TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : በዛሬውና ነገ በሚውለው በዶላር ምዛሬ ዋጋ መግዣው ላይ የ12 ብር ልዩነት ፤ በመሸጫው ላይ የ15 ብር ልዩነት ታይቷል። ዛሬ የነበረው መግዣ 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም ነበር። ነገ ማለትም #ቅዳሜ ሐምሌ 27 የሚውለው የምንዛሬ ዋጋ መግዣው 95 ብር ከ6931 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 101 ብር ከ4347 ሳንቲም ነው። ሌላው በጣም ልዩነት የታየበት…
#DailyExchangeRate

ዛሬግል ባንኮች ያለው የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ከላይ ተያይዟል።

ከላይ የ7 የግል ባንኮች ዕለታዊ ምዛሬ ቀርቧል።

ከነዚህ ባንኮች 3ቱ ማለትም ኦሮሚያ፣ አባይ ፣ ዳሽን የዶላር መግዣቸውን በ90 ብር አድርገው በሳንቲም ይለያያሉ መሸጫቸው ግን ልዩነት አለው።

ኦሮሚያ የዶላር መግዣው 102 ብር ከ3848 ሳንቲም ነው ፤ ሲሆን በአባይ 102 ብር ከ9560 ሳንቲም ፤ በዳሽን ደግሞ 100 ብር ከ7768 መሸጫው ነው።

ሌሎቹ ባንኮች አቢሲንያ፣ አዋሽ ፣ ሲዳማና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንኮች መሸጫቸውም መግዣቸውም ይለያያል።

አቢሲንያ ዛሬ ሁለት (ጥዋት እና ከሰዓት) የዶላር ምንዛሬ ነው የተጠቀመው ።

ጥዋት ላይ በ90 ብር ከ0690 ሳንቲም መግዣ መሸጫ ደግሞ 106 ብር ከ7318 ሳንቲም ነበር ፤ አሁን ይፋ ባደረገው የከሰዓት ምንዛሬ ግን መግዣውን ወደ 96 ብር ከ3738 ሳንቲም መሸጫውን 107 ብር ከ9387 ሳንቲም አሳድጎታል።

አዋሽ ዶላር መግዣው 96 ብር ከ3011 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 106 ብር ከ8941  ሳንቲም ነው። ሲዳማ በ96 ብር ከ6500 ገዝቶ በ106 ብር ከ3110 ሳንቲም እንደሚሸጥ ገልጿል። ኦሮሚያ ህብረት ስራ በበኩሉ መፍዣው 97 ብር ከ7329 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 107 ብር ከ5062 ሳንቲም ነው።

ከዶላር ውጭ ያሉ ምንዛሬዎችም በግል ባንኮች ዋጋቸው ጨምሯል። ዝርዝሩን ከላይ ይመልከቱ።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ባንኮች ይፋ ከሚያደርጉት የውጭ ምንዛሬ መግዣና መሸጫ ዋጋ ውጭ የሚያስከፍሉትን ኮሚሽን እና ሌላ ክፍያ እንዲያቆሙ ወስኗል።

እንዲህ ያሉ ክፍያዎችን ካስከፈሉ እንኳን ከመግዣና መሸጫ ዋጋው ጋር አካተው አንድ ላይ ለደንበኞቻቸው ይፋ እንዲያደርጉት ተብሏል።

ይህም የውጭ ምንዛሬ ግዥና ሽያጭ ላይ ግልፅነትን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተመላክቷል።

በሌላ በኩል ግን ይህ አሰራር ደንበኞች ከውጭ ሀገር ግዢ ለመፈፀም LC ለመክፈት ሲጠይቁ የሚኖረውን ግብይት አይመለከትም ተብሏል፡፡

ውሳኔው ከዛሬ ጀምሮ በስራ ላይ መዋል መጀመሩንም ብሔራዊ ባንክ አሳውቋል።

#ShegerFMRADIO #NBE

@tikvahethiopia
ፎቶ፦ ይህ በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ የተከሰተ የመሬት መንሸራተት ነው።

