TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃሳብ ልዩነቱ ወደ ግጭት አያመራም " - አቶ ጌታቸው ረዳ ዓመታዊው የ2016 ዓ/ም የአሸንዳ በዓል ዛሬ ነሃሴ 16/2016 ዓ/ም በመላ ትግራይ መከበር ጀምሯል። በዓሉ እስከ ነሃሴ 24/2016 ዓ.ም አንደሚቀጥል የወጣው መርሃ ግብር ያመለክታል። በሌላ በኩል ፕሬዜዳንት ጌታቸው በ2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የተገነባ የ10.2 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ ሲመርቁ ፤ የአሸንዳ አደባባይ ግንባታ መሰረተ…
#ኣሸንዳ
ከሰሞኑን በፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ የከረመችው ትግራይ በደማቅ ሁኔታ የዘንድሮውን የኣሸንዳ በዓል እያከበረች ነው።
በዓሉን ለማክበር በርካታ እንግዶች ትግራይ ይገኛሉ።
በዓሉ እስከ ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ/ም በተለያዩ ስነስርዓቶች እየተከበረ ይቀጥላል።
በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሚከበረው የኣሸንዳ በዓል ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ሲሆን በዓሉ በልጃገረዶች ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበረል።
ልጃገረዶች አደባባይ ወጥተው ይህን በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።
የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።
የሌሎች ሃሳቦች፣ ጭፈራዎች እና ትእይንቶች እንዲታዩ የሚጋብዝ በዓል ከመሆኑም ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።
ፎቶ፦ ትግራይ ቲቪ (ኖርዘርን ስታር ሆቴል፣ መቐለ ነሐሴ 17)
#Ashenda #Tigray
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን በፖለቲካ ትኩሳት ውስጥ የከረመችው ትግራይ በደማቅ ሁኔታ የዘንድሮውን የኣሸንዳ በዓል እያከበረች ነው።
በዓሉን ለማክበር በርካታ እንግዶች ትግራይ ይገኛሉ።
በዓሉ እስከ ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ/ም በተለያዩ ስነስርዓቶች እየተከበረ ይቀጥላል።
በትግራይ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሚከበረው የኣሸንዳ በዓል ፍቅር፣ ይቅር ባይነትና መልካም ተግባቦት በተግባር የሚንጸባረቅበት በዓል ሲሆን በዓሉ በልጃገረዶች ይበልጥ ትኩረት ተሰጥቶት ይከበረል።
ልጃገረዶች አደባባይ ወጥተው ይህን በዓልን በድምቀት ያከብራሉ።
የበዓሉ ይዘት በዋናነት ህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ መልካም ተግባቦቶች፣ ፍቅርንና ይቅር ባይነት ላይ ያነጣጠረ ነው።
የሌሎች ሃሳቦች፣ ጭፈራዎች እና ትእይንቶች እንዲታዩ የሚጋብዝ በዓል ከመሆኑም ባለፈ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት አይንፀባረቅበትም።
ፎቶ፦ ትግራይ ቲቪ (ኖርዘርን ስታር ሆቴል፣ መቐለ ነሐሴ 17)
#Ashenda #Tigray
@tikvahethiopia
የአማራ ህዝብ አስተማማኝ ሰላምን ካጣ ዓመታት አልፈዋል።
በየጊዜው የሚያገረሸው የተኩስ ልውውጥ የሰዎችን ህይወት መቅጠፉን ቀጥሏል።
በክልሉ ያሉ ሲቪል ሰዎች በሰላም ወጥቶ መግባት ቅንጦት እንደሆነ ይናገራሉ።
የኢኮኖሚውና የሰላም እንቅስቃሴውም ከሌሎች ክልሎች አንጻር እየተዳከመ ይገኛል።
ከዚህ ቀደም የሀገርና የውጭ ቱሪስት የሚጎርፍባቸው አካባቢዎች ዛሬ ሰው አይታይባቸውም።
በዚህ ስራ የተሰማሩ ዜጎችም ስራ አጠተው ቁጭ ብለዋል።
አስተያየቱን የሰጠን ወጣት አስጎብኚ ፥ " ይኸው ግራ ተጋብተን ቁጭ ብለናል። የሚበላ ማግኘት አልቻልም። ይህ ሁኔታ በዚህ እየቀጠለ ከሄደ ከአሁኑም በላይ ከባድ መዘዝ ይዞ ይመጣል " ሲል ገልጿል።
የሸቀጦች ዋጋም ቀደሞም ተወዷል አሁን ደግሞ ጭራሽ ዶላር ጨምሯል ተብሎ ተሰቅሏል።
ከተኩስ ልውውጥ ባለፈ እገታ ፣ ዘረፋ የተለመደ ተግባር እየሆነ ነው።
ገንዘብ ያላቸው ባለሃብቶች ባለው የፀጥታ ችግር ከክልሉ ውጭ ሃብታቸውን ይዘው እየሄዱ ናቸው።
አንድ ቃላቸውን የሰጡን የንግድ ሰው ፣ ባህር ዳር ላይ እሳቸውን ጨምሮ ሌሎች በሚፈለገው ልክ ስራ መስራት ስላልተቻለ እንዲሁም ጥናት ተደርጎ በሚፈጸመው እገታ ምክንያት የሚወዱትን ከተማ ለቀው አ/አ ለመግባት መገደዳቸውን ጠቁመዋል።
ከምንም በላይ ግን በዝቅተኛ ኢኮኖሚ ላይ ያለው ህዝብ ፣ ህጻናት፣ እናቶች ከፍተኛ ዋጋ እየከፈሉ ናቸው።
ትራንስፖርት በየጊዜው ስለሚቋረጥ ለህክምናም ይሁን ለሌላ ጉዳይ መንቀሳቀስ አልተቻለም። የአየር ትራንስፖርት ለመጠቀም አቅም የለም።
አንድ ደብረ ማርቆስ ያሉ እናት በሰጡት ቃል " እኔ ልጄን ማሳከም ነበረብኝ አዲስ አበባ ፥ ግን ሰሞኑን የጸጥታ ሁኔታው አስጊ ስለነበር አልተቻለም። ፈጣሪን እየተማጸንኩ ቁጭ ብያለሁ " ብለዋል።
አንድ የባህር ዳር ነዋሪ በበኩላቸው ፥ በየጊዜው የሚያገረሸው ጦርነት ምክንያት ህዝቡ የከፋ ቀውስ ላይ እንደጣለው ይህም ደግሞ አሁን ከአመት እንዳለፈው ገልጸዋል።
ከዚህ ባለፈው በባህር ዳር በየጊዜው የሚጣለው ቦምብ ከፍተኛ የደህንነት ስጋት እንደደቀነ ምሽት ላይ ለመንቀሳቀስ እንደማይችል ተናግረዋል።
ከባህር ዳር ወደ አ/አ በትራንስፖርት መሄድ አስቸጋሪ እንደሆነ ፣ ያለው የዋጋ ግሽበትም ማህበረሰቡን ለከፋ ኢኮኖሚያዊ ችግር እየጋለጠ እንደሆነ አመልክተዋል።
በተለያዩ ቦታዎችም የመድሃኒት አቅርቦት አሳሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል።
" አሁን አሁን በሰላም ወጥቶ መግባት ቅንጦት " የሚሉት ነዋሪው ፤ የአማራ ጉዳይ ግን ችላ እንደተባለ ተናግረዋል።
ሌላው የተማሪዎች ጉዳይ ሲሆን ዘንድሮ ብዙ ተማሪ ሀገር አቀፍ ፈተና ላይ አልተቀመጠም። አማራ ክልል ጂኒየስ የሚባሉ ተማሪዎችን በየዓመቱ ያፈራል። በጦርነት ውስጥ እንኳን ሆኖ ከሀገር ከፍተኛውን ውጤት የሚያመጡት የዚሁ ክልል ልጆች ናቸው።
አንድ 12ኛ ክፍል ፈተና መፈተን ያልቻለ የጎጃም አካባቢ ተማሪ ፥ " ቀጣይ እንፈትናለን ይላሉ መቼ እንደሆነ አናውቅም። እኛ አካባቢ ዛሬም ድረስ መረጋጋት የለም። ይኸው እድሜያቻን በከንቱ ማለቁ የማይቀር ይመስላል " ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።
የአማራ ህዝብ ከዓመታት በፊት የትግራይ ጦርነት ተስፋፍቶ በመጣበት ወቅት ለወራት በከፍተኛ ስቃይ ፣ መከራ እና በደል ውስጥ አልፏል።
ከሲቪሎች ግድያ፣ ጉዳት ባለፈ ለበርካታ ወራት ኢኮኖሚው ቆሞ ነበር። ጦርነቱ በሰላም ስምምነት ከቆመ በኃላ ደግሞ ክልሉ ዛሬም ድረስ በሌላ ቀውስ ውስጥ ነው ያለው።
ባለፉት ዓመታት በክልሉ ዘላቂ መረጋጋት ታይቶበት አያውቅም። ይህ ሁኔታ በቀጣይ አመታት በሁሉም ዘርድ የሚያሳድረው ጫና ከፍተኛ ነው።
#Amhara #Ethiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF #Tigray የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ተናገሩ። አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩት ቡድን " አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም ” ብለዋል። ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም…
#Tigray
የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ።
ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጡ አደራ በማለት ያሳስባል።
አዲሱ ተሿሚ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ኽርስቶስ ቀደም ሲል በዞኑ የእንደርታ ወረዳ አስተዳዳሪ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
ወ/ሮ ሊያ ከቀናት በፊት የህወሓት ስራ አስፈጻሚ በመሆን መመረጣቸው ይታወሳል።
ህወሓት ባካሄደው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ያልሰጠው ፤ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን " ህጋዊ አይደለም " ያሉት ጉባኤ ካልተሳተፉት መካከል ፦
- የምዕራባዊ
- የማእከላዊ
- የምስራቃዊ
- የደቡበዊ ዞኖች አስተዳዳሪዎች ይገኙበታል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው የስልጣን ሹምሽር ያደረጉበት የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ኣስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው የተሸሙት ወ/ሮ ሊያ ካሳ የተኩት አምስተኛ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ የሚቃወሙ የዞን አስተዳዳሪ ናቸው።
በትግራይ ካሉ 7 የዞን አስተዳደሮች አምስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ ሁለት ዞኖች ማለትም የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በተካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተኽላይ ገ/መድህን የመቐለ ከተማ ደግሞ በተካሄደው ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይትባረክ ኣማሃና ኤልያስ ካሕሳይ ዋናና ምክትል በመሆን በመመራት ላይ ይገኛሉ።
ቀሪዎቹ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን አካሄድ የሚደግፉ የሁለት ዞን አስተዳዳሪዎች በያዙት ሃላፊነት የቆዩ ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።
የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከቀናት በፊት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ ተናግረው ነበር።
ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም " ነበር ያሉት።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዜያዊ አስተደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የስልጣን ሽምሹር አደረጉ።
ፕሬዜዳንቱ በህወሓት የፓሊት ቢሮ አባልዋ ወ/ሮ ሊያ ካሳ ምትክ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ክርስቶስ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ በማድረግ ሾመዋል።
በአቶ ጌታቸው ረዳ ተፈርሞ ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም የወጣው ደብዳቤ ፤ ፀጋይ ገብረተኽለ የዞኑ አስተዳዳሪ በመሆን የሚገባቸው ጥቅም ተጠብቆላቸው ሃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጡ አደራ በማለት ያሳስባል።
አዲሱ ተሿሚ ፀጋይ ገብረተኽለ ገ/ኽርስቶስ ቀደም ሲል በዞኑ የእንደርታ ወረዳ አስተዳዳሪ እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
ወ/ሮ ሊያ ከቀናት በፊት የህወሓት ስራ አስፈጻሚ በመሆን መመረጣቸው ይታወሳል።
ህወሓት ባካሄደው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ያልሰጠው ፤ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበር የሚገኙባቸው 14 የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትና የማእከላዊ የቁጥጥር ኮሚሽን " ህጋዊ አይደለም " ያሉት ጉባኤ ካልተሳተፉት መካከል ፦
- የምዕራባዊ
- የማእከላዊ
- የምስራቃዊ
- የደቡበዊ ዞኖች አስተዳዳሪዎች ይገኙበታል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው የስልጣን ሹምሽር ያደረጉበት የደቡባዊ ምስራቅ ዞን ኣስተዳዳሪ ፀጋይ ገ/ተኽለ ህወሓት ባካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው የተሸሙት ወ/ሮ ሊያ ካሳ የተኩት አምስተኛ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ የሚቃወሙ የዞን አስተዳዳሪ ናቸው።
በትግራይ ካሉ 7 የዞን አስተዳደሮች አምስቱ የእነ ዶ/ር ደብረፂዮን አካሄድ በሚቃወሙ የሚመሩ ሲሆኑ ሁለት ዞኖች ማለትም የሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በተካሄደው ጉባኤ የፓሊት ቢሮ አባል ሆነው በተመረጡት ተኽላይ ገ/መድህን የመቐለ ከተማ ደግሞ በተካሄደው ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ሆኖው በተመረጡት ይትባረክ ኣማሃና ኤልያስ ካሕሳይ ዋናና ምክትል በመሆን በመመራት ላይ ይገኛሉ።
ቀሪዎቹ የእነ ዶ/ር ደብረፅዮን አካሄድ የሚደግፉ የሁለት ዞን አስተዳዳሪዎች በያዙት ሃላፊነት የቆዩ ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።
የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከቀናት በፊት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመምራት ህወሓት " የራሱን ሰዎች መመደብ ይችላል " ሲሉ ተናግረው ነበር።
ሊቀመንበሩ ፤ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚገኙበት ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ህወሓትን ወክሎ ነው የገባው። አሁን ህወሓትን መወከል አይችልም " ነበር ያሉት።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
#Boeing
በኢትዮጵያ የተከሰከሰው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ የቦይንግ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን ከአደጋው በፊት የኤሌክትሪክ ችግሮች እንዳሉበት የሚያሳየውን መረጃ መደበቁን የቀድሞ የቦይንግ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ፋውንዴሽን ፎር አቪየሽን ሴፍቲ የተባለ ቡድን የሚመሩት የቦይንግ የቀድሞ ሥራ አስኪያጅ ለ157 ሰዎች እልቂት የሆነው እና ከስድስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተከሰከሰው 737 ማክስ 9 አውሮፕላን የኤሌክትሪክ ችግሮች እንዳሉበት በኩባንያው ይታወቅ ነበር ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በዝቅተኛ ከፍታ ላይ ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን እንደሚችል እና በርካታ እክሎች እንደነበሩበት ይፋ አድርገዋል።
ፋውንዴሽኑ በአሁኑ ወቅት እየበረሩ ያሉ ከ1000 በላይ የቦይንግ አውሮፕላኖች በሚመረቱበት ወቅት በነበሩ ችግሮች ምክንያት የኤሌክትሪክ ብልሽት ስጋት እንደተጋረጠባቸው ገልጿል።
ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ጉዞውን በጀመረ በስድስት ደቂቃዎች ውስጥ የተከሰከሰው አውሮፕላን የኤሌክትሪክ ብልሽቶች ነበሩበት ብለዋል።
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ወቅት አዲስ ሞዴል 737 ማክስ 9 ነበር።
ከዚያ ቀደም ብሎ ተመሳሳይ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን በኢንዶኔዥያው አየር መንገድ አደጋ ተከስክሶ የ189 ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-08-24-2
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የተከሰከሰው ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ የቦይንግ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን ከአደጋው በፊት የኤሌክትሪክ ችግሮች እንዳሉበት የሚያሳየውን መረጃ መደበቁን የቀድሞ የቦይንግ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ።
ፋውንዴሽን ፎር አቪየሽን ሴፍቲ የተባለ ቡድን የሚመሩት የቦይንግ የቀድሞ ሥራ አስኪያጅ ለ157 ሰዎች እልቂት የሆነው እና ከስድስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተከሰከሰው 737 ማክስ 9 አውሮፕላን የኤሌክትሪክ ችግሮች እንዳሉበት በኩባንያው ይታወቅ ነበር ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በዝቅተኛ ከፍታ ላይ ከቁጥጥር ውጭ ሊሆን እንደሚችል እና በርካታ እክሎች እንደነበሩበት ይፋ አድርገዋል።
ፋውንዴሽኑ በአሁኑ ወቅት እየበረሩ ያሉ ከ1000 በላይ የቦይንግ አውሮፕላኖች በሚመረቱበት ወቅት በነበሩ ችግሮች ምክንያት የኤሌክትሪክ ብልሽት ስጋት እንደተጋረጠባቸው ገልጿል።
ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ተነስቶ ጉዞውን በጀመረ በስድስት ደቂቃዎች ውስጥ የተከሰከሰው አውሮፕላን የኤሌክትሪክ ብልሽቶች ነበሩበት ብለዋል።
አውሮፕላኑ በተከሰከሰበት ወቅት አዲስ ሞዴል 737 ማክስ 9 ነበር።
ከዚያ ቀደም ብሎ ተመሳሳይ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን በኢንዶኔዥያው አየር መንገድ አደጋ ተከስክሶ የ189 ሰዎች ሕይወት ተቀጥፏል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-08-24-2
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
DARE to change and be part of our vision!
Jasiri is looking for young individuals who exhibit discipline, attitude, resilience, and eagerness. We plan to create the next generation of high-impact African entrepreneurs.
If that sounds like something you want to be, apply for our fully-funded entrepreneurship development program using the link below
Apply now: https://bit.ly/3A8rxtV
For more information join our telegram channel https://t.iss.one/jasiri4Africa
Jasiri is looking for young individuals who exhibit discipline, attitude, resilience, and eagerness. We plan to create the next generation of high-impact African entrepreneurs.
If that sounds like something you want to be, apply for our fully-funded entrepreneurship development program using the link below
Apply now: https://bit.ly/3A8rxtV
For more information join our telegram channel https://t.iss.one/jasiri4Africa
#አብና🕯
" የ4ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል ፤ የ6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም ! "
በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 10 ሰዎች ሞተዋል።
የጠለምት ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋየ ወርቅነህ ምን አሉ ?
" የ4 ሰዎች አስከሬን በፍለጋ ተገኝቷል ፤ የቀሪ 6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም።
በጉዳቱ በ8 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። በደጃች ሜዳ ጤና ጣቢያ የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው።
በመሬት መንሸራተት አደጋው ከ35 በላይ የቤት እንሰሳት ሞተዋል። ከ30 ሄክታር በላይ በሰብል የተሸፈነ መሬት ጉዳት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ 480 አባውራዎች እና 2 ሺህ 400 የቤተሰብ አባላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል። በቀበሌው ማዕከል ወደሚገኙ ማኅበራዊ ተቋማት በጊዜያዊ እንዲጠለሉ ተደርጓል።
በቀጣይም የመሬት መንሸራተት አደጋ ሊከሰትባቸው ይችላሉ በተባሉ የኖላ፣ ላጌ፣ ውፋ፣ ኩዳድ እና ጅብ ዋሻ አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። " #አሚኮ
@tikvahethiopia
" የ4ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል ፤ የ6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም ! "
በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 10 ሰዎች ሞተዋል።
የጠለምት ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋየ ወርቅነህ ምን አሉ ?
" የ4 ሰዎች አስከሬን በፍለጋ ተገኝቷል ፤ የቀሪ 6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም።
በጉዳቱ በ8 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። በደጃች ሜዳ ጤና ጣቢያ የሕክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ነው።
በመሬት መንሸራተት አደጋው ከ35 በላይ የቤት እንሰሳት ሞተዋል። ከ30 ሄክታር በላይ በሰብል የተሸፈነ መሬት ጉዳት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ 480 አባውራዎች እና 2 ሺህ 400 የቤተሰብ አባላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተፈናቅለዋል። በቀበሌው ማዕከል ወደሚገኙ ማኅበራዊ ተቋማት በጊዜያዊ እንዲጠለሉ ተደርጓል።
በቀጣይም የመሬት መንሸራተት አደጋ ሊከሰትባቸው ይችላሉ በተባሉ የኖላ፣ ላጌ፣ ውፋ፣ ኩዳድ እና ጅብ ዋሻ አካባቢዎች የሚኖሩ ወገኖች ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። " #አሚኮ
@tikvahethiopia
#ዮናታን_ቢቲ_ፈርኒቸር
Yonatan BT Furniture
በዓሉን ምክንያት በማድረግ በቤት እቃዎቻችን ላይ ከ10 እስከ 25% ቅናሽ ማድረጋችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው! 🌼🌼 ይምጡ እና ይጎብኙን በዕቃዎቻችን ጥራትና ጥንካሬ ይደመማሉ!
የውበት እና የጥራት ዳር ድንበር ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር!
አድራሻችን፦
1.ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251995272727
2.ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251957868686
3.ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251993828282
👉 Telegram
👉 Facebook
👉 Instagram
👉 TikTok
#yonatanbtfurniture #furniture #modernfurniture #sofa #diningtable
Yonatan BT Furniture
በዓሉን ምክንያት በማድረግ በቤት እቃዎቻችን ላይ ከ10 እስከ 25% ቅናሽ ማድረጋችንን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው! 🌼🌼 ይምጡ እና ይጎብኙን በዕቃዎቻችን ጥራትና ጥንካሬ ይደመማሉ!
የውበት እና የጥራት ዳር ድንበር ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር!
አድራሻችን፦
1.ዊንጌት አደባባዩን ተሻግሮ: +251995272727
2.ፒያሳ እሪ በከንቱ : +251957868686
3.ሲ ኤም ሲ አደባባዩን አለፍ ብሎ: +251993828282
👉 Telegram
👉 TikTok
#yonatanbtfurniture #furniture #modernfurniture #sofa #diningtable