በተመጣጣኝ ዋጋ የቀረቡትን የሳፋሪኮም ቲክቶክ ጥቅሎችን በመጠቀም አዳዲስ ቪዲዮዎችን እየሰራን ለምንወዳቸው ሰዎች እንላክ፣ ዘና ፈታ እንበል!
አሁኑኑ ወደ *777# በመደወል ጥቅላችንን እንግዛ!
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
አሁኑኑ ወደ *777# በመደወል ጥቅላችንን እንግዛ!
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " - የጋቦን ወታደሮች በጋቦን መፈንቅለ መንግሥት ተደረገ። ባሳለፍነው ቅዳሜ በአፍሪካዊቷ ሀገር ጋቦን ምርጫ ተደርጎ ነበር በዚህም ምርጫ ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር። ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮችየተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን መቆጣጠራቸውን አሳውቀዋል። በአገሪቱ…
#Update
የጋቦን ወታደሮች አሊ ቦንጎን የቤት ውስጥ እስረኛ አድርገዋቸዋል።
መፈንቅለ መንግሥት የተደረገባቸው ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ካሉበት ቤት ውስጥ ሆነው " እርዱኝ " የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ለወዳጆቻቸው በቪድዮ አሰራጭተዋል።
ምንጩ በትክክል ባልታወቀውና በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰጨው ቪድዮ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ " በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ሁሉ ድምፅ እንዲያሱም " ተማፅነዋል።
" እዚህ ያሉ ሰዎች እኔን እና ቤተሰቦቼን አስረዋል ፤ ልጄ የሆነ ቦታነው ያለው፤ ባለቤቴ ሌላ ቦታ ነች ፤ እኔ ደግሞ አሁን ያለሁት በመኖሪያ ቤቴ ውስጥ ነው። ምንም እየተፈጠረ አይደለም ፤ ምን እየሆነ እንዳለም አላውቅም። " ብለዋል።
በመሆኑም በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ድምፅ እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል።
ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለት በጋቦን ምርጫ ተደርጎ የነበር ሲሆን በምርጫው ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር።
ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮች የተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን ተቆጣጥረዋል።
ወታደራዊ አመራሮች በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት " የጋቦንን አስተዳደር ይዘናል " ብለዋል።
" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" አስተዳደሩ ኃላፊነት የጎደለውና ወዴት እንደሚሄድ የማይታወቅ ስለሆነ የአገሪቱን ማኅበራዊ ኑሮ በማመሳቀል ወደ ቀውስ ከቶናል " ሲሉም ተናግረዋል።
ወታደሮቹ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ያሸነፉበትን የምርጫውን ውጤት ሰርዘውታል።
በወታደራዊ አመራሮች ከሥልጣን ተወግዷል የተባለው የአሊ ቦንጎ ቤተሰብ ጋቦንን #ለ56_ዓመታት መርቷል ፤ ከነዚህ አመታት ውስጥ አሊ ቦንጎ ብቻቸው 14 ዓመት ሀገሪቱን መርተዋል።
@tikvahethiopia
የጋቦን ወታደሮች አሊ ቦንጎን የቤት ውስጥ እስረኛ አድርገዋቸዋል።
መፈንቅለ መንግሥት የተደረገባቸው ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ካሉበት ቤት ውስጥ ሆነው " እርዱኝ " የሚል ይዘት ያለው መልዕክት ለወዳጆቻቸው በቪድዮ አሰራጭተዋል።
ምንጩ በትክክል ባልታወቀውና በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በተሰጨው ቪድዮ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ " በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ሁሉ ድምፅ እንዲያሱም " ተማፅነዋል።
" እዚህ ያሉ ሰዎች እኔን እና ቤተሰቦቼን አስረዋል ፤ ልጄ የሆነ ቦታነው ያለው፤ ባለቤቴ ሌላ ቦታ ነች ፤ እኔ ደግሞ አሁን ያለሁት በመኖሪያ ቤቴ ውስጥ ነው። ምንም እየተፈጠረ አይደለም ፤ ምን እየሆነ እንዳለም አላውቅም። " ብለዋል።
በመሆኑም በዓለም ዙሪያ ያሉ ወዳጆቻቸው ድምፅ እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል።
ባሳለፍነው ቅዳሜ ዕለት በጋቦን ምርጫ ተደርጎ የነበር ሲሆን በምርጫው ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎ ማሸናፋቸው ተነግሮ ነበር።
ነገር ግን የሀገሪቱ ወታደሮች የተካሄደውን ምርጫ ውጤት በመሻር ፕሬዝዳንት አሊ ቦንጎን ከስልጣን ገልብጠው መንበሩን ተቆጣጥረዋል።
ወታደራዊ አመራሮች በሀገሪቱ ቴሌቪዥን ባስተላለፉት መልዕክት " የጋቦንን አስተዳደር ይዘናል " ብለዋል።
" ይሄንን ሙሰኛ አስተዳደር በማስወገድ ሰላምን ለማስፈን ወስነናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" አስተዳደሩ ኃላፊነት የጎደለውና ወዴት እንደሚሄድ የማይታወቅ ስለሆነ የአገሪቱን ማኅበራዊ ኑሮ በማመሳቀል ወደ ቀውስ ከቶናል " ሲሉም ተናግረዋል።
ወታደሮቹ ፕሬዜዳንት አሊ ቦንጎ ያሸነፉበትን የምርጫውን ውጤት ሰርዘውታል።
በወታደራዊ አመራሮች ከሥልጣን ተወግዷል የተባለው የአሊ ቦንጎ ቤተሰብ ጋቦንን #ለ56_ዓመታት መርቷል ፤ ከነዚህ አመታት ውስጥ አሊ ቦንጎ ብቻቸው 14 ዓመት ሀገሪቱን መርተዋል።
@tikvahethiopia
ጅግጅጋ የሆነው ምንድነው ?
ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል።
የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል።
ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል።
ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎችን በመያዙ ሂደት ላይ ሰዎችን ለይቶ በአፈሳ የማሰር ድርጊት እንደነበር ቃላቸውን የሰጡ የጅግጅጋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጅግጅጋ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፤ ከህፃኗ መደፈር ድርጊት ጋር በተያያዘ ሰኞ 4 ተጠርጣሪዎች ቢያዙም በከተማው ሰፊ አፈሳ ሲደረግ ነበር ብለዋል።
በተለይም ከደቡብ አካባቢ የመጡ ልጆች በድርጊቱ ላይ በመጠርጠራቸው ይህን መሰረት ያደረገ እስር ሲፈፀም እንደነበር ገልጸዋል። ድርጊቱ እስከ ትላንት ድረስ መቀጠሉን ጠቁመዋል።
አንድ ሌላ ነዋሪ ድርጊቱ እጅግ በጣም አሰቃቂና አስደንጋጭ እንደነበር ገልጸው ከተጠርጣሪዎች አያያዝ ጋር በተያያዘ በፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው ድርጊት ተገቢ አይደለም ብለዋል።
" ተጠርጣሪዎችን በልዩነት ማሰር እየተቻለ ሰዎች በአፈሳ ወደ ማቆያ ሲገቡ ነበር ይህ ተገቢ ያልሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላ አንድ ነዋሪ ደግሞ ፤ " እሁድ እለት አንድ ልጅ ተደፈራ ከተገደለች በኃላ ድርጊቱን የፈፀሙ ግለሰቦች ተይዘው ለህግ ቀርበዋል " ብለዋል።
" ይሄ ጥሩ ነው " ያሉት እኚሁ ነዋሪ ነገር ግን ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የለላቸውን ሰዎች ፓሊስ በጅምላ በማፈስ ማሰረሱን ፣እና መደብደቡን ጠቁመዋል።
በነበረው ሁኔታ የሰዎች ህይወት ማለፉን እንደሰሙ ገልጸዋል።
በተለይ ከደቡብ የመጡ ወጣቶችን መታወቅያ በማየት እስር ፣ ድብደባ ሲፈፀም ነበር ይህን የሚመለከተው አካል ይወቀው ሲሉ ገልጸዋል።
የሶማሌ ክልል መንግሥት ግን ከአሰቃቂው የወንጀል ድርጊት በኃላ ተፈፅሟል የተባለው ድርጊት #አሉባልታ እና #ሀሰተኛ ነው ብሏል።
የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብድቃድር ረሽድ ፤ " በሱማሌ ክልል የሌላ ክልል ተወላጆች እየታፈሡ እየታሰሩ ፣እየተገደሉ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው አሉባልታ ወሬ ነው " ያሉ ሲሆን የሚንገረው ሁሉ ውሸት ነው ብለዋል።
" የሶማሌ ህዝብ ሰፊ ህዝብ ነው አቃፊ ነው ፣ ከየትኛውም ህዝብ ጋር የመኖር ባህል ያለው ማህበረሰብ ነው ፤ የሌላ ኢትዮጵያዊ ተወላጅ የማሳደድ፣ የመግደል ባህል ፈፅሞ የለውም የሚነገረው ሁሉ ውሸት ነው፤ የሶማሌ ህዝብን ስም ለማንቋሸሽ የሚሰራ ፕሮፖጋንዳ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" የህግ አካላት ቦታው ላይ ሳይደርሱ ሁከት ለመፍጠር ሙከራ ተደርጎ ነበር " ያሉት ኃላፊው የህግ አካላት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ የወሰዱት እርምጃዎች ነበሩ ብለዋል።
" እነዛም መቆያ አካባቢዎች ለደህንነታቸው ስጋት የቆዩ አካላት በማጣራት ወደመደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ትላንት በፀጥታ አካላት መመሪያ ተሰጥቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።
" በሶማሌ ክልል ምንም ችግር የለም ሰላም ነው ፤ የሶማሌ ህዝብ አቃፊ ነው " ያሉት ኃላፊው የፖለቲካ አጀንዳ በማድረግ ተቃውሞ በመፍጠር ብጥብጥ ለመፍጠር ፣ በክስተቶች ላይ ክስተት በማጋነን ፣ እከሌ ተገደለ፣ እከሌ ዘሩ እንዲህ ነው በማለት ለፖለቲካ የሚጠቀሙ ኃይሎች አሉ " ብለዋል።
" የሶማሌ ክልል ሰላም ነው ፤ ሁሉም ወደ መደበኛው ስራ ተመልሷል " ሲሉ አክለዋል።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል።
የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል።
ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል።
ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎችን በመያዙ ሂደት ላይ ሰዎችን ለይቶ በአፈሳ የማሰር ድርጊት እንደነበር ቃላቸውን የሰጡ የጅግጅጋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።
አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጅግጅጋ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፤ ከህፃኗ መደፈር ድርጊት ጋር በተያያዘ ሰኞ 4 ተጠርጣሪዎች ቢያዙም በከተማው ሰፊ አፈሳ ሲደረግ ነበር ብለዋል።
በተለይም ከደቡብ አካባቢ የመጡ ልጆች በድርጊቱ ላይ በመጠርጠራቸው ይህን መሰረት ያደረገ እስር ሲፈፀም እንደነበር ገልጸዋል። ድርጊቱ እስከ ትላንት ድረስ መቀጠሉን ጠቁመዋል።
አንድ ሌላ ነዋሪ ድርጊቱ እጅግ በጣም አሰቃቂና አስደንጋጭ እንደነበር ገልጸው ከተጠርጣሪዎች አያያዝ ጋር በተያያዘ በፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው ድርጊት ተገቢ አይደለም ብለዋል።
" ተጠርጣሪዎችን በልዩነት ማሰር እየተቻለ ሰዎች በአፈሳ ወደ ማቆያ ሲገቡ ነበር ይህ ተገቢ ያልሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላ አንድ ነዋሪ ደግሞ ፤ " እሁድ እለት አንድ ልጅ ተደፈራ ከተገደለች በኃላ ድርጊቱን የፈፀሙ ግለሰቦች ተይዘው ለህግ ቀርበዋል " ብለዋል።
" ይሄ ጥሩ ነው " ያሉት እኚሁ ነዋሪ ነገር ግን ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የለላቸውን ሰዎች ፓሊስ በጅምላ በማፈስ ማሰረሱን ፣እና መደብደቡን ጠቁመዋል።
በነበረው ሁኔታ የሰዎች ህይወት ማለፉን እንደሰሙ ገልጸዋል።
በተለይ ከደቡብ የመጡ ወጣቶችን መታወቅያ በማየት እስር ፣ ድብደባ ሲፈፀም ነበር ይህን የሚመለከተው አካል ይወቀው ሲሉ ገልጸዋል።
የሶማሌ ክልል መንግሥት ግን ከአሰቃቂው የወንጀል ድርጊት በኃላ ተፈፅሟል የተባለው ድርጊት #አሉባልታ እና #ሀሰተኛ ነው ብሏል።
የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብድቃድር ረሽድ ፤ " በሱማሌ ክልል የሌላ ክልል ተወላጆች እየታፈሡ እየታሰሩ ፣እየተገደሉ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው አሉባልታ ወሬ ነው " ያሉ ሲሆን የሚንገረው ሁሉ ውሸት ነው ብለዋል።
" የሶማሌ ህዝብ ሰፊ ህዝብ ነው አቃፊ ነው ፣ ከየትኛውም ህዝብ ጋር የመኖር ባህል ያለው ማህበረሰብ ነው ፤ የሌላ ኢትዮጵያዊ ተወላጅ የማሳደድ፣ የመግደል ባህል ፈፅሞ የለውም የሚነገረው ሁሉ ውሸት ነው፤ የሶማሌ ህዝብን ስም ለማንቋሸሽ የሚሰራ ፕሮፖጋንዳ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" የህግ አካላት ቦታው ላይ ሳይደርሱ ሁከት ለመፍጠር ሙከራ ተደርጎ ነበር " ያሉት ኃላፊው የህግ አካላት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ የወሰዱት እርምጃዎች ነበሩ ብለዋል።
" እነዛም መቆያ አካባቢዎች ለደህንነታቸው ስጋት የቆዩ አካላት በማጣራት ወደመደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ትላንት በፀጥታ አካላት መመሪያ ተሰጥቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።
" በሶማሌ ክልል ምንም ችግር የለም ሰላም ነው ፤ የሶማሌ ህዝብ አቃፊ ነው " ያሉት ኃላፊው የፖለቲካ አጀንዳ በማድረግ ተቃውሞ በመፍጠር ብጥብጥ ለመፍጠር ፣ በክስተቶች ላይ ክስተት በማጋነን ፣ እከሌ ተገደለ፣ እከሌ ዘሩ እንዲህ ነው በማለት ለፖለቲካ የሚጠቀሙ ኃይሎች አሉ " ብለዋል።
" የሶማሌ ክልል ሰላም ነው ፤ ሁሉም ወደ መደበኛው ስራ ተመልሷል " ሲሉ አክለዋል።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጅግጅጋ የሆነው ምንድነው ? ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል። የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል። ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል። ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት…
#ጅግጅጋ
ከሶማሌ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን በተገኘው መረጃ በጅግጅጋ ከተማ የ9 ዓመቷን ልጅ #ደፍረው_ገድለዋል ተብለው የተጠረጠሩት 4 ተጠርጣሪዎች በአባቷ ቤት ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ናቸው።
በልጅቷ አባት ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር ከተባሉት ከአራቱ ተጠርጣሪዎች አንዱ ላይ በዋናነት ምልክቶች እንደሚታዩ የክልሉ መንግሥት አሳውቋል።
ከሚታዩት ምልክቶች አንዱ ፤ ልጅቷን ሲደፍሯት የጥፍሮቿ ምልክት እንዲሁም ደም ይታይበታል ተብሏል።
የወንጀሉ ድርጊት ምርመራ አሁንም እየተካሄደ ሲሆን ክልሉ ምርመራው እንዳለቀ ለህዝብ ይፋ አደርጋለሁ ብሏል።
@tikvahethiopia
ከሶማሌ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን በተገኘው መረጃ በጅግጅጋ ከተማ የ9 ዓመቷን ልጅ #ደፍረው_ገድለዋል ተብለው የተጠረጠሩት 4 ተጠርጣሪዎች በአባቷ ቤት ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ናቸው።
በልጅቷ አባት ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር ከተባሉት ከአራቱ ተጠርጣሪዎች አንዱ ላይ በዋናነት ምልክቶች እንደሚታዩ የክልሉ መንግሥት አሳውቋል።
ከሚታዩት ምልክቶች አንዱ ፤ ልጅቷን ሲደፍሯት የጥፍሮቿ ምልክት እንዲሁም ደም ይታይበታል ተብሏል።
የወንጀሉ ድርጊት ምርመራ አሁንም እየተካሄደ ሲሆን ክልሉ ምርመራው እንዳለቀ ለህዝብ ይፋ አደርጋለሁ ብሏል።
@tikvahethiopia
በፈጣኑ እና አስተማማኙ የሳፋሪኮም ሜጋ ኢንተርኔት ጥቅል የቤተሰባችንን ጨዋታ እርቀው ላሉ ዘመዶቻችን ያለምንም መቆራረጥ እናጋራ! ወደ *777# በመደወል ዛሬውኑ እንግዛ።
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#AAU አንጋፋው የ " #አዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ " በሀገሪቱ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆነ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የራስ ገዝ ማቋቋሚያ ደንብ ላይ ተወያይቶ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ እንዲሆን ወስኗል። ውሳኔው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአካዳሚክ ነጻነት እንዲረጋገጥ፣ ከፖለቲካዊም ሆነ አስተዳደራዊ…
#AAU
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ #የአዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ።
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #ቻንስለር ተደርገው በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተሹመዋል።
ሹመቱ የተሰጣቸው፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ እንዲቋቋም እንዲቋቋም በአዋጅ መጽደቁን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ ከተሾሙት ቻንስለር በተጨማሪ አዳዲስ የቦርድ አመራሮች የተሰየሙለት ሲሆን ፤ ቦርዱም ዩኒቨርሲቲውን በሃላፊነት ሊመሩ የሚችሉ ፕሬዚዳንት እና ም/ፕሬዚዳንቶችን በቀጣይነት እንደሚሾም ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#Update
ቦርዱ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩን የቦርድ ሊቀመንበር አድርጎ መሾሙን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ደግሞ ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸውን ገልጸዋል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ #የአዲስ_አበባ_ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ሆነው ተሾሙ።
የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #ቻንስለር ተደርገው በጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተሹመዋል።
ሹመቱ የተሰጣቸው፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርስቲ ሆኖ እንዲቋቋም እንዲቋቋም በአዋጅ መጽደቁን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ ከተሾሙት ቻንስለር በተጨማሪ አዳዲስ የቦርድ አመራሮች የተሰየሙለት ሲሆን ፤ ቦርዱም ዩኒቨርሲቲውን በሃላፊነት ሊመሩ የሚችሉ ፕሬዚዳንት እና ም/ፕሬዚዳንቶችን በቀጣይነት እንደሚሾም ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#Update
ቦርዱ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩን የቦርድ ሊቀመንበር አድርጎ መሾሙን የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሀኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታው ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ደግሞ ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው መሾማቸውን ገልጸዋል።
ምንጭ፦ ትምህርት ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#አይቴል
ጥራት ያላቸውን የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ከሚያቀርቡ ታላላቅ የሞባይል አምራች ኩባያዎች አንዱ የሆነው አይቴል ሞባይል ለኩባንያው አዲስ የሆነውን እና በላቁ ፈጠራዎችን እጅግ ከዘመኑ ግልጋሎቶች ጋር በማጣመር የተመረተውን አይቴል ኤስ23+ ሞዴል በኢትዮጵያ ባዘጋጀው ዝግጅት በይፍ አስተዋውቋል።
ላለፉት ዓመታት ተወዳጅነት አና ተቀባይነት ያገኙ በአገልግሎት እና በዋጋ ተመራጭ የሆኑ የስልክ ምርቶቹን ለተጠቃሚዎች ሲያቀርብ የቆየው አይቴል ሞባይል በቴክኖሎጂ እና ዲዛይን ልዩ የሆነውን ብሎም የተለያዩ ግልጋሎቶች በመያዝ የተመረተውን ኤስ23+ አዲስ የሞባይል ሞዴል ማስተዋወቅን ዓላማው ያደረገ ዝግጅት የኩባንያው ሀላፊዎች አና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በታደሙበት ስነስርዓት በይፋ አስመረቀ ።
አይቴል ሞባይል
#ItelMobile #ItelEthiopia #S23+
ጥራት ያላቸውን የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ከሚያቀርቡ ታላላቅ የሞባይል አምራች ኩባያዎች አንዱ የሆነው አይቴል ሞባይል ለኩባንያው አዲስ የሆነውን እና በላቁ ፈጠራዎችን እጅግ ከዘመኑ ግልጋሎቶች ጋር በማጣመር የተመረተውን አይቴል ኤስ23+ ሞዴል በኢትዮጵያ ባዘጋጀው ዝግጅት በይፍ አስተዋውቋል።
ላለፉት ዓመታት ተወዳጅነት አና ተቀባይነት ያገኙ በአገልግሎት እና በዋጋ ተመራጭ የሆኑ የስልክ ምርቶቹን ለተጠቃሚዎች ሲያቀርብ የቆየው አይቴል ሞባይል በቴክኖሎጂ እና ዲዛይን ልዩ የሆነውን ብሎም የተለያዩ ግልጋሎቶች በመያዝ የተመረተውን ኤስ23+ አዲስ የሞባይል ሞዴል ማስተዋወቅን ዓላማው ያደረገ ዝግጅት የኩባንያው ሀላፊዎች አና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በታደሙበት ስነስርዓት በይፋ አስመረቀ ።
አይቴል ሞባይል
#ItelMobile #ItelEthiopia #S23+
#CBE
የጋብቻ ቁጠባ ሂሳብ
=========
ጋብቻ ሲያስቡ
የሰርግ ወጪዎን ለመሸፈን፣ ቤትዎን ለማሟላት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተሻለ ወለድ ጋር በሚሰጠው የጋብቻ ቁጠባ ሂሳብ አገልግሎት አስቀድመው ይቆጥቡ!
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• Telegram፡- https://t.iss.one/combankethofficial
የጋብቻ ቁጠባ ሂሳብ
=========
ጋብቻ ሲያስቡ
የሰርግ ወጪዎን ለመሸፈን፣ ቤትዎን ለማሟላት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተሻለ ወለድ ጋር በሚሰጠው የጋብቻ ቁጠባ ሂሳብ አገልግሎት አስቀድመው ይቆጥቡ!
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• Telegram፡- https://t.iss.one/combankethofficial
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጅግጅጋ ከሶማሌ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን በተገኘው መረጃ በጅግጅጋ ከተማ የ9 ዓመቷን ልጅ #ደፍረው_ገድለዋል ተብለው የተጠረጠሩት 4 ተጠርጣሪዎች በአባቷ ቤት ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ናቸው። በልጅቷ አባት ቤት ውስጥ ይሰሩ ነበር ከተባሉት ከአራቱ ተጠርጣሪዎች አንዱ ላይ በዋናነት ምልክቶች እንደሚታዩ የክልሉ መንግሥት አሳውቋል። ከሚታዩት ምልክቶች አንዱ ፤ ልጅቷን ሲደፍሯት የጥፍሮቿ ምልክት እንዲሁም…
#ጅግጅጋ
" እኔ ተጎጂ ነኝ፤ ፍትሕ እፈልጋለሁ " - አባት
በጅግጅጋ ከተማ የተደፈረችው ልጅ አባት ምን አሉ ?
አባት ኡጋስ አረብ በጅግጅጋ ከተማ ወረዳ 13 ተብሎ በሚጠራው ቦታ ልጃቸው በራሳቸው ሰራተኞች ከተደፈረች በኃላ መገደሏን ገልጸዋል።
ለቢቢሲ ሶማሊ ክፍል አባት ኡጋስ አረብ ፦
" እኔ ተጎጂ ነኝ፤ ፍትሕ እፈልጋለሁ። እለኔ ልጅ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም በዚህ መንገድ ሕይወታቸው ለጠፋ ሁሉ ፍትሕ እንዲሰፍን እጠይቃለሁ።
በወቅቱ መኝታ ቤቴ ውስጥ ተኝቼ ነበር። ቤት ውስጥም ከእኔ ውጭ ትልልቅ ሰዎች አልነበሩም።
ልጄ ጋር ሄጄ ሳያት እየተነፈሰች አልነበረም ደረቷንም በመጫን እንድትተነፍስ ለማድረግ ሞከርኩ።
አንገቷንም ሳየው ገመድ ተጠምጥሞባት ታንቃለች። ገመዱን ቆርጬ ወደ ሐኪም ወሰድኳት።
ለሕክምና ወደ ሆስፒታል አፋፍሰን ብንወስዳትም ሕይወቷ አልፏል።
በሞባይል ጥገና ሱቄ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ አራቱ ሠራተኞቼ በድርጊቱ ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል። አንደኛው ሠራተኛዬ ጠፍቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።
Via BBC Somali
@tikvahethiopia
" እኔ ተጎጂ ነኝ፤ ፍትሕ እፈልጋለሁ " - አባት
በጅግጅጋ ከተማ የተደፈረችው ልጅ አባት ምን አሉ ?
አባት ኡጋስ አረብ በጅግጅጋ ከተማ ወረዳ 13 ተብሎ በሚጠራው ቦታ ልጃቸው በራሳቸው ሰራተኞች ከተደፈረች በኃላ መገደሏን ገልጸዋል።
ለቢቢሲ ሶማሊ ክፍል አባት ኡጋስ አረብ ፦
" እኔ ተጎጂ ነኝ፤ ፍትሕ እፈልጋለሁ። እለኔ ልጅ ብቻ ሳይሆን ከዚህ ቀደም በዚህ መንገድ ሕይወታቸው ለጠፋ ሁሉ ፍትሕ እንዲሰፍን እጠይቃለሁ።
በወቅቱ መኝታ ቤቴ ውስጥ ተኝቼ ነበር። ቤት ውስጥም ከእኔ ውጭ ትልልቅ ሰዎች አልነበሩም።
ልጄ ጋር ሄጄ ሳያት እየተነፈሰች አልነበረም ደረቷንም በመጫን እንድትተነፍስ ለማድረግ ሞከርኩ።
አንገቷንም ሳየው ገመድ ተጠምጥሞባት ታንቃለች። ገመዱን ቆርጬ ወደ ሐኪም ወሰድኳት።
ለሕክምና ወደ ሆስፒታል አፋፍሰን ብንወስዳትም ሕይወቷ አልፏል።
በሞባይል ጥገና ሱቄ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ አራቱ ሠራተኞቼ በድርጊቱ ተጠርጥረው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል። አንደኛው ሠራተኛዬ ጠፍቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።
Via BBC Somali
@tikvahethiopia
#ጋብቻ
እየተጠናቀቀ ባለው በ2015 ዓ/ም የጋብቻ ፍቺ የፈፀሙ እና የተመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ባለትዳሮች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር #በእጥፍ እንደበለጠ ታውቋል።
የአ/አ ሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በሰጡት ቃል፤ " በ2015 ዓ/ም በጀት አመት 4,696 ሰዎች ፍቺ አስመዝግበዋል ፤ አምና መጥተው ያስመዘገቡት 2,937 ሰዎች ነበሩ " ብለዋል።
ምዝገባው ነው የጨመረው እንጂ ፍቺው ከዚህም በላይ ሊሆን ይችላል ሲሉ ዳይሬክተሩ አክለዋል።
የፍቺ ሁኔታ ከእጥፍ በላይ ጭማሪ ቢያሳይም ሂደቱ ፍርድ ቤትን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የሚከናወን በመሆኑ ትክክለኛውን ቁጥር ለማውቅ አዳጋች እንደሆነ አቶ ዮሴፍ ገልጸዋል።
" ፍ/ቤት ላይ የሚፈፀመውን ፍቺ እዛው ወቅታዊ ምዝገባውን የማከናወን ስራ በዚህ አመት አቅደን አልተሳካም ሚቀጥለው አመት እየተነጋገርን ነው ፍርድ ቤት ሆነን ምዝገባ የሚከናወንበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለን እንጠብቃለን። " ብለዋል።
" በዚህ መንገድ ትክክለኛውን ዳታ ፍቺ እየጨመረ ነው ወይስ እየቀነሰ ነው የሚለውን ውሳኔ ለመስጠት እንችላለን " ያሉት አቶ ዮሴፍ " አሁን ላይ ግን የኛ ምዝገባ ሰው ፍልጎ ፍቺውን በተለያየ አግባብ ለንብረት ክፍፍል ፣ ከመታወቂያ ዲጂታላይዝ መደረግ ጋር ተያይዞ የጋብቻ ሁኔታ ፍቺ የማስባል እና ሌሎች ነገሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ... በዛ ምክንያት እኛ ጋር ምዝገባው ከአምና ከፍ ብሏል የሚል ድምዳሜ ነው የያዝነው " ሲሉ ተናግረዋል።
#ቪኦኤ
@tikvahethiopia
እየተጠናቀቀ ባለው በ2015 ዓ/ም የጋብቻ ፍቺ የፈፀሙ እና የተመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ባለትዳሮች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር #በእጥፍ እንደበለጠ ታውቋል።
የአ/አ ሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በሰጡት ቃል፤ " በ2015 ዓ/ም በጀት አመት 4,696 ሰዎች ፍቺ አስመዝግበዋል ፤ አምና መጥተው ያስመዘገቡት 2,937 ሰዎች ነበሩ " ብለዋል።
ምዝገባው ነው የጨመረው እንጂ ፍቺው ከዚህም በላይ ሊሆን ይችላል ሲሉ ዳይሬክተሩ አክለዋል።
የፍቺ ሁኔታ ከእጥፍ በላይ ጭማሪ ቢያሳይም ሂደቱ ፍርድ ቤትን ጨምሮ በተለያየ መንገድ የሚከናወን በመሆኑ ትክክለኛውን ቁጥር ለማውቅ አዳጋች እንደሆነ አቶ ዮሴፍ ገልጸዋል።
" ፍ/ቤት ላይ የሚፈፀመውን ፍቺ እዛው ወቅታዊ ምዝገባውን የማከናወን ስራ በዚህ አመት አቅደን አልተሳካም ሚቀጥለው አመት እየተነጋገርን ነው ፍርድ ቤት ሆነን ምዝገባ የሚከናወንበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለን እንጠብቃለን። " ብለዋል።
" በዚህ መንገድ ትክክለኛውን ዳታ ፍቺ እየጨመረ ነው ወይስ እየቀነሰ ነው የሚለውን ውሳኔ ለመስጠት እንችላለን " ያሉት አቶ ዮሴፍ " አሁን ላይ ግን የኛ ምዝገባ ሰው ፍልጎ ፍቺውን በተለያየ አግባብ ለንብረት ክፍፍል ፣ ከመታወቂያ ዲጂታላይዝ መደረግ ጋር ተያይዞ የጋብቻ ሁኔታ ፍቺ የማስባል እና ሌሎች ነገሮች ሊኖሩ ስለሚችሉ ... በዛ ምክንያት እኛ ጋር ምዝገባው ከአምና ከፍ ብሏል የሚል ድምዳሜ ነው የያዝነው " ሲሉ ተናግረዋል።
#ቪኦኤ
@tikvahethiopia