TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሲቢኢ ብር - ለቀላል፣ ፈጣን፣ አስተማማኝ የነዳጅ ግብይት!
=================
ደንበኞች ወደ ነዳጅ ማደያ ከመምጣታቸው አስቀድመው

• የሲቢኢ ብር አገልግሎታቸው በአግባቡ እንደሚሠራ ቢያረጋግጡ፣
• ሲቢኢ ብርን መጠቀም ካልጀመሩም ወደ *847# በመደወል፣ ወይም የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ በራሳቸው ተመዝግበው፤ እና
• በሲቢኢ ብር አካውንታቸው በቂ ገንዘብ መኖሩን አረጋግጠው ቢመጡ የተቀላጠፈ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡

ስለ ሲቢኢ ብር አገልግሎት በቂ መረጃ ለማግኘት ወደ 951 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ!
*********************
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለመጫን፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
#እግድ

" የማህበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ቴሌቪዥን ጣቢያ " በመንግስት #በጊዜያዊነት ታገደ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን ዛሬ እሁድ በፃፈው ደብዳቤ " ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ " ን በጊዜያዊነት እንዳገደ አሳውቋል።

ባለስልጣን መ/ቤቱ ፤ ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ዛሬ በግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም " ሰበር ዜና " በሚል ባሰራጨው መግለጫ ከሐይማኖት መገናኛ ብዙኃን ሚና ውጪ በሆነ አግባብ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያካሄደውን ስብሰባ የሚያውክና ህዝብን ለግጭት የሚያነሳሳ መልዕክት ማሰራጨቱን አረጋግጫለሁ ብሏል።

ይህም የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን የሚተላለፍና በሀገር ሁለንተናዊ ሰላም ላይ ጉዳት ሊያስከትል የሚችል እንደሆነም ገልጿል።

ከጉዳዩ አጣዳፊነትና ሊያስከትለው ከሚችለው ጉዳት አንፃር በቀጣይ በባለሥልጣኑ ቦርድ ታይቶ ዘላቂ ውሳኔ እስከሚሰጥበት ጊዜ ድረስ የጣቢያው ፈቃድ በጊዜያዊነት የታገደ መሆኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡

ማህበረ ቅዱሳ ቴሌቪዥን ጣቢያ በመገናኛ መረቡ " ሰበር ዜና " በሚል ያሰራጨው " ወቅታዊ የቤተክርስቲያን ችግርን ለመቅረፍ በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው አብይ ኮሚቴ " በኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት ላይ አወጥቶታል ያለውን መግለጫ ነው።

https://www.facebook.com/100069179198602/posts/pfbid0kKRZfaiNWQpCJpyUSuuNWtyXNHahgy1DZH4DUMudijNXNbcu8N7G1CGUP73Y6e9dl/?app=fbl

የግንቦት 2015 ዓ/ም ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከቀናቶች በፊት ተጀምሮ እየተካሄደ ሲሆን በየዕለቱ በቤተክርስቲያኗ ቴሌቪዥን ዕለታዊ መረጃዎች/ውሳኔዎች ሲተላለፉ ነበር ፤  እስከ ዛሬ ድረስ ጉባኤው መቋጫ አግንኝቶ #በቅዱስ_ሲኖዶስ በኩል ለምዕመኑ የተሰጠ አጠቃላይ መግለጫ የለም።

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ

በድሬደዋ ከተማ ባለፉት ጥቂት ቀናት ከወትሮው የተለየ ከፍተኛ የሆነ የሙቀት መጠን መስተዋሉን ተከትሎ የከተማው ጤና ቢሮ ለነዋሪዎች የጥንቃቄ መልእክት አስተላልፏል።

በተለይም አረጋውያን እና የተለያዩ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸው (ከፍተኛ ደም ግፊት፣ የስኳር ህመም፣ የልብ ህመም፣ የኩላሊት ህመምና ሌሎችም)፣ እራሳቸውን መንከባከብ የማይችሉ የአእምሮ ህሙማን እና ህፃናት በተለየ መልኩ ከታች የተዘረዘሩትን የጥንቃቄ መልእክቶች ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

1. ወቅታዊው ከፍተኛ የሙቀት መጠን እስኪያልፍ መኖሪያ ቤትዎን በተለያዩ መንገዶች ማቀዝቀዝ፤

2. ቤትዎ በሚሆኑበት ግዜና በእንቅልፍ ወቅት የቤትዎን መስኮትና በር ክፍት ማድረግ፤

3. በቤትዎ የአየር መታፈን እና ከፍተኛ ሙቀት በሚኖርበት ወቅት ከቤትዎ ውጪ/በረንዳዎ ላይ መቆየት፤

4. ጥም ባይኖርቦትም በቂ ፈሳሽ/ውሃ/ መውሰድ፤

5. አመጋገብዎን ማስተካከል(ስብና ቅባት የበዛባቸው ምግቦችን መቀነስ)፤

6. ቀለል ይሉ አካላዊ እንቅስቃሴዎችን ጥላማ በሆኑ ቦታዎች ላይ መስራት፤

7. የአልኮል መጠጦችን አለመጠቀም/መቀነስ፤

8. ህፃናትን እና የአዕምሮ ህሙማንን በተዘጉ/አየር በሌላቸው ክፍሎች ለብቻ አለመተው፤

9. የተለያየ ህመም  ማለትም እንደ ከፍተኛ ደም ግፊት፣ ስኳርና የልብ ህመም ካለብዎ የህክምና ክትትልዎን በሚገባ ማድረግ፣ የታዘዘውን መድኃኒት በትዕዛዙ መሰረት በመውሰድ ጤናዎን እንዲጠብቁ መልዕክት አስተላልፏል።

t.iss.one/tikvahethmagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ባልደራስ

ከዚህ ቀደም ጠቅላላ ጉባኤውን እንዳያደርግ ተከልክሎ እንደነበር የገለፀው ባለደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ዛሬ ጠቅላላ ጉባኤውን አድርጓል።

ፓርቲው በጠቅላላ ጉባኤው ፥ አቶ አምሃ ዳኜው ፕሬዝዳንት አድርጎ ሾሟል።

አቶ አማሃ ዳኜው ፤ ፓርቲውን በም/ፕሬዝዳንትነት ሲያገለግሉ ነበሩ። ዛሬ በአብላጫ ድምፅ አቶ ለቀጣይ 3 አመታት በፕሬዝዳንትነት እንዲያገለግሉ ተመርጠዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ፤ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ዛሬ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ #ሀገራዊ_ፓርቲ ለመሆን ውሳኔ አሳልፏል።

ባልደራስ ፓርቲ ፤ ምንም እንኳን ኢትዮጵያዊ ሀሳቦችን እያነሳው የታገልኩኝ ቢሆንም ባለኝ ፍቃድ መሰረት ግን መንቀሳቀስ የቻልኩት አዲስ አበባ ላይ ብቻ ነው ብሏል።

የዛሬው ጉባኤ ፓርቲው ሀገር አቀፍ ፓርቲ ለመሆን የሚያስፈልጉ ቅድመ ተግባራትን እያከናወነ እንዲቆይ እና ከወራት በኋላ በሚደረገው ጉባኤ ወደ ሀገር አቀፍነት እንዲያድግ ያለ ተቃውሞ እና ድምፀ ታቅቦ መፅደቁ ተገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ ጠቅላላ ጉባኤው ፓርቲው ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ከውህደት-መለስ አብሮ እንዲሰራ ፈቅዷል።

ነገር ግን ከፓርቲዎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት የፓርቲው ምክር ቤት እንዲወስን ጉባኤው ፍቃድ ሰጥቷል።

በዚህ መሰረት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ከፓርቲዎች ጋር የሚኖረውን ግንኙነት መርምሮ እና አጥንቶ ለፓርቲው ምክር ቤት እንዲያቀርብ፤ እንዲሁም ም/ቤቱ ስራ አስፈፃሚ የሚያቀርብለትን የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ እንዲያፀድቅ ወስኗል።

መረጃው ከፓርቲው ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia
" በህግ ማስከበር ስም የድሆችን ቤት እና ቤተ እምነቶችን ማፍረስ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው " - ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ በአዲስ መልክ በመደራጀት ላይ ባለው " ሸገር ከተማ " ባለፉት ጥቂት ወራት ህገ ወጥ ግንባታዎችን ለመከላከል በሚል በተወሰደው እርምጃ በርካታ ቤቶች በመፍረስ ላይ እንዳሉ እንደሚታወቅ እና እርምጃው ዛሬም ድረስ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።

ፓርቲው እየተወሰደ ባለው እርምጃ በርካታ ቤቶች እንዲፈርሱ የተደረገ መሆኑንና በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በሚያሳዝን ሁኔታ ጎዳና ላይ እንዲወድቁ መደረጉን አመልክቷል።

እርምጃው ቤታቸው በፈረሰባቸው ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እና እንግልት ከማሳደሩም ባሻገር፣ የማፍረስ ሂደቱ ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ ቀስቅሷል ሲልም አክሏል።

ነእፓ ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጫለሁ እንዳለው ቤት የማፍረስ እርምጃው ህጋዊ ፍቃድ የሌላችውን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ህጋዊ ሰነድ ያላቸውን ዜጎች ጭምር ሰለባ ያደረገ መሆኑና ይህም ቤት የማፍረስ እርምጃው ዓላማ ግልጽነት የጎደለው እንዲሆን ማድረጉን ገልጿል።

" የማፍረስ እርምጃው ከዜጎች የመኖሪያ ቤት በተጨማሪ የእምነት ተቋማትን ኢላማ ያደረገ ነው " ያለው ነእፓ " በዚሁ ሳቢያ በርካታ #መስጂዶች መፍረሳቸው ተረጋግጧል፡ " ብሏል።

ይህ እርምጃ ምንም አይነት ህጋዊ መሰረት የሌለው፣ ተጠያቂነት የጎደለው ተግባር ከመሆኑ ባሻገር የእምነት ተቋማትን ክብር ያጎደፈ እና መንግስት ለምእመኑ ያለውን ንቀት የሚያሳይ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ሲል ገልጿል።

ነእፓ ፤ " አብዛኛው የሀገራች ህዝብ በአስከፊ ድህነት ውስጥ እየኖረ ባለበት፣ የእለት ጉርስ እና የአመት ልብስ ማግኘት ህልም በሆነበት፣ ዳቦ፣ ዘይት እና ስኳር ቅንጦት በሆነበት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በጦርነት እና በግጭት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ባሉበት ሀገር ያለ በቂ ጥናት እና ዝግጅት የዜጎችን ቤት በጅምላ ማፍረስ በህግም ሆነ በሞራል ተቀባይነት የሌለውና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው " ብሏል።

" በሀገራችን ተንሰራፍቶ በቆየው ብልሹ አስተዳደር ሳቢያ፣ እንዲሁም መንግስት የመኖሪያ ቤት እና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ ባለመቻሉ፣ ዜጎች ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ከጸሀይ ሀሩር እና ከክረምት ዝናብ የሚከልሉበት ጎጆ እንዲቀልሱ ተገደው ኖረዋል " ያለው ፓርቲው " በዚህ ምክንያት በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች በመንግስት #ደካማ እና #በሙስና የተጨማለቀ አሰራር ምክንያት ዜጎች ለበርካታ አስርት አመታት ህጋዊ ይዞታ የሚያገኙበት ስርአት ሳይዘረጋላቸው ቆይቷል " ሲል ገልጿል።

ይህንን የመንግስት እንዝላልነት እና ብልሹ አሰራር ህግ እና ስርአት በጠበቀ መልኩ ማስተካከል ሲገባ፣ ዜጎች በሀብታቸው፣ በንብረታቸው እና በህይወታቸው ዋጋ እንዲከፍሉ ማድረግ ሰብአዊነት እና ኃላፊነት የጎደለው ታሪካዊ ስህተት ነው ብሏል።

" ቤት ማፍረሱ ሳያንስ፣ ዜጎች ለበርካታ አመታት ከኖሩበት ጎጆ በቂ ጊዜ እና አማራጭ የመኖሪያ ስፍራ እንዲያገኙ እድል ሳይሰጥ ' በጊዜ የለንም ' ፍጥነት ከመኖሪያ ደጃቸው እንዲነሱ የተደረገበት አሰራር ሂደቱን ይበልጥ አሳዛኝ፣ አሳሳቢ እና አጠያያቂ አድርጎታል " ያለው ነእፓ በአዲሱ የሸገር ከተማ በመካሄድ ላይ ያለው ቤት የማፍረስ ዘመቻ ፦
- በቂ ህጋዊ መሰረት የሌለው፣
- ከፍተኛ የአፈጻጸም ክፍተት ያለበት ፣
- የክልሉን ብሎም የሀገራችንን አሁናዊ የጸጥታ ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ድርብርብ ችግሮች እና ሀቆች በቅጡ ያላገናዘበ በመሆኑ #በአፋጣኝ_እንዲቆም አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ በ " ቴሌ ብር " መከፈል ሊጀመር ነው ?

ገንዘብ ሚኒስቴር ፤ በባንኮች በኩል ተከፋይ የሚሆነውን የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ወደ " ቴሌ ብር " የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ለማሸጋገር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕ/ተ/ም/ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት ወቅት ነው ይህ ይፋ የሆነው።

አቶ አህመድ ሽዴ ምንድነው ያሉት ?

" አሁን በባንኮች የክፍያ ሥርዓት በጥቅል (በበልክ) እየተከፈለ ያለውን ሒደት በቀጣይ ወደ ቴሌ ብር ለማሸጋገር ሥራዎች እየተሠሩ ነው። "

ይህ በተመለከተ ' ኢትዮ ቴሌኮም  ' ምን አለ ?

ቺፍ ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ መሳይ ውብሸት ፦

" በመንግሥት የተያዙት ጉዳዮች ወቅቱን ጠብቀው ቢገለጹ ይሻላል።

ነገር ግን ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን ለማቅረብ የሚያስችል በቂ ዝግጅትና አቅም አለው።

ተቋሙ በሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎቱ እስካሁን ከ32 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን አገልግሎት እየሰጠ እንደገሚገኘው መጠን የተዘረጋው ሲስተም አገልግሎቱን በቀላሉ ለመስጠት ያስችለዋል።

የትኛውም ውሳኔ ከሚመለከተው አካል ከመጣ መሥራት ይቻል።

ደመወዝ በቴሌ ብር መከፈሉ የተቋማትን ቅልጥፍና ለመጨመር አስተዋጽኦ ያድረጋል።

በዕረፍትና በበዓላት ወቅት የሚውል የደመወዝ ክፍያ ቀንና ተዛማጅ ጉዳዮች ለደመወዝ ከፋዩም ሆነ ተከፋዩ በሚያመች ለመክፈል ያስችላል።

እስካሁን ባለው አገልግሎቱ እንደ ደመወዝ ዓይነት የጅምላ (በበልክ) ክፍያ በሚከፈልበት ወቅት ሠራተኞች የደመወዛቸውን እስከ 35 በመቶ ያለምንም ዋስትና መበደር ይችላሉ። በቀጣይ ሌሎች ተጨማሪ አማራጮችም ይቀርባሉ።

እስካሁን ድረስ ግን ከሚመለከተው አካል የመጣ አቅጣጫ የለም። " ብለዋል።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊ ደመወዥ በ " ቴሌ ብር " ለማድረግ ስለታሰበው እቅድ በተመለከተ " እንዲህ መባሉን መረጃ የለኝም " ብለዋል።

በባንኩ በኩል የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝ የሚከፍል መሆኑን የገለፁት እኚሁ ኃላፊ ለዚህ አገልግሎቱ ምንም ዓይነት ክፍያ የማይጠይቅበት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡

በቴሌ ብር በኩል ደመወዝ ይከፈል ከተባለ ግን አሁንም ኢትዮ ቴሌኮም የሚጠቀመው ከባንኮች ጋር በመተሳሰር መሆኑ አይቀርም ብለዋል፡፡

አጫጭር መረጃ ፦

እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ፦

- የመንግሥት ኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ድርሻን ለማሳደግና እስካሁን የ159 ባለ በጀት መ/ቤቶች የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ዘዴ እንዲተገብሩ ተደርገዋል።

- በተያዘው ዓመት የዘጠኝ ወራት 79.2 ቢሊዮን ብር ክፍያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ተከፍሏል።

- ኢትዮ ቴሌኮም የመንግሥት የኤክትሮኒክስ ክፍያ ድርሻ ለመወጣት እንዲያስችለው የሪፎርም ሥራዎችን እየሠራ ነው የታክስ ክፍያ አሰባሰብም ሥርዓቱ በቴሌ ብር እንዲከፈል የሚያስችል ሥርዓት ተዘርግቷል።

እንደ ኢትዮ ቴሌኮም መረጃ ፦

- የቴሌ ብር የሞባይል ገንዘብ ዝውውርን ይፋ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እስከ የግንቦት ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ 32.2 ሚሊዮን ደንበኞች አፍርቷል።

- እስካሁን ከ375.2 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ግብይቶች (ትራንዛክሽንስ) ተፈፅሟል።

- የነዳጅ ክፍያ በአስገዳጅነት በዲጂታል እንዲፈጸም ከተደረገበት ከሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ 2.7 ቢሊዮን ብር ግብይት ተፈፅሟል።

Credit : ሪፖርተር ጋዜጣ

@tikvahethiopia
የገቢዎች ሚኒስቴር ግብር ከፋዮች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበ።

ሚኒስቴሩ ፤ ማንነታቸው በውል ያልታወቁ ግለሰቦች እና ቡድኖች የተለያዩ የማደናገሪያ እና የማጭበሪያ መንገዶችን እንዲሁም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ስም እና ሀሰተኛ ማንነት በመጠቀም ግብር ከፋዮችን #እያጭበረበሩ ይገኛሉ ብሏል።

ይህ የማጭበርበር ተግባር እየተሰራ ያለው የግብር ከፋዩን የስልክ አድራሻ በመጠቀም እንደሆነም ገቢዎች ሚኒስቴር ገልጿል።

የማጭበርበር ተግባሩ የሚፈፀመው እንዴት ነው ?

የግብር ከፋዮችን አድራሻ በመጠቀም ፦

1.  ለታማኝ ግብር ከፋይ የሚሰጠውን ሽልማት እንድትሸለሙ እናስመርጣችኋለን፣

2. የኦዲት ውሳኔ #እናስቀንስላችኋለን

3.  ድርጅታችሁ #ወንጀል_መስራቱ ስለተደረሰበት በህግ እንዳትጠየቁ እናደርጋለን የሚሉና የመሳሰሉ #የማስፈራራት እና #የማግባባት ሙከራዎች እና ዘዴዎችን በመጠቀም ነው።

ገቢዎች ሚኒስቴር ይህ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑ በክትትል ለማወቅ እንደቻለ ገልጾ ግብር ከፋዮች የነዚህ መሰል የማጭበርበር ሙከራዎች ሰለባ እንዳይሆኑ አስጠንቅቋል።

ማንኛውም ግብር ከፋይ ይህ መሰል ሁኔታዎች ሲያጋጥሙትም በአቅራቢያው ለሚገኝ የግብር ሰብሳቢ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በአፋጣኝ ጥቆማ እንዲሰጥ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ጋምቤላ

10 ሰዎች ሲገደሉ 12 ሰዎች ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ቅዳሜ ዕለት ከደቡብ ሱዳን በመነሳት የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ወደ ጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን የገቡ የ " ሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች " 10 ሰዎችን ገድለው 12 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ማድረሳቸውን ከጋምቤላ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ታጣቂዎቹ ቅዳሜ ምሽት 3 ሰዓት ተኩል ገደማ ድንበር ጥሰው በመግባት በማኩዌይ ወረዳ ቢልኬች ቀበሌ እንዲሁም በዋንቱዋ ወረዳ መተሀር ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በፈፀሙት ጥቃት በአጠቃላይ 10 ሰዎችን ገድለው ፤ 12 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት አድርሰዋል።

በጥቃቱ ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ወደ ጋምቤላ ጠቅላላ ሆስፒታል ለህክምና የተላኩ ሲሆን ቀላል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች ደግሞ በኝንኛንግ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ተነግሯል።

ከጥቃቱ በኃላ በጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ቴንኩዌይ ጆክ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኑዌር ዞን በሙርሌ ጥቃት የደረሰባቸውን ዜጎች ምልከታ አድርጓል።

አቶ ቴንኩዌይ ጆክ  ፤ በተደጋጋሚ ወቅትና ጊዜ እየጠበቁ ጥቃት የሚሰነዝሩት የደቡብ ሱዳን የሙርሌ ታጣቂዎች፣ ትቅዳሜ ምሽት ድንገተኛ ተኩስ በመክፈት ነው ጥቃቱን ያደረሱት ብለዋል።

የክልሉ መንግስት ጥቃት አድራሾችን ተከታትሎ ለማደን ጥረት እያደረገ ነው ያሉ ሲሆን ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈፀም የተጠናከረ ጥበቃ ይደረጋል ብለዋል።

የክልሉ መንግስት በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደምም እነዚሁ ድንበር ጥሰው የሚገቡ የሙርሌ ጎሳ ታጣቂዎች በኑዌር ዞንና አኙዋ ዞኖች ገብተው የተለያዩ ጥቃቶችን ማድረሳቸው ይታወሳል።

ድንበሩ ሰፊ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በሌሎች አካባቢዎችም ተመሳሳይ ጥቃት እንዳይፈጸም መንግስት ከሚያደርገው ጥረት በተጓዳኝ ህብረተሰቡ በንቃት አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቧል።

መረጃው ከጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬተሪያት የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ወደ ባንክ ቅርንጫፍ መሄድ ሳይጠበቅብዎ በቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎቻችን ከእሁድ እስከ እሁድ ለ24 ሰዓት የተሟላ የባንክ አገልግሎት ያግኙ።

#BankofAbyssinia #BankingServices #ITM #VirtualBanking #DigitalBanking #MoneyTransfer #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የተላለፈው ይዘት በቤተ ክርስቲያኗ ምእመናን መካከል እርስ በእርስ ግጭት የሚፈጥር ነው ብለን አናምንም " - ማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን

ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ፤ ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ በሚቃረን ሁኔታ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን መታገዱን በመግለጽ አቤቱታውን ተቋሙን በበላይነት ለሚመራው ቦርድ አቀረበ።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን " የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያካሄደውን ስብሰባ የሚያውክና ህዝብን ለግጭት የሚያነሳሳ መልዕክት አሰራጭቷል ፤ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን ተላልፏል " በሚል ለማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ቴሌቪዥንን እሑድ ግንቦት 13/2015 ዓ.ም በተጻፈው ደብዳቤ በጊዜያዊነት እግድ አስተላልፏል።

ማኅበረ ቅዱሳን ፤ እግዱ የመገናኛ ብዙኃኑን አዋጅ የጣሰ ነው በማለት ተቋሙን በበላይነት ለሚመራው ቦርድ ቅሬታውን አቅርቧል።

የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ምን አለ ?

ትላንት የተላለፈው መግለጫ በኢ/ኦ/ተ/ቤ ቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን እውቅና ያላቸው ከ10 በላይ ማኅበራት ያሉበት ዐቢይ ኮሚቴ መግለጫ መሆኑን ገልጿል።

ማህበረ ቅዱሳን መግለጫውን የማስተላለፍ ግዴታ አለብን ያለ ሲሆን ባለስልጣን መ/ቤቱ የወሰደው እርምጃ ግን በሃይማኖት የውስጥ ጉዳዮች ላይ ነው ብሎ እንደሚያምን ገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ የተላለፈው ይዘት ከሌሎች ሃይማኖቶች ጋር የሚገናኝ ነገር እንደሌለውም ፤ ማንኳሰስም የሌለበት እና መቻቻል እንዳይፈጠር የሚያደርግ ዘገባ እንዳልሆነ አስረድቷል።

ይዘቱ " የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ይከበር በአባቶች መካከል የሚስተዋለው መከፋፈል ይቅር " የሚል በመሆኑ በማንኛውም መንገድ በቤተ ክርስቲያኗ ምእመናን መካከል እርስ በእርስ ግጭት የሚፈጥር ነው ብለን አናምንም ሲል አክሏል።

" ዘገባው በተሠራ ጥቂት ሰዓታት ውስጥ ማን ምን አይነት ቅሬታ እንዳቀረበ ለጣቢያችን አልተገለጸም። " ያለው ማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን " በአዋጁ መሠረት ለባለሥልጣኑ የቀረበ ቅሬታ ካለም ጣቢያችን ዘገባውን የሠራበትን ምክንያት ሳይጠየቅና ሳያስረዳ በባለሥልጣኑ የተወሰደ ርምጃ ነው፡፡ ይህም በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ አንቀጽ 7 የተቀመጠውን የባለሥልጣኑን ገለልተኝነት እና ነጻነት የሚጋፋ ሆኖ አግኝተነዋል " ብሏል።

ጣቢያው ምንም እንኳን የሠራው ዘገባ ስሕተት ነው ብሎ እንደማያምን ቢገልጽ። ባለሥልጣኑ በተረዳው መንገድ ስሕተት ሆኖ ቢገኝ እንኳ በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ አንቀጽ 73 የተቀመጠውን ከጽሑፍ ደብዳቤ እስከ የብሮድካስት አገልግሎት ባለፈቃድን ፈቃድ እስከማገድ ያሉ 4 ደረጃዎችን በመጣስ ያለማስጠንቀቂያና ውይይት የአዋጁን አስተዳደራዊ ርምጃዎች ሂደት ያልተከተለ ውሳኔ አስተላልፏል ሲል ገልጿል።

በመሆኑም የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ቦርድ በቴሌቪዥን ጣቢያው ላይ የተላለፈውን ጊዜያዊ እገዳ እንደገና በማየት በጣቢያውና በሃይማኖቱ ተከታዮች ዘንድ የሚፈጥረውን አሉታዊ ተጽዕኖ በማገናዘብ እግዱን አንሥቶ ጣቢያው አገልግሎቱን እንዲቀጥል በፃፈው የአቤቱታ ደብዳቤ ጠይቋል።

@tikvahethiopia