ትላንት ቀን 10:30 በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 1 ሰው ሲሞት ፣ 1 ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።

8 የአከባቢው ነዋሪዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።

በተከሰተው ናዳ አደጋ ህይወቷ ያለፈው የ11 ዓመት ሴት ልጅ ናት። አብራት የነበረችው ወላጅ እናቷ ደግሞ ከአደጋው ለጥቂት ተርፋለች።

#WolaitaZoneGov

@tikvahethiopia
📢Attention aspiring candidates in Ethiopia 🇪🇹🇪🇹! We invite you for an info session where the Jasiri team will provide insights into the Jasiri Talent Investor program and answer any questions you may have. Only 150 slots available. Please RSVP for the session at this link bit.ly/3WrVIDV.

#Jasiri4Africa
#SafariconEthiopia

እለታዊ 1 ጊ.ባ ጥቅል በ25 ብር ከ M-PESA ስንገዛ፤ ለ 24 ሰዓት የሚቆይ  የ50 %  ጉርሻ  ወይም 500 ሜ.ባ. አለን! 

በሽ በሽ በM-PESA !
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom  #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #TPLF " እኔ ሳላውቀው ያለፈው ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ጉባኤ ለማካሄድ በድብቅ ሲሰራ ነበር። ይህ እንዲሆን ለምን አስፈለገ ?  "  - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር እና የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ ጉዳዮች አስመልክተው ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ቃለመጠይቅ ሰጥተው ነበር። አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ? - የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት…
#TPLF

የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ አባላት ነጋ አሰፋ እና ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ ህወሓት ለማካሄድ ካቀደው ድርጅታዊ ጉባኤ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለድምጺ ወያነ ሰጥተው ነበር።

በዚህም ፤ " ጉባኤው እንዳይካሄድ የተቋወመ የለም " ብለዋል።

ጥያቄያው መተማመንንና መግባባት የተደረሰበት አሳታፊ፣ ግልፅና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን የማድረግ ጉዳይ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከጉባኤው በፊት መታየትን መጥራት ያለባቸው በርካታ ጉዳዮች እንዳሉ የጠቀሱት ከፍተኛ አመራሮቹ " ድርጅቱ ከፍተኛ የሆነ የስትራቴጂክ አመራር ውድቀት አጋጥሞታል ሊካሄድ የታሰበው ጉባኤ ደግሞ ይህንን በመሰረቱ ሊፈታ የሚችል መሆን ይገባዋል "  ሲሉ ተናግረዋል።

" ከጉባኤው በፊት የተካሄደው ደም አፋሳሽና አሰቃቂ ጦርነት ሂደቱና ውጤቱ በጥልቀት መገምገም ይቅደም " ሲሉም ተደምጠዋል።

አሁን የሚታየው ልዩነት ከጉባኤው በፊት በመግባባት እና በመተማመን መፈታት እንደሚገባ አመልክተው " በችኮላ እንዲካሄድ ይታሰበው ጉባኤ የግል ሰብእናና ስልጣን ከማስጠበቅ ያለፈ እርባና የለውም " ብለውታል።

" የህዝብና የድርጅቱ ጥቅም የሚያስቀድም አካል ጉባኤ ለማካሄድ መጣደፍ የለበትም "  ሲሉ አሳስበዋል።

#TPLF #Tigray

@tikvahethiopia
#ግብር

የግብር ግዴታቸውን ለመወጣት የሄዱ ጠበቆች ነጋዴ የሚያቀርበውን ሂሳብ መዝገብ ካላቀረባችሁ አትስተናገዱም በሚል መጉላላት እየደረሰባቸዉ ነው።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማሕበር የበጀት ዓመቱን የግብር ግዴታቸውን ለመወጣት የሄዱ ጠበቆች " ነጋዴ የሚያቀርበውን ሂሳብ መዝገብ አይነት ከተመዘገበ ካፒታል ጋር ካላቀረባችሁ አትስተናገዱም " በሚል መጉላላት እየደረሰባቸው እንደሚገኝ አስታውቋል።

