#China
ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?
#ኢትዮጵያ
ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።
አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።
" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።
አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።
#ሱዳን
ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።
ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።
#ኤርትራ
ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።
የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።
ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።
#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?
#ኢትዮጵያ
ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።
አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።
" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።
አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።
#ሱዳን
ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።
ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።
#ኤርትራ
ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።
የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።
ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።
#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ሀገሪቱ ካሏት 47 ሽህ ገደማ ትምህርት ቤቶች 99 በመቶዎቹ አመቺ አይደሉም። በተሰራው ምዘና አራት ትምህርት ቤቶች ብቻ ከፍተኛውን ደረጃ አሟልተዋል። 86 በመቶ የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም 71 በመቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፍፁም ከደረጃ በተታች ናቸው። በትምህርት ምዘናና ጥናት ውጤት ከ4ተኛ ክፍል 20 በመቶዎቹ…
የትምህርት ማስረጃ ማጣራት . . .
የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለህ/ተ/ም/ቤት የተናገሩት ፦
" በሁሉም #የፌደራል_ተቋማት የሰራተኞችን ማህደር መመርመር ጀምረናል። ምን ያህሉ እውነተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዞ ነው ? ምን ያህሉ አይደለም የሚል ምርመራ እያካሄድን ነው፤ ከራሳችን ጀምረን።
ማህበረሰቡ ልክ እንደፈተናው [የ12ተኛ ክፍል ፈተና] እንዲያውቅልን የምንፈልገው ከአሁን በኋላ በተጭበረበረ ድግሪ፤ በተጭበረበረ ዲፕሎማ የሚሰራ ስራ አይኖርም የሚለውን ለማሳወቅ ነዉ። በዚህ ዓመት እሱን እንጨርሳለን ብለን እናስባለን። "
Credit : #AlAIN
@tikvahethiopia
የትምህርት ሚንስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለህ/ተ/ም/ቤት የተናገሩት ፦
" በሁሉም #የፌደራል_ተቋማት የሰራተኞችን ማህደር መመርመር ጀምረናል። ምን ያህሉ እውነተኛ የትምህርት ማስረጃ ይዞ ነው ? ምን ያህሉ አይደለም የሚል ምርመራ እያካሄድን ነው፤ ከራሳችን ጀምረን።
ማህበረሰቡ ልክ እንደፈተናው [የ12ተኛ ክፍል ፈተና] እንዲያውቅልን የምንፈልገው ከአሁን በኋላ በተጭበረበረ ድግሪ፤ በተጭበረበረ ዲፕሎማ የሚሰራ ስራ አይኖርም የሚለውን ለማሳወቅ ነዉ። በዚህ ዓመት እሱን እንጨርሳለን ብለን እናስባለን። "
Credit : #AlAIN
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሙሴቬኒ ምን አሉ ?
የዓለም ባንክ ፤ ኡጋንዳን ለምን የ " ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን የሚከለክል ሕግ ተግባራዊ አደርግሽ ፤ ይህ ሕግ መሰረታዊ ከሆኑ እሴቶቼ ጋር ይቃረናል " በማለት አዲስ ብድር እንደማይሰጣት አሳውቋል።
ይህ ውሳኔ በተመለከተ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ ምን አሉ ?
" ኡጋንዳ ያለ ዓለም ባንክ ብድር ማደግ ትችላለች።
የዓለም ባንክ እምነታችንን ፣ ሉዓላዊነታችንን እና ባህላችንን በገንዘብ እንድንቀይር እያስገደደን ነው።
ምዕራባዊያን አፍሪካን ዝቅ አድርገው መመልከት እና ጫና ማሳደር ይፈልጋሉ ፣ እኛ ችግራችንን እንዴት መፍታት እንዳለብን እናውቃለን፣ እነሱም የእኛ ችግሮቻችን ናቸው።
ኡጋንዳ ከዓለም ባንክ ጋር ያለባትን ችግር ለመፍታት የሚቻል ከሆነ ውይይት ለማድረግ ትቀጥላለች። " #ALAIN
ኡጋንዳ ባፀደቀችውና ተግባራዊ ባደረገችው የፀረ ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ሕግ እድሜ ልክ በእስር ቤት መማቀቅን ጨምሮ ሞት ሊያስፈርድ ይችላል።
ይህን ሕግ አሜሪካን ጨምሮ ምዕራባውያን ሀገራት እና ተቋማት የተቃወሙ ሲሆን የዓለም ባንክ ደግሞ አዲስ ብድር አልሰጥሽም ብሏል።
@tikvahethiopia
የዓለም ባንክ ፤ ኡጋንዳን ለምን የ " ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን የሚከለክል ሕግ ተግባራዊ አደርግሽ ፤ ይህ ሕግ መሰረታዊ ከሆኑ እሴቶቼ ጋር ይቃረናል " በማለት አዲስ ብድር እንደማይሰጣት አሳውቋል።
ይህ ውሳኔ በተመለከተ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ዮሪ ሙሴቪኒ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ ምን አሉ ?
" ኡጋንዳ ያለ ዓለም ባንክ ብድር ማደግ ትችላለች።
የዓለም ባንክ እምነታችንን ፣ ሉዓላዊነታችንን እና ባህላችንን በገንዘብ እንድንቀይር እያስገደደን ነው።
ምዕራባዊያን አፍሪካን ዝቅ አድርገው መመልከት እና ጫና ማሳደር ይፈልጋሉ ፣ እኛ ችግራችንን እንዴት መፍታት እንዳለብን እናውቃለን፣ እነሱም የእኛ ችግሮቻችን ናቸው።
ኡጋንዳ ከዓለም ባንክ ጋር ያለባትን ችግር ለመፍታት የሚቻል ከሆነ ውይይት ለማድረግ ትቀጥላለች። " #ALAIN
ኡጋንዳ ባፀደቀችውና ተግባራዊ ባደረገችው የፀረ ተመሳሳይ ፆታ ግንኙነት ሕግ እድሜ ልክ በእስር ቤት መማቀቅን ጨምሮ ሞት ሊያስፈርድ ይችላል።
ይህን ሕግ አሜሪካን ጨምሮ ምዕራባውያን ሀገራት እና ተቋማት የተቃወሙ ሲሆን የዓለም ባንክ ደግሞ አዲስ ብድር አልሰጥሽም ብሏል።
@tikvahethiopia
በመላው ዓለም ኢንተርኔት ሊቋረጥ ይችላል ?
የአሜሪካው የጠፈር ምርምር ተቋም ወይም በምህጻረ ቃሉ ናሳ ከሰሞኑ አንድ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
የተቋሙ ማስጠንቀቂያም በሚቀጥለው ሳምንት በተለይም በፈረንጆቹ ጥቅምት 10 እና 11 ባሉት ቀናት ውስጥ ከባድ የጸሀይ መብረቅ ወይም ሞገድ ሊከሰት ይችላል ብሏል።
ይህን የናሳን ማስጠንቀቂያ መሰረት በማድረግ በመላው ዓለም ኢንተርኔት ሊቋረጥ ይችላል የሚሉ ዜናዎች በዓለም ላይ በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ።
ይህ ዜና በስፋት መሰራጨቱ ያሳሰበው ናሳም ኢንተርኔት በመላው ዓለም ይቋረጣል በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጅቱ አክሎም በሚቀጥለው ሳምንት በጸሀይ ሀይል ምክንያት ይፈጠራል በተባለው መብረቅ የኢንተርኔት አገልግሎት ሊቋረጥ የሚችልበት ምንም አይነት ግልጽ ስጋት የለም ብሏል።
የአሜሪካ መንግሥት ንብረት የሆነው ናሳ ስለ ጠፈር ሳይንስ የተለያዩ ጥናቶችን እና ግኝቶችን ለመላው ዓለም በማቅረብ ይታወቃል።
Credit - #AlAin_Amharic
@tikvahethiopia
የአሜሪካው የጠፈር ምርምር ተቋም ወይም በምህጻረ ቃሉ ናሳ ከሰሞኑ አንድ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
የተቋሙ ማስጠንቀቂያም በሚቀጥለው ሳምንት በተለይም በፈረንጆቹ ጥቅምት 10 እና 11 ባሉት ቀናት ውስጥ ከባድ የጸሀይ መብረቅ ወይም ሞገድ ሊከሰት ይችላል ብሏል።
ይህን የናሳን ማስጠንቀቂያ መሰረት በማድረግ በመላው ዓለም ኢንተርኔት ሊቋረጥ ይችላል የሚሉ ዜናዎች በዓለም ላይ በስፋት እየተሰራጩ ይገኛሉ።
ይህ ዜና በስፋት መሰራጨቱ ያሳሰበው ናሳም ኢንተርኔት በመላው ዓለም ይቋረጣል በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።
ድርጅቱ አክሎም በሚቀጥለው ሳምንት በጸሀይ ሀይል ምክንያት ይፈጠራል በተባለው መብረቅ የኢንተርኔት አገልግሎት ሊቋረጥ የሚችልበት ምንም አይነት ግልጽ ስጋት የለም ብሏል።
የአሜሪካ መንግሥት ንብረት የሆነው ናሳ ስለ ጠፈር ሳይንስ የተለያዩ ጥናቶችን እና ግኝቶችን ለመላው ዓለም በማቅረብ ይታወቃል።
Credit - #AlAin_Amharic
@tikvahethiopia
#TOYOTA
ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።
ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።
ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።
ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።
ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?
#ቶዮታ
➡ ኮሮላ (2020 - 2021)
➡ ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
➡ ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
➡ አቫሎን ፣ አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
➡ ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
➡ ሴና ሀይብሪድ (2021)
#ሌክሰስ
➡ ES250 (2021)
➡ ES300H (2020-2022)
➡ ES350 (2020-2021)
➡ RX350 (2020-2021)
➡ RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።
ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።
የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።
ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።
ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።
ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።
#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።
Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room
@tikvahethiopia
ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።
ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።
ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።
ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።
ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?
#ቶዮታ
➡ ኮሮላ (2020 - 2021)
➡ ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
➡ ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
➡ አቫሎን ፣ አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
➡ ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
➡ ሴና ሀይብሪድ (2021)
#ሌክሰስ
➡ ES250 (2021)
➡ ES300H (2020-2022)
➡ ES350 (2020-2021)
➡ RX350 (2020-2021)
➡ RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።
ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።
የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።
ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።
ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።
ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።
#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።
Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room
@tikvahethiopia