በአንድ ሞተር ላይ ሆነው ሲጓዙ የነበሩ 3 ሰዎች ከአይሱዙ መኪና ጋር ተጋጭተው የሁሉም ህይወት ወዲያው ማለፉ ተሰማ።

ይህ አሰቃቂ አደጋ የደረሰው ትላንት መስከረም 26 ቀን 2016 ዓ/ም ልክ ከቀኑ 8:10 ላይ  በኮንታ ዞን ኮንታ ኮይሻ ወረዳ 01 ቀበሌ ልዩ ስሙ " ጥሴ " ተብሎ የሚጠራው አካባቢ ነው።

እንደ ፖሊስ መረጃ መነሻውን ከመንደር 11 ወደ ኮይሻ ገበያ 3 ሰዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ሞተር ከኮይሻ ገበያ ወደ መንደር 11 ይጓዝ የነበረ የጭነት አይሱዚ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ የሞተሩ አሽከርካሪ እና 2 ተሳፋሪዎች ወዲያውኑ ህይወታቸዉ አልፏል።

መረጃው ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን የተገኘ ነዉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

• የሞቱ እስራኤላውያን ከ700 በላይ ሆነዋል። ከ350 በላይ ፍልሥጤማውያንም ህይወታቸው ጠፍቷል።

#ኢራን ፍልስጤምን ደግፋ ስትቆም ፤ #አሜሪካ ከእስራኤል ጎን መሆኗን አረጋግጣ ወታደራዊ ድጋፍ ማድረግ እንደምትጀምር አሳውቃለች።

በእስራኤል ጦርና በፍልስጤሙ ሃማስ መካከል ጦርነቱ ዛሬም ተባብሶ መቀጠሉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በተለይም እስራኤል ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች ብርቱ ውጊያ እየተካሄደ ነው ተብሏል።

በጦርነቱ እስራኤል ውስጥ ከ700 በላይ #እስራኤላውያን መገደላቸው ተሰምቷል።

እስራኤል ተከፍቶብኛል ላለችው ጦርነት እየወሰደች ባለችው የአፀፋ እርምጃ በጋዛ ሰርጥ ከ350 በላይ #ፍልጤማውያን ተገድለዋል።

በአጠቃላይ ባለፉት ሰዓታት ብቻ እስካሁን ይፋ በተደረገው ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች ሞተዋል።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተጎድተዋል።

ጋዛ ውስጥ መሰረተልማቶች ፣ ህንፃዎች እንዳልነበሩ ሆነዋል፣ የኤሌክትሪክ ፣ የነዳጅና የፍጆታ እቃዎች አቅርቦት ተቋርጧል ፤ ያለው ሁኔታ እጅግ የከፋ ነው ተብሏል። ሰብዓዊ እርዳታ የሚገባበት መንገድ እንኳን የለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እስራኤል የሊባኖሱ ሂዝቦላህ ከፍቶብኛል ላለችው ተኩስ በሊባኖስ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈፅማለች።

ሂዝቦላም እስራኤል ላይ ተኩስ ስለመክፈቱ ኃላፊነቱን ወስዷል።

ተኩሱ የተከፈተው እስራኤል፣ ሊባኖስ እና ሶሪያ በሚወዛገቡበት ግዛት እና ሶስቱንም ሃገራት በሚያገናኛቸው የዶቭ ተራራ አካባቢ ነው።

እስራኤል የሊባኖስ ታጣቂ ሂዝቦላህ በውጊያው ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ አስጠንቅቃለች።

ሃማስ ፤ እስራኤል በወረራ ከያዘቻቸው ግዛቶች ለመጠራረግ ፍልስጥኤማውያን እንዲሁም ሌሎች አረቦች ትግሉን እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል።

እስራኤል ያለጥርጥር በበርካታ ግንባሮች ሊከፈት የሚችል ጦርነት ሊኖር እንደሚችል ነው እየታያት ያለው ተብሏል።

ምናልባትም ጦርነቱ የከፋ የሚሆነው ከፍተኛ ኃይል ያለውን የሊባኖሱን ታጣቂ ቡድን ሂዝቦላ መሳብ ከቻለ እንደሆነ ተነግሯል።

በእስራኤል እና የፍልስጤም ሃማስ ጦርነት ሀገራት የተለያዩ አቋማቸውን እያንፀባረቁ ሲሆን ኢራን የሃማስን ጥቃት ደግፋ ቆማለች።

ኢራን " የፍልስጤምን ሕጋዊ የመከላከል መብት እደግፋለሁ " ብላለች።

አሜሪካ በበኩሏ ከእስራኤል ጎን እንደሆነች በተደጋጋሚ እያረጋገጠች ነው ፤ ወታደራዊ ድጋፍም ለማድረግ እየተዘጋጀች መሆኑ ተሰምቷል። የአሜሪካ መከላከያ ድጋፉን ከዛሬ ጀምሮ የሚልክ ሲሆን በመጪዎቹ ቀናት ይደርሳል ተብሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የእስራኤል ጦር ከፍተኛ በሆነ ሁኔታ ወታደሮቹን እያሰማራ ሲሆን በጋዛ ላይ ተከታታይ የአየር ጥቃቶችን ከማድረግ በተጨማሪ የምድር ላይ ዘመቻ ለማድረግ ማቀዱን ተሰምቷል።

መረጃው ከቢቢሲ እና አልጀዚራን ጨምሮ ከሌሎች ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተገኘ ነው።

More - @BirlikEthiopia

@tikvahethiopia