ቅሬታዉን ለፍትህ ሚኒስትር ያቀረበዉ ማህበሩ  ከጥብቅና አገልግሎት አሰጣጥ እና ከግብር አከፋፈል ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ ሲያጋጥም የቆየውን ችግር በዘላቂነት እንደሚቀርፍ የታመነበት ዝርዝር መመሪያ ሳይወጣና በሥራ ላይ እንዲውል ሳይደረግ የ2016 በጀት ዓመት የግብር መክፈያ ወቅት ተጀምሯል ብሏል።

ይህን ተከትሎ ፍትህ ሚኒስትር ለገንዘብ ሚኒስትር እና ለአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ደብዳቤዉ ጽፏል።

በዚህም የጠበቆችን ታክስ አከፋፈል በተመለከተ ዝርዝር መመሪያ ወጥቶ ችግሩ ወጥ በሆነ መልኩ በዘላቂነት እስከሚፈታ ድረስ ከዚህ ቀደም በነበሩ ዓመታት ሲስተናገዱበት በቆየው ነባር አሰራር የ2016 በጀት ዓመት የግብር ግዴታቸውን እንዲወጡ እንዲደረግ ጠይቋል።

በዚህ ምላሽ ሊያገኙ እንደሚችል በተገለፀበት ደብዳቤ  ጠበቆች " ነጋዴ የሚያቀርበውን ሂሳብ መዝገብ አይነት ከተመዘገበ ካፒታል ጋር ካላቀረባችሁ አትስተናገዱም " በሚል የሚደርስባቸዉን መጉላላት ሊቀርፍ ይችላል የሚል እምነት ተጥሎበታል።

#CapitalNewspaper #Ethiopia

@tikvahethiopia
#CentralEthiopia

" እባካችሁ የሰራንበትን ፤ የላባችንን ክፍያ ስጡን " እያሉ ቀን በቀን የሚጮሁ ዜጎች ባሉባት ሀገር እዚህ ጋር ደግሞ ጭራሽ የመንግሥት ሰራተኛ ላልሆኑ ሰዎች በመቶ ሺዎች ብር ወጥቶ ተከፍሏል።

የመንግስት ሰራተኛ ላልሆኑ 19 ሰዎች  ደመወዝ ሲከፍሉ ተደርሶባቸው በሙስና ወንጀል የተከሰሱ 3 ግለሰቦች በጽኑ እስራት እና በገንዘብ መቀጮ መቀጣታቸው ተሰምቷል።

በተፈፀመው ወንጀል ተሳታፊ በመሆን ሳይቀጠሩ ደመወዝ ይከፈላቸው የነበሩ ተከሳሾችም በ3 ዓመት ፅኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።

የሙስና ወንጀሉ የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀድያ ዞን ሻሾጎ ወረዳ ነው።

የሀድያ ዞን ዐቃቤ ህግ ህዳር 30/2016 ዓ.ም ለሀድያ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ፅፎ ባቀረበው ክስ ምን ይላል ?

1ኛ. ተከሳሽ አቶ ናትናኤል አምቢኮ በሻሾጎ ወረዳ የፋይናንስ ጽ/ቤት የክፍያ ኦፊሰር፤
2ኛ. ተከሳሽ ወ/ሮ አዳነች ጡምደሎ በሻሾጎ ወረዳ የፋይናንስ ጽ/ቤት የክፍያ ቡድን መሪ፤
3ኛ. ተከሳሽ አቶ ታምራት ኒኔ የሻሾጎ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ (በሌለበት የታየ)፤
4ኛ. ተከሳሽ አቶ ሲሳይ ቢያድጌ በወረዳው በመንግስት ሰራተኛነት ሳይቀጠር ደመወዝ ሲከፈለው የነበረ፤
5ኛ. አቶ ሰላሙ አበጀ በወረዳው በመንግስት ሰራተኛነት ሳይቀጠር ደመወዝ ሲከፈለው የነበረ ሲሆን፤

በሻሾጎ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ላልተቀጠሩ  መምህራን ሰራተኞች በቁጥር 19 ሰዎች ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ እስከ መስከረም 2016 ዓ/ም ድረስ ከ5 ወር እስከ 11 ወራት ደወመዝ እንዲከፈላቸው አድርገዋል።

በዚህም በድምሩ 7 መቶ 30 ሺህ 2 መቶ 39 ብር በመንግስት እና ሕዝብ  ሀብት ላይ ጉዳት አድርሰዋል ፤ ያላግባብ ስልጣንን በመገልገል ወንጀል ፈፅመዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።

የሀድያ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ጉዳዩን ተከታትሏል።

ተከሳሾች የቀረቧቸው የመከላከያ ምስክሮች የዐቃቤ ህግን የሰውና የሰነድ ማስረጃ አስተባብለው ባለመገኘታቸው ፍ/ቤቱ በሙሉ ድምፅ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቶባቸዋል።

በዚሁም መሰረት ፦ 

1ኛ. ተከሳሽ አቶ ናትናኤል አምቢኮ በሻሾጎ ወረዳ የፋይናንስ ጽ/ቤት ፔሮል አዘጋጅ የክፍያ ኦፊሰር በ7 ዓመት ከ8 ወር ፅኑ እስራትና በ5 ሺህ ብር እንዲቀጣ።

2ኛ. ተከሳሽ ወ/ሮ አዳነች ጡምደሎ ኩሪሶ  በሻሾጎ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የክፍያ ሂሳብ ቡድን መሪ በ7 ዓመት ከ8 ወር ፅኑ እስራትና በ 5 ሺህ ብር እንድትቀጣ።

3ኛ. ተከሳሽ አቶ ታምራት ኒኔ የሻሾጎ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ የነበረ እጁን ለህግ አካላት ያልሰጠና በፖሊስ ታድኖ ሲያዝ የእስራት ጊዜውን የሚያጠናቅቅ ሆኖ (በሌለበት የተወሰነ) በ11 ዓመት ፅኑ እስራትና በ 10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ።

4ኛ. ተከሳሽ አቶ ሲሳይ ቢያድጌ በትምህርት ጽ/ቤት ሳይቀጠርና መምህር ሳይሆን ለ9 ወራት ደመወዝ ሲከፈለው የነበረ በ3 ዓመት ፅኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ።

5ኛ. ተከሳሽ አቶ ሰላሙ አበጀ ተባበል በወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ሳይቀጠርና መምህር ሳይሆን ለ 9 ወራት ደመወዝ ሲከፈለው የነበረ በ3 ዓመት ፅኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኖባቸዋል።

መረጃ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ነው የተገኘው።

#CentralEthiopia #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray : " ... ከጦርነቱ በኋላ የተቋቋመው መንግስት ስራውን ለመስራት አቅም ያጣበት ወቅት ላይ እንገኛለን " - አቶ ጌታቸው ረዳ ሀምሌ 25 እና 26/2016 ዓ.ም " የትግራይ ፓለቲካዊ አስተዳደር " በሚል ርእሰ አንድ መድረክ መቐለ ውስጥ ተካሂዶ ነበር። የክልሉ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ተገኝተውም ንግግር አድርገው ነበር። ምን አሉ ? - በትግራይ የሃሳብ ጠቅላይነት ሊኖር አይችልም።…
#Tigray : በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር በተደራጀ ገለልተኛ በተባለ አንድ አጥኚ ቡድን የክልሉን ሁኔታ በተመለከተ ጥናት ተደርጎ ነበር።

በዚህም ፦

በክልሉ ሕገወጥነት መስፈኑ እና ይህም ወደ ስርዓት አልበኝነት የሚሄድበት ዕድል ከፍተኛ መሆኑን ገልጿል።

የመንግሰት መዋቅር በአንድ ፓርቲ መጠለፉን ያመለክታል።

የክልሉ ህዝብ እና መንግስት ሀብት በግለሰቦች ፣ የውጭ ዜጎች ጭምር እየተዘረፈ እንደሆነ ያሳያል።

የፍትህ ስርዓቱ ተአማኒነት ማጣቱን ያመለክታል።

በህዝቡ ዘንድን ተስፋ ማጣትና ስደት መንሰራፋቱ ይኸው ጥናት አሳይቷል።

የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፥ መንግስት ስራው እንዳይሰራ መቸገሩን ገልፀዋል።

የተቃዋሚ ፓርቲ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሊቀመንበር አቶ አሉላ ሃይሉ ፤ " የክልሉ አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ከመስራት ይልቅ፥ ችግሮች በመዘርዘር ተጠምዷል " ብለዋል።

" እኔ እኮ በጣም የሚያሳዝነኝ ነገር በትግራይ ችግሮቹ ተዘርዝረው እየተነገሩ ያሉት፣ ችግሮቹን ሊፈቱ ስልጣን በያዙ ሰዎች ነው። ኃላፊነታችሁ ልትወጡ ይገባል " ሲሉ ለዶቼ ቨለ ተናግረዋል።
#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መምህራን " የአማራ ክልል ከማንም ጋር የሚወዳደር አይደለም ፤ መምህራን ጥይት በላያቸው ላይ እያፏጨ ነው ያስተማሩት " - ማኀበሩ የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር / ኢመማ / በአማራ ክልል የሚገኙ መምህራን ከባድ የሚባል ፈተና ለመጋፈጥ እየተገደዱ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ። ቃሉን ለቲክቫህ የሰጠው ማኀበሩ፣ መምህራኑ በከፋ የጸጥታ ችግር ውስጥ ሆነው እየሰሩ ባለበት እንኳ ደመወዛቸው እየተቆረጠባቸው…
🔈#መምህራን

" ብሔሩ ተቆጥሮ ያልተፈናቀለ መምህር የለም !! " - የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር

በተለያየ ጊዜ በብሔራቸው አማካኝነትያ ከተለያዩ ክልሎች የተፈናቀሉ መምህራን በሥራ አጥነት ሳቢያ የከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር (ኢመማ) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለልጿል።

የማኅበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አበበ በሰጡት ቃል፣ " ትግራይ ክልል ዝግ ሆኖ የቆዬ አካባቢ ነው፡፡ ከዚያ አንጻር የተፈናቀሉ መምህራን አሉ " ብለዋል፡፡

" የአማራ ክልል ተወላጅ የሆኑ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ ሥራ ፈትተው የተቀመጡ መምህራን አሉ። የትግራይ ክልል መምህራን ሆነው ከአማራ ክልል የተፈናቀሉ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ ያሉም አሉ " ሲሉ ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡

" ኮይሃ የሚባል አካባቢም የትግራይ ክልል ተወላጆች ሆነው ግን አፋር ክልል ይሰሩ የነበሩ ተፈናቅለው ሥራ ፈትተው የተቀመጡ መምህራን አሉ " ሲሉ አክለዋል።

" በትግራይ ክልል ይሰሩ የነበሩ የአማራ ክልል ተወላጅ መምህራንም ቢሆኑ ተፈናቅለው ጎንደር የተቀመጡ አሉ " ያሉት አቶ ሽመልስ፣ መምህራን የትም አካባቢ ሂደው መስራት እንዳለባቸው ቢታመንም ችግሮች ግን ጎልተው እየተስተዋሉ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም እንዲሁ ከሶማሌ ክልል ተፈናቅለው ለመውጣት የተገደዱ መምህራን እንደነበሩ አስታውሰው፣ " ብሔሩ ተቆጥሮ ያልተፈናቀለ መምህር የለም " ብለዋል፡፡

" በተለያዩ ጊዜያት ችግራቸው እንዲፈታ፣ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ ለአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሳውቀናል" ሲሉ ማኅበሩ ያደረገውን ጥረት አስረድተዋል፡፡

" ለትግራይ ትምህርት ቢሮ አሳውቀናል፡፡ ትግራይ ክልልም የሰው ኃይል እጥረት አለና ቀጥራችሁ አሰሯቸው የሚል ሃሳብ ነው እያነሳን ያለነው " ብለዋል፡፡

መምህራን ያለምንም ፈቃዳቸው በተለያየ መንገድ ደመወዝ እንደሚቆረጥባቸው ፣ የደረጃ እድገት እየተሰራላቸው እንዳልሆነ ማኅበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#Mesirat

ቢዝነስዎን ለማሳደግ እሄ ወርቃማ እድል እንዳያመልጥዎ! https://mesirat.acceleratorapp.co/application/new?program=mesirat-entrepreneurs-application-form-sixth-cohort ላይ ተመዝግበው
- በፋይናንስ፣
- በማርኬቲንግ፣
- በቴክኖሎጂ፣
- በኔትወርኪንግ፣
- የባለሙያ አማካሪዎችን በማግኘት፣
- በአገልግሎት ሰጪነት እና
- በአማካሪነት ድጋፍ ያግኙ።

የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም አካል ይሁኑና ቢዝነስዎ እንዲያድግ አጠቃላይ ድጋፍን ያግኙ።
ፕሮግራማችን የባለሙያ ምክር ማግኘት፣ ጠቃሚ ግብአቶች እና ተመሳሳይ አስተሳሰብ ካላቸው ስራ ፈጣሪዎች ጋር ንቁ እድገትን ለማፋጠን የተነደፈ ነው።

#መስራት #ስራፈጠራ
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ2017 በጀት አመት 971.2 ቢሊዮን ብር በጀት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ከጸደቀው ገንዘብ ውስጥ ፦ ➡️ 451,307,221,052 ለመደበኛ ወጪዎች ➡️ 283,199,335,412 ለካፒታል ወጪዎች ➡️ 222,694,109,445 ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ ➡️ 14,000,000,000 ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ ነው፡፡ @tikvahethiopia
#Ethiopia

ለ2017 የበጀት አመት ተጨማሪ በጀት በቅርቡ ይጸድቃል።

የዘንድሮ በጀት 1.8 ትሪሊየን ብር እንደሚሆን ይጠበቃል።

ይህ መጠን ባለፈው ሰኔ ወር ለ2017 በጀት አመት ከጸደቀው 971 ቢሊየን ብር አንጻር በእጥፍ የሚጨምር ነው፡፡

ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ መጀመሩን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ የውጭ ድጋፍ ማግኘት የጀመረው መንግስት ለውጡን ተከትሎ ሊፈጠሩ የሚችሉትን ጫናዎችን ለመከላከል የተለያዩ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡

ከነዚህም ውስጥ #ድጎማ እና #የደመወዝ_ጭማሪ የሚጠቀሱ ሲሆን በተጨማሪም ሌሎች ወጪዎች በአመቱ ሊኖሩ እንደሚችሉ ይጠበቃል፡፡

IMF ሰንድ ትንበያ ምን ያሳያል ?

- የመንግስት ወጪ ቀደም ሲል ከጸደቀው 971 ቢሊየን ብር በእጥፍ ሊጨምር ይችላል።

- ይህንን ወጪ ለመሸፈን ከአገር ውስጥ ገቢ 1.3 ትሪሊየን ብር (1.15 ትሪሊየን ብር ከታክስ) 214 ቢሊየን ብር ከውጭ የበጀት ድጋፍ በጥቅሉ 1.52 ትሪሊየን ብር የሚገኝ ይሆናል።

- ከውጭ ከሚገኘው 214 ቢሊየን ብር ብድር እና እርዳታ አምና (2016) ከተገኘው 43 ቢሊየን ብር አንፃር በአምስት እጥፍ (500 በመቶ) ጭማሪ ይኖረዋል።

- ከውጭ ከሚገኘው የበጀት ድጋፍ በተጨማሪም ደግሞ በእርዳታ ተቋማት አማካኝነት የሚፈሰው ሃብት ሲካተትበት በጠቅላላ ወደ 304 ቢሊየን ብር ይደርሳል።

- ወጪ ይደረጋል ተብሎ የሚጠበቀው 1.8 ትሪሊየን ብር ሲሆን የበጀት ጉድለቱ 270 ቢሊየን ብር ይሆናል።

- ከጠቅላላው የመንግስት ወጪ 1.24 ትሪሊየን ብር የመደበኛ ወጪ ይሆናል። ቀሪው 557 ቢሊየን ብር የካፒታል ወጪ ይሆናል፡፡

ሰኔ መጨረሻ ለ2017 በጀት አመት ፀድቆ ከነበረው 971 ቢሊየን ብር በጀት ውስጥ 358.5 ቢሊየን ብር ወይም ከጠቅላላው በጀት 37 በመቶ የሚሆነው የበጀት ጉድለት ነበር፡፡

ሆኖም በIMF ትንበያ ወጪ ይደረጋል ከተባለው 1.8 ትሪሊየን ብር ውስጥ የበጀት ጉድለቱ ከወር በፊት ተቀምጦ ከነበረው መጠን የሚያንስ ነው፡፡

መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።

#Capitalnewspaper #Ethiopia #IMF

@tikvahethiopia
#HawassaUniversity

በህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተለጠፈው ማስታወቂያ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲውስ ምን ምላሽ ሰጠ ?

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲልኩ ነበር።

ለዚህ ቅሬታ መነሻቸውም አንድ ተለጥፎ ያዩት ማስታወቂያ ነው።

ማስተወቂያው ፦

° በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት ተማሪዎች ወደቤት መሄዳቸውን ይጠቁማል።

° የገበያው አለመረጋጋት አቅራቢዎች ላይ በፈጠረው ከፍተኛ ጫና እና በቀን ለ1 ተማሪ የተወሰነው 22 ብር ዕለታዊ ወጪ ጋር ተመጣጣኝ ባለመሆኑ ላልተወሰነ ጊዜ የመግቢያ ቀን መራዘሙን ያሳያል።

° ኢንተርን ሽፕ ላይ ያሉ እና ካፌ ተጠቃሚ የነበሩ እጩ ዶክተሮች በምግብ ምትክ የሚሰጠውን የነን ካፌ ፎግም ሞልተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይላል።

° የተማሪዎች መግቢያ እስኪገለጽ ከቀን 29 /11/ 2016 ዓ/ም ጀምሮ የምግብ እና የመኝታ አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ በመቋረጡ በተለያዩ ምክንያቶች ግቢ ያሉ ተማሪዎች በ4 ቀን ለቀው እንዲወጡ ይላል።

የተማሪዎች ቅሬታስ ምንድነው ?

መልክዕታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ ተማሪዎች ትልቅ ቅሬታ እንዳላቸው ይገልጻሉ።

ቅሬታቸው ፦

- ላለፉት ስምንት ዓመታት ትምህርት ላይ ብንሆንም አሁንም በተለያየ መልኩ ጊዜያችን እየተቃጠለ ነው።
- የመመረቂያ ጊዜያችን አሳሳቢ ሆኗል።
- መግቢያችን ለሁለተኛ ጊዜ መራዘሙ ትክክል አይደለም።
- በኮቪድ-19 ለአስር ወራት እንዲሁም በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት የትምህርት ጊዚያችን ተቃጥሏል። ወሁን የመመረቂያ ጊዚያችን ተራዝሟል።
- በዚህ ዓመት ለ12ኛ ክፍል ፈተና እንድንወጣ ተደርገን ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም ነው የተጠራነው። በኋላም ወደ ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም ተገፋ። አሁን ደግሞ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ሰማን። ይህ ትክክል አይደለም።
- የሚመለከተው አካል መፍትሔ ይስጠን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተማሪዎች ቅሬታን እንዲሁም የተለጠፈውን ማስታወቂያ ይዞ ዩኒቨርሲቲው አለኝ የሚለውን ማብራሪያ ለተማሪ እንዲሰጥ ጠይቋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ  ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ተባባሪ  ፕሮፌሰር አለሙ ጣሚሶ ምን አሉ ?

የቀረበዉ መረጃ ትክክል አይደለም።

ኢንተርን ሀኪሞች ከግቢ አይወጡም። ዶርማቸውንም አይለቁም። ይልቁንም ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርስቲው የምግብ አገልግሎት በመቋረጡ በጀታቸዉን እንