TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF #Tigray የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ። አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት ቡድን " አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም ” ብለዋል። ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም…
#Tigray

የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ።

ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል።

በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጡ አደራ በማለት ያሳስባል።

አዲሱ ተሿሚ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ኽርስቶስ ቀደም ሲል በዞኑ የእንደርታ ወረዳ አስተዳዳሪ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል። 

ወ/ሮ ሊያ ከቀናት በፊት የህወሓት ስራ አስፈጻሚ በመሆን መመረጣቸው ይታወሳል።

ህወሓት ባካሄደው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ያልሰጠው ፤ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን " ህጋዊ አይደለም " ያሉት ጉባኤ ካልተሳተፉት መካከል  ፦
- የምዕራባዊ
- የማእከላዊ
- የምስራቃዊ
- የደቡበዊ ዞኖች አስተዳዳሪዎች ይገኙበታል። 

ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው የስልጣን ሹምሽር ያደረጉበት የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ኣስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው የተሸሙት ወ/ሮ ሊያ ካሳ የተኩት አምስተኛ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ የሚቃወሙ የዞን አስተዳዳሪ ናቸው።

በትግራይ ካሉ 7 የዞን አስተዳደሮች አምስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ ሁለት ዞኖች ማለትም የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በተካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት  ተኽላይ ገ/መድህን የመቐለ ከተማ ደግሞ በተካሄደው ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይትባረክ ኣማሃና ኤልያስ ካሕሳይ ዋናና ምክትል በመሆን በመመራት ላይ ይገኛሉ።

ቀሪዎቹ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን አካሄድ የሚደግፉ የሁለት ዞን አስተዳዳሪዎች በያዙት ሃላፊነት የቆዩ ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው። 

የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከቀናት በፊት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ ተናግረው ነበር።

ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም " ነበር ያሉት።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
#Boeing 

በኢትዮጵያ የተከሰከሰው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ የቦይንግ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን ከአደጋው በፊት የኤሌክትሪክ ችግሮች እንዳሉበት የሚያሳየውን መረጃ መደበቁን የቀድሞ የቦይንግ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።

ፋውንዴሽን ፎር አቪየሽን ሴፍቲ የተባለ ቡድን የሚመሩት የቦይንግ የቀድሞ ሥራ አስኪያጅ ለ157 ሰዎች እልቂት የሆነው እና ከስድስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተከሰከሰው 737 ማክስ 9 አውሮፕላን የኤሌክትሪክ ችግሮች እንዳሉበት በኩባንያው ይታወቅ ነበር ብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በዝቅተኛ ከፍታ ላይ ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን እንደሚችል እና በርካታ እክሎች እንደነበሩበት ይፋ አድርገዋል።

ፋውንዴሽኑ በአሁኑ ወቅት እየበረሩ ያሉ ከ1000 በላይ የቦይንግ አውሮፕላኖች በሚመረቱበት ወቅት በነበሩ ችግሮች ምክንያት የኤሌክትሪክ ብልሽት ስጋት እንደተጋረጠባቸው ገልጿል።

ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ጉዞውን በጀመረ በስድስት ደቂቃዎች ውስጥ የተከሰከሰው አውሮፕላን የኤሌክትሪክ ብልሽቶች ነበሩበት ብለዋል።

አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ወቅት አዲስ ሞዴል 737 ማክስ 9 ነበር።

ከዚያ ቀደም ብሎ ተመሳሳይ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን በኢንዶኔዥያው አየር መንገድ አደጋ ተከስክሶ የ189 ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-08-24-2

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
DARE to change and be part of our vision!

Jasiri is looking for young individuals who exhibit discipline, attitude, resilience, and eagerness. We plan to create the next generation of high-impact African entrepreneurs.

If that sounds like something you want to be, apply for our fully-funded entrepreneurship development program using the link below

Apply now: https://bit.ly/3A8rxtV

For more information join our telegram channel https://t.iss.one/jasiri4Africa
#አብና🕯

" የ4ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል ፤ የ6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም ! "

በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 10 ሰዎች ሞተዋል።

የጠለምት ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋየ ወርቅነህ ምን አሉ ?

" የ4 ሰዎች አስከሬን በፍለጋ ተገኝቷል ፤ የቀሪ 6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም።

በጉዳቱ በ8 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። በደጃች ሜዳ ጤና ጣቢያ የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው።

በመሬት መንሸራተት አደጋው ከ35 በላይ የቤት እንሰሳት ሞተዋል። ከ30 ሄክታር በላይ በሰብል የተሸፈነ መሬት ጉዳት ደርሷል።

በደረሰው አደጋ 480 አባውራዎች እና 2 ሺህ 400 የቤተሰብ አባላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል። በቀበሌው ማዕከል ወደሚገኙ ማኅበራዊ ተቋማት በጊዜያዊ እንዲጠለሉ ተደርጓል።

በቀጣይም የመሬት መንሸራተት አደጋ ሊከሰትባቸው ይችላሉ በተባሉ የኖላ፣ ላጌ፣ ውፋ፣ ኩዳድ እና ጅብ ዋሻ አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። " #አሚኮ

@tikvahethiopia
#ዮናታን_ቢቲ_ፈርኒቸር
Yonatan BT Furniture

በዓሉን ምክንያት በማድረግ በቤት እቃዎቻችን ላይ ከ10 እስከ 25% ቅናሽ ማድረጋችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው! 🌼🌼 ይምጡ እና ይጎብኙን በዕቃዎቻችን ጥራትና ጥንካሬ ይደመማሉ!

የውበት እና የጥራት ዳር ድንበር ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር!

አድራሻችን፦
1.ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251995272727
2.ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251957868686
3.ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251993828282

👉 Telegram
👉 Facebook
👉 Instagram
👉 TikTok

#yonatanbtfurniture #furniture #modernfurniture #sofa #diningtable
6 ቀን ብቻ ቀረ!!!!

ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች ለሁላችንም በታላቅ ቅናሽ ከዲኤስቲቪ !

ዛሬውኑ የዲኤስቲቪ ዲኮደርዎን ከ800 ብር ቅናሽ ጋር በመግዛት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ፣ ቻምፒዮንስ ሊግ ፣ ላሊጋ ፣ ሴሪ አን ጨምሮ የሚወዱትን ክለብ በሚመርጡት ፓኬጅ ላይ እንደየምርጫዎ በዲኤስቲቪ ይዝናኑ!

ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች፣ ሁሉንም የቡድን ወኔ፣ ሁሉንም ትንታኔዎች ... ሁሉም በዲኤስቲቪ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#DStvEthiopia #ሁሉምያለውእኛጋርነው
#Telegram

የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ ፓቨል ዱሮቭ ፈረንሳይ ውስጥ ታሰረ።

በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ የዱሮቭን ሁኔታ በቅርብ እየተከታተለ ነው።

ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል።

ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች የተቃውሞ ሰልፍ እየጠሩ ናቸው።


የቴሌግራም መተግበሪያ መስራቹና ዋና ስራ አስኪያጁ ፓቨል ዱሮቭ ትላንት ቅዳሜ ምሽት ፈረንሳይ ፣ በፈረንሳይ ከፓሪስ ወጣ ብሎ በሚገኘው ቡርጌት ኤርፖርት በቁጥጥር ስር ውሏል።

ዱሮቭ በግል ጄቱ ተሳፍሮ ሊጓዝ ሲል ነው የታሰረው።

ለእረፍት ካቀናበት አዘርባጃን ተነስቶ በፈረንሳይ አድርጎ ሊጓዝ በኤርፖርቱ ባረፈበት ወቅት ነው መያዙ የታወቀው።

በፈረንሳይ የመጀመሪያ ደረጃ የፖሊስ ምርመራ አካል በሆነ የእስር ማዘዣ እንደተያዘም ነው የተነገረው።

ምርመራው ያተኮረው በቴሌግራም ሞደሬት / ቁጥጥር የማድረግ ክፍተት ላይ ነው። የፈረንሳይ ፖሊስ " ቴሌግራም የወንጀል ድርጊቶች፣ የአደገኛ እፅ ዝውውር፣ ሽብር፣ መኒ ላውንደሪንግ፣ ማጭበርበር ያለገደብ የሚተለለፉበት ሆኗል " በሚል ምርመራ ያደርጋል ነው የተባለው።

ዱሮቭ ዛሬ ፍርድ ቤት ይቀርባል ተብሏል።

ቴሌግራም በጉዳዩ ላይ እስካሁን ያለው ነገር የለም። የፈረንሳይ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ፖሊስም በጉዳዩ ላይ ምንም አላሉም።

የሩስያ ምክትል የዱማ አፈ-ጉባዔ ቭላዲላቭ ዳቫንኮቭ ዱሮቭ እንዲፈታ የሚጠይቅ መልዕክት ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ፅፈዋል።

እስራቱ በፖለቲካዊ ተነሳሽነት ያለውና የቴሌግራም ተጠቃሚዎችን ግላዊ መረጃ ለማግኘት መሳሪያ ሊሆን ይችላል ነው ያሉት።

በፈረንሳይ የሩስያ ኤምባሲ ጉዳዩን በቅርብ እየተከታተለ ነው።

ብሎገሮች በፈረንሳይ ኤምባሲዎች ተቃውሞ እየጠሩ ናቸው።

በርካቶች ቴሌግራም ላይ ያነጣጠረው የሃሳብ ነጻነትን መንፈግ ነው ብለዋል።

ቴሌግራም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ተጠቃሚዎች እጅ በጣም መጨመራቸው ይታወቃል።

በተለይ በሩስያ፣ ዩክሬን አካባቢ እጅግ በርካታ ተጠቃሚዎች ያሉት ሲሆን በመላው ዓለም ተጠቃሚዎቹ 1 ቢሊዮን ደርሰዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በበርካታ የዓለም ሀገራት መሪዎች እና ባለስልጣናት ዋነኛ ተመራጭ የመልዕክት ማስተላለፊያ መድረክ ሆኗል።

ዱሮቭ የሩስያ-ፈረንሳይ ዜግነት አለው።

#TF1TV #BFM

@tikvahethiopia
#GRED🇪🇹

የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ 3ኛው እና 4ኛውን ተርባይኖች ሥራ መጀመራቸውን ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ አሳውቀዋል።

" ሌሎቹ ዩኒቶች በተቀመጠላቸው እቅድ መሰረት በመከናወን ላይ ይገኛሉም " ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ " ወደታችኛው የአባይ ተፋሰስ ሀገራት ተጨማሪ ብስራት ከጉባ ተደምጧል " ብለው " የወንዝ ፍሰት ሳይስተጓጎል ከመቀጠሉም በተጨማሪ የግድቡ የውሃ ማስተንፈሻ በሮች ተከፍተው ተጨማሪ 2800 ሜኪ ውሃ በሰከንድ ማፍሰስ ጀምረዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የውሃ ፍሰትን በመቆጣጠር፣ የጎርፍ አደጋ ስጋትን በመቀነስ፣ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በተለይ በድርቅ ዘመን መጠኑ ያልዋዠቀ የውሃ አቅርቦት እንዲደርሳቸው ያደርጋል " ነው ያሉት።

" ይህ የተመዘነና የተመጣጠነ የውሃ ልቀት ግብርናን፣ የኃይል የማመንጨት ሥራን፣ በቀጠናው ያለ የሀብት አጠቃቀም ምጣኔን ለማጎልበት በእጅጉ ይጠቅማል " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ። ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል። በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ…
#TPLF #Tigray

በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ማንኛውም አይነት የስልጣን ሹምሽር አልቀበልም አለ።

በእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት " በማንኛው የሃላፊነት እርከን በራስ ፍላጎት የሚደረግ የስራ ምደባና ሹምሽር ተቀባይነት የለውም " ብሏል።

የእነ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ለሁሉም የዞንና የወረዳ የድርጅቱ ፅህፈት ጠቅሶ ባሰራጨው ደብዳቤ ፥ " ከሰርዓታዊና ተቋማዊ አሰራር ውጪ የሚካሄዱ የስራ ምደባዎች ኢህጋዊ ብቻ ሳይሆኑ ተጠያቂነትን ያስከትላሉ " ሲል አስጠንቅቋል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ነሃሴ 17/2016 ዓ.ም በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ መሾማቸው ዘግበናል።

ነሃሴ 18/2016 ዓ.ም የወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ደግሞ በሰሜናዊ ምዕራብ ዋና አስተዳዳሪና በቅርቡ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተክላይ ገ/መድህን ምትክ የክልሉ የስፓርት ኮሚሽን ኮምሽነር የነበሩት ተኽላይ ፍቓዱ ተሹመዋል።

ትግራይ ካሉዋት ሰባት የዞን አስተዳደሮች በአሁኑ ጊዜ ስድስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ የመቐለ ከተማ ብቻ በቅርቡ  በተካሄደ ጉባኤ  የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይመራል። 

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia