የአፄ ቴዎድሮስ ሹሩባ🔝
ኢትዮጵያ የአፄ ቴዎድሮስን #ሹሩባ ከእንግሊዝ #ተረከበች። ርክክቡ የተካሄደው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር #ሂሩት_ካሳው በተገኙበት በለንደን ነው። ዶክተር ሂሩት #እንግሊዝ የወሰደችውን ሌሎች ቅርሶችንም #እድትመልሰም ጥያቄ አቅርበዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopua
ኢትዮጵያ የአፄ ቴዎድሮስን #ሹሩባ ከእንግሊዝ #ተረከበች። ርክክቡ የተካሄደው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሯ ዶክተር #ሂሩት_ካሳው በተገኙበት በለንደን ነው። ዶክተር ሂሩት #እንግሊዝ የወሰደችውን ሌሎች ቅርሶችንም #እድትመልሰም ጥያቄ አቅርበዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopua
የጥላቻ ንግግር...
.
.
.
ዛሬ የኢትዮጵያን ማህበራዊ ሚዲያ ለአፍታ የተመለከተ ሰው ሀገሪቱ ምን ያህል በጥላቻ እየታመሰች መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ ካለው ማንነትን መሰረት ካደረገ ግድያ፣ መፈናቀል፣ የንብረት ውድመትና ጅምላ ፍረጃ ጀርባ የጥላቻ ንግግር መኖሩ አጠያያቂ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ከሌላው ዜጋ ጋር የግል ፀብ ከሌለው በስተቀር፤ አንዱ ዜጋ ሌላውን ከመሬት ተነስቶ ሊያጠቃ የሚችልበት ምንም አይነት ምክንያት አይኖርም፡፡
ያም ሆኖ ከግለሰቦች ዕለታዊ ፀብ ያለፈ ጉዳይ ሲፈጠር ግን የጀርባውን መንስኤ በሚገባ መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ከድርጊት ጀርባ ሀሳብ ያለ መሆኑ ግን ሊዘነጋ አይገባም፡፡
የጥላቻ ንግግር ሲባል አገላለፁ በቀጥታ ከአንደበት ወይም ከንግግር ጋር የተያያዘ ይመስላል እንጂ በውስጡ በርካታ ጥቅል ሀሳቦችን የያዘ መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ የጥላቻ ንግግር በአንደበት አማካኝነት በመድረክ ከሚነገረው ንግግር ጀምሮ በፅሁፍ እንደዚሁም በኤሌክትሮኒክስና በምስል ጭምር እስከሚገለፀው የጥላቻ ድርጊት ደርስ አካቶ የሚይዝ ነው፡፡
አገላለፁ በፈረንጆቹም ጭምር “Hate Speech” በሚለው አጠርር ስለሚታወቅ ጉዳዩ ከአንድበት ንግግር ጋር ብቻ የሚያያዝ ይመስላል፡፡ ሆኖም ትንታኔው በጥልቀት ሲመረመር የጥላቻ ንግግር (Hate Speech) መገለጫው አንድን ማህበረሰብ ወይንም ግለሰብ ለማጥቃት ለማሸማቀቅና ለማግለል በማሰብ በንግር፣ በምስል ፣በፅሁፍ፣ በካርቱን፣ በቅርፃ ቅርፅና በልዩ ልዩ ምልክቶች ተደግፎ ጥላቻን ማሰራጨት ማለት ነው፡፡ ጥላቻው የሚሰራጨው ከግለሰቡ ወይንም ከማህበረሰቡ ዘር፣ ማንነት፣ የቆዳ ቀለም፣ ሀይማኖት፣ ዜግነት፣ ፆታና የጤንነት ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሊሆን ይችላል፡፡
አንድ ነገር በመጨረሻ ከሚታየው ውጤት በፊት እንደ የሁኔታው የሚያልፍባቸው ደረጃዎች አሉት፡፡ በርካታ የማህበራዊ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚያመለክቱት ከዘር ማጥፋት፣ ዜጎችን ከማፈናቀል፣ የጅምላ ጥቃትን ከማድረስ በፊት ወይንም ጀርባ የጥላቻ ንግግሮች አሉ፡፡ የጥላቻ ንግግሮች አንድን አካል ሰይጣናዊ መልክ ሰጥተው በመፈረጅ በተዳሚያኑ አዕምሮ ውስጥ ጥልቅ ጥላቻ እንዲኖር የማድረግ ኃይል አላቸው፡፡ ይህ ጥላቻ አንድ ጊዜ በታዳሚው አዕምሮ ውስጥ ከሰረፀ በኋላ ደግሞ ማህበራዊ መደላድልን በሚያገኝበት መልኩ በደንብ ይብላላል፡፡
ተብላልቶም አያበቃም፡፡ በጥላቻ አይን እንዲታይ የጥላቻው ስብከት ሰለባ የሆነው ማህበረሰብ ክፍል፤ በሂደት ሥርዓት ባለው መልኩ ቅርፅና ይዘት ተሰጥቶት ከተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዲገለል ይደረጋል፡፡ የጥላቻው ንግግር ሰለባ የሆነው ማህበረሰብ በሌላው አዕምሮ እንዲሳል (Portrayed) የተደረገበት መንገድ አደገኛ በመሆኑ፤ ሰለባውን በሂደት ከማህበራዊ ትስስር ከመነጠልና ከማግለል ባለፈ የተፈረጀውን የህብረተሰብ ክፍል ወደ ማጥቃትና ለማጥፋት ወደመነሳት ተግባር የሚገባበት ሁኔታ አለ፡፡
እናም ይህንን ሁኔታ ስንመለከት የጥላቻ ንግግር የዘር ማጥፋት ዋነኛ መሰረት መሆኑን እንረዳለን፡፡ የጥላቻ ንግግር ከጀርባው ያላስተናገደ አንዳች አይነት የዘር ማጥፋት በዓለማችን አልተፈፀመም፡፡ ናዚ በአይሁዳዊያን ላይ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት መፈፀም ከመጀመሩ በፊት ጀርመናዊያን በአይሁዶች ላይ የከፋ ጥላቻን እንዲያዳብሩ ሰፊ የፕሮፖጋንዳ መደላድልን ሰርቷል፡፡
ይህ ጥልቅ የሆነ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ በእያንዳንዱ ጀርመናዊ አዕምሮ ውስጥ በመስረፁ የአይሁዳዊያን በማጎሪያ ካምፕ ውስጥ በመርዝ ጭስ መገደል፣ ቆዳቸው እንደ እርድ እንስሳ በህይወት እያሉ መገፈፍና እንደ ዝንጀሮ የመድሀኒት መሞከሪያና መማሪያ መደረጉ እንደ ድል ብስራት ተደርጎ የሚነገርበት ሁኔታ ነበር፡፡ ይህም የናዚ ፀረ ሴማዊ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ምን ያህል የጀርመናዊያንን ከሌሎች ጋር አብሮ የመኖር መሰረት ንዶት እንደነበር ግልፅ ማሳያ ነው፡፡
የናዚን ትዕዛዝ የሚያስፈፅሙ አካላትም ቢሆኑ በዚህ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ስርፀት ውስጥ ያለፉ ስለነበሩ ሲፈፅሟቸው በነበሩት እኩይ ተግባራት ሁሉ ሊያመዛዝን የሚችለው ሰብዓዊ የህሊና ክፍላቸው ሙሉ በሙሉ የታወረ ስለነበር፤ ድርጊታቸውን እንደ ፅድቅ የሚቆጥሩበት ሁኔታ ነበር፡፡
በሩዋንዳ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ከደረሰው የዘር ማጥፋት ጀርባ በሬዲዮ ፕሮፖጋንዳ ጭምር የታገዘ የጥላቻ ንግግር ዘመቻ ነበር፡፡ በተለይ በቱትሲዎች ላይ የጅምላ ግድያው ሲፈፀም፤ የቱትሲዎችን ነፍስ ለማሳነስ “በረሮዎች” ወይንም “cockroaches” የሚል የጥላቻ ስያሜ ተሰጥቷቸው ነበር።
በመሆኑም አንድ ሁቱ፤ አንድን ቱትሲ ሲገድል የሚሰማው ስሜት በረሮ የገደለ ያህል ነበር ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ በሀገረ ሩዋንዳ በቱትሲና ሁቱ መካከል በተሰራጨው የዘር ጥላቻ ከአንድ ሚሊዮን ላላነሱ ሰዎች የዘር ጭፍጨፋ ምክንያት ሆኗል፡፡
ሀገሪቱ ከተረጋጋች በኋላ በርካታ በድርጊቱ የተሳተፉ ሩዋንዳዊያን በቁጥጥር ሥር ውለው ሲጠየቁ በጊዜው በነበረው የጥላቻ ንግግር በከባድ የበቀል ሥካር ስሜት ጥቃቱን የፈፀሙ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ እናም እነዚህ ሁኔታዎች ሲታዩ የጥላቻ ንግግር ምን ያህል ለጥፋት አቀጣጣይ ነዳጅ እንደሆነ ግልፅ ማሳያ ነው፡፡
በጥላቻ ንግግር የተመረዙ ሰዎች በዚያ በተመረዙበት ጉዳይ ሊያመዛዝኑ የሚችሉበት የአዕምሮ ክፍል(Reasoning Faculty ) ሙሉ በሙሉ ዝግ ነው፡፡ እናም በውስጣቸው ከሚነደው የጥላቻ እሳት የተነሳ የጠሉትን ሰው ሲያርዱ፣ ሲደበድቡ፣ ሲገሉና አካሉን ሲቆራርጡ የሚሰማቸው ውስጣዊ ስሜት፤ ፍርሀትና ፀፀት ሳይሆን፤ ደስታ ነው፡፡ ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት ጀርባ ያለው ነዳጅ ደግሞ ጥላቻ ነው፡፡ እናም የጥላቻ ንግግር ለጥፋት ያለው እምቅ አቅም ከ…እስከ.. ተብሎ የሚገለፅ አይደለም፡፡
.
.
.
Via Teshome Tadesse
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
.
ዛሬ የኢትዮጵያን ማህበራዊ ሚዲያ ለአፍታ የተመለከተ ሰው ሀገሪቱ ምን ያህል በጥላቻ እየታመሰች መሆኑን በቀላሉ መረዳት ይቻላል፡፡ በዚህ ዘመን በኢትዮጵያ ካለው ማንነትን መሰረት ካደረገ ግድያ፣ መፈናቀል፣ የንብረት ውድመትና ጅምላ ፍረጃ ጀርባ የጥላቻ ንግግር መኖሩ አጠያያቂ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ከሌላው ዜጋ ጋር የግል ፀብ ከሌለው በስተቀር፤ አንዱ ዜጋ ሌላውን ከመሬት ተነስቶ ሊያጠቃ የሚችልበት ምንም አይነት ምክንያት አይኖርም፡፡
ያም ሆኖ ከግለሰቦች ዕለታዊ ፀብ ያለፈ ጉዳይ ሲፈጠር ግን የጀርባውን መንስኤ በሚገባ መመርመር ያስፈልጋል፡፡ ከድርጊት ጀርባ ሀሳብ ያለ መሆኑ ግን ሊዘነጋ አይገባም፡፡
የጥላቻ ንግግር ሲባል አገላለፁ በቀጥታ ከአንደበት ወይም ከንግግር ጋር የተያያዘ ይመስላል እንጂ በውስጡ በርካታ ጥቅል ሀሳቦችን የያዘ መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ የጥላቻ ንግግር በአንደበት አማካኝነት በመድረክ ከሚነገረው ንግግር ጀምሮ በፅሁፍ እንደዚሁም በኤሌክትሮኒክስና በምስል ጭምር እስከሚገለፀው የጥላቻ ድርጊት ደርስ አካቶ የሚይዝ ነው፡፡
አገላለፁ በፈረንጆቹም ጭምር “Hate Speech” በሚለው አጠርር ስለሚታወቅ ጉዳዩ ከአንድበት ንግግር ጋር ብቻ የሚያያዝ ይመስላል፡፡ ሆኖም ትንታኔው በጥልቀት ሲመረመር የጥላቻ ንግግር (Hate Speech) መገለጫው አንድን ማህበረሰብ ወይንም ግለሰብ ለማጥቃት ለማሸማቀቅና ለማግለል በማሰብ በንግር፣ በምስል ፣በፅሁፍ፣ በካርቱን፣ በቅርፃ ቅርፅና በልዩ ልዩ ምልክቶች ተደግፎ ጥላቻን ማሰራጨት ማለት ነው፡፡ ጥላቻው የሚሰራጨው ከግለሰቡ ወይንም ከማህበረሰቡ ዘር፣ ማንነት፣ የቆዳ ቀለም፣ ሀይማኖት፣ ዜግነት፣ ፆታና የጤንነት ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሊሆን ይችላል፡፡
አንድ ነገር በመጨረሻ ከሚታየው ውጤት በፊት እንደ የሁኔታው የሚያልፍባቸው ደረጃዎች አሉት፡፡ በርካታ የማህበራዊ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚያመለክቱት ከዘር ማጥፋት፣ ዜጎችን ከማፈናቀል፣ የጅምላ ጥቃትን ከማድረስ በፊት ወይንም ጀርባ የጥላቻ ንግግሮች አሉ፡፡ የጥላቻ ንግግሮች አንድን አካል ሰይጣናዊ መልክ ሰጥተው በመፈረጅ በተዳሚያኑ አዕምሮ ውስጥ ጥልቅ ጥላቻ እንዲኖር የማድረግ ኃይል አላቸው፡፡ ይህ ጥላቻ አንድ ጊዜ በታዳሚው አዕምሮ ውስጥ ከሰረፀ በኋላ ደግሞ ማህበራዊ መደላድልን በሚያገኝበት መልኩ በደንብ ይብላላል፡፡
ተብላልቶም አያበቃም፡፡ በጥላቻ አይን እንዲታይ የጥላቻው ስብከት ሰለባ የሆነው ማህበረሰብ ክፍል፤ በሂደት ሥርዓት ባለው መልኩ ቅርፅና ይዘት ተሰጥቶት ከተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎቶች እንዲገለል ይደረጋል፡፡ የጥላቻው ንግግር ሰለባ የሆነው ማህበረሰብ በሌላው አዕምሮ እንዲሳል (Portrayed) የተደረገበት መንገድ አደገኛ በመሆኑ፤ ሰለባውን በሂደት ከማህበራዊ ትስስር ከመነጠልና ከማግለል ባለፈ የተፈረጀውን የህብረተሰብ ክፍል ወደ ማጥቃትና ለማጥፋት ወደመነሳት ተግባር የሚገባበት ሁኔታ አለ፡፡
እናም ይህንን ሁኔታ ስንመለከት የጥላቻ ንግግር የዘር ማጥፋት ዋነኛ መሰረት መሆኑን እንረዳለን፡፡ የጥላቻ ንግግር ከጀርባው ያላስተናገደ አንዳች አይነት የዘር ማጥፋት በዓለማችን አልተፈፀመም፡፡ ናዚ በአይሁዳዊያን ላይ ከፍተኛ የዘር ማጥፋት መፈፀም ከመጀመሩ በፊት ጀርመናዊያን በአይሁዶች ላይ የከፋ ጥላቻን እንዲያዳብሩ ሰፊ የፕሮፖጋንዳ መደላድልን ሰርቷል፡፡
ይህ ጥልቅ የሆነ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ በእያንዳንዱ ጀርመናዊ አዕምሮ ውስጥ በመስረፁ የአይሁዳዊያን በማጎሪያ ካምፕ ውስጥ በመርዝ ጭስ መገደል፣ ቆዳቸው እንደ እርድ እንስሳ በህይወት እያሉ መገፈፍና እንደ ዝንጀሮ የመድሀኒት መሞከሪያና መማሪያ መደረጉ እንደ ድል ብስራት ተደርጎ የሚነገርበት ሁኔታ ነበር፡፡ ይህም የናዚ ፀረ ሴማዊ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ምን ያህል የጀርመናዊያንን ከሌሎች ጋር አብሮ የመኖር መሰረት ንዶት እንደነበር ግልፅ ማሳያ ነው፡፡
የናዚን ትዕዛዝ የሚያስፈፅሙ አካላትም ቢሆኑ በዚህ የጥላቻ ፕሮፖጋንዳ ስርፀት ውስጥ ያለፉ ስለነበሩ ሲፈፅሟቸው በነበሩት እኩይ ተግባራት ሁሉ ሊያመዛዝን የሚችለው ሰብዓዊ የህሊና ክፍላቸው ሙሉ በሙሉ የታወረ ስለነበር፤ ድርጊታቸውን እንደ ፅድቅ የሚቆጥሩበት ሁኔታ ነበር፡፡
በሩዋንዳ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ከደረሰው የዘር ማጥፋት ጀርባ በሬዲዮ ፕሮፖጋንዳ ጭምር የታገዘ የጥላቻ ንግግር ዘመቻ ነበር፡፡ በተለይ በቱትሲዎች ላይ የጅምላ ግድያው ሲፈፀም፤ የቱትሲዎችን ነፍስ ለማሳነስ “በረሮዎች” ወይንም “cockroaches” የሚል የጥላቻ ስያሜ ተሰጥቷቸው ነበር።
በመሆኑም አንድ ሁቱ፤ አንድን ቱትሲ ሲገድል የሚሰማው ስሜት በረሮ የገደለ ያህል ነበር ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ በሀገረ ሩዋንዳ በቱትሲና ሁቱ መካከል በተሰራጨው የዘር ጥላቻ ከአንድ ሚሊዮን ላላነሱ ሰዎች የዘር ጭፍጨፋ ምክንያት ሆኗል፡፡
ሀገሪቱ ከተረጋጋች በኋላ በርካታ በድርጊቱ የተሳተፉ ሩዋንዳዊያን በቁጥጥር ሥር ውለው ሲጠየቁ በጊዜው በነበረው የጥላቻ ንግግር በከባድ የበቀል ሥካር ስሜት ጥቃቱን የፈፀሙ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ እናም እነዚህ ሁኔታዎች ሲታዩ የጥላቻ ንግግር ምን ያህል ለጥፋት አቀጣጣይ ነዳጅ እንደሆነ ግልፅ ማሳያ ነው፡፡
በጥላቻ ንግግር የተመረዙ ሰዎች በዚያ በተመረዙበት ጉዳይ ሊያመዛዝኑ የሚችሉበት የአዕምሮ ክፍል(Reasoning Faculty ) ሙሉ በሙሉ ዝግ ነው፡፡ እናም በውስጣቸው ከሚነደው የጥላቻ እሳት የተነሳ የጠሉትን ሰው ሲያርዱ፣ ሲደበድቡ፣ ሲገሉና አካሉን ሲቆራርጡ የሚሰማቸው ውስጣዊ ስሜት፤ ፍርሀትና ፀፀት ሳይሆን፤ ደስታ ነው፡፡ ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት ጀርባ ያለው ነዳጅ ደግሞ ጥላቻ ነው፡፡ እናም የጥላቻ ንግግር ለጥፋት ያለው እምቅ አቅም ከ…እስከ.. ተብሎ የሚገለፅ አይደለም፡፡
.
.
.
Via Teshome Tadesse
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢትዮ ቴሌኮም ከመኖሪያቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ ማሰባሰቢያ የሚውል አጭር የፅሁፍ መልዕክት ቁጥር እና የ40 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ። ኩባንያው እንዳስታወቀው የገንዘብ ድጋፉ እና ለገቢ ማሰባሰቢያ የሚውል አጭር የፅሁፍ መልክት ቁጥሩ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም እና በመንግስት እየተደረገ ያለውን ሀገር አቀፍ ጥረት ለማገዝ መሆኑን አስታውቋል። በዚህም መሰረት ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር እያደረጉ ያለውን የድጋፍ እንቅስቃሴ በተቀናጀ መልኩ ለማካሄድ ይረዳ ዘንድ 6020 አጭር የፅሁፍ መልክት ቁጥር ማዘጋጀቱን አስታውቋል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: በአሁኑ ሰአት የኢትዬጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን በወደቀበት ቦታ ለሟቾች የ12ኛ ቀንን ምክንያት በማድረግ ጸሎተ ፍታት እየተደረገላቸው ነው። ይህንን ያስተባበሩትና ወጪውንም የቻሉት #የአካባቢው_ነዋሪዎች ናቸው።
Via Sile
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via Sile
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር...
(TIKVAH-ETH)
ኢሳት ቲቪ በትላንትናው ዕለት ዘገባው በኢንጂነሪ ታከለ ኡማ ትዕዛዝ ለOBN ጋዜጠኞች የኮንዶሚንየም ቤት ተሰጣቸው ብሎ የሰራው ዘገባ ፍፁም የተሳሳተ ነው፡፡
እውነታው ፦
1. ጋዜጠኞቹ ጥያቄ ያቀረቡት ከሁለት ዓመት በፊት ነው!
2. የከተማ አስተዳደሩ በአሰራሩ መሠረት የቤቶች ኤጀንሲ ትብብር እንዲያደርግ እና የቀበሌ ቤቶች በኪራይ ውል እንዲሰጥ የሚገልፅ ደብዳቤ በ2/11/2010 (ማለትም ኢ/ር ታከለ ከመሾሙ 8 ቀናት በፊት)ፃፈ፡፡
3. ከከተማ አስተዳደሩ በተላለፈው መመርያ መሠረት እስከ አሁን ለአንድም የOBN ጋዜጠኛ የተሰጠ ኮንዶሚንየም የለም፡፡
4.ጥያቄ ካቀረቡ ጋዜጠኞች መካከል ለ 7 ጋዜጠኞች ብቻ የቀበሌ ቤት በኪራይ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
5. ኢ/ር ታከለ ኡማ ወደ ስልጣን ከመጣ በኃላ ለOBN ጋዜጠኞች አይደለም የኮንዶሚንየም ቤት ሊሰጣቸው በቀድሞ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ የተፈቀደው የቀበሌ ቤት እድልንም ተነጥቀናል በማለት ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ በኢ/ር ታከለ ኡማ ላይ ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡
-
-
-
-
-
እንዲህ እንዲህ ፤ እውነት እውነታው ለህዝባችን ግልፅ እያደረግን የጀመርነውን የለውጥ ጉዞ ከግብ እናደርሳለን፡፡
Via የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለTIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
(TIKVAH-ETH)
ኢሳት ቲቪ በትላንትናው ዕለት ዘገባው በኢንጂነሪ ታከለ ኡማ ትዕዛዝ ለOBN ጋዜጠኞች የኮንዶሚንየም ቤት ተሰጣቸው ብሎ የሰራው ዘገባ ፍፁም የተሳሳተ ነው፡፡
እውነታው ፦
1. ጋዜጠኞቹ ጥያቄ ያቀረቡት ከሁለት ዓመት በፊት ነው!
2. የከተማ አስተዳደሩ በአሰራሩ መሠረት የቤቶች ኤጀንሲ ትብብር እንዲያደርግ እና የቀበሌ ቤቶች በኪራይ ውል እንዲሰጥ የሚገልፅ ደብዳቤ በ2/11/2010 (ማለትም ኢ/ር ታከለ ከመሾሙ 8 ቀናት በፊት)ፃፈ፡፡
3. ከከተማ አስተዳደሩ በተላለፈው መመርያ መሠረት እስከ አሁን ለአንድም የOBN ጋዜጠኛ የተሰጠ ኮንዶሚንየም የለም፡፡
4.ጥያቄ ካቀረቡ ጋዜጠኞች መካከል ለ 7 ጋዜጠኞች ብቻ የቀበሌ ቤት በኪራይ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡
5. ኢ/ር ታከለ ኡማ ወደ ስልጣን ከመጣ በኃላ ለOBN ጋዜጠኞች አይደለም የኮንዶሚንየም ቤት ሊሰጣቸው በቀድሞ ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ የተፈቀደው የቀበሌ ቤት እድልንም ተነጥቀናል በማለት ጋዜጠኞች በተደጋጋሚ በኢ/ር ታከለ ኡማ ላይ ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡
-
-
-
-
-
እንዲህ እንዲህ ፤ እውነት እውነታው ለህዝባችን ግልፅ እያደረግን የጀመርነውን የለውጥ ጉዞ ከግብ እናደርሳለን፡፡
Via የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለTIKVAH-ETH
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢ/ር ታከለ ኡማ በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር #ድንገተኛ የስራ ምልከታ አደረጉ፡፡ ኢ/ር ታከለ ኡማ በክ/ከተማው ስር ባሉ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን የጎበኙ ሲሆን ከተጠቃሚዎች፣ ከክ/ከተማው አመራሮች እና ሰራተኞች ጋርም ተነጋግረዋል፡፡
Via @MayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via @MayorofficeAA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአማራ ክልል ለተፈናቀሉ ሰዎች በተዘጋጀው ቴሌቶን ከ626 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የአዲስ አበባ ገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡ ቴሌቶኑ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ያሳተፈ እንደነበር የመዲናዋ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ዋና ሰብሳቢ አቶ #መላኩ_ፈንታ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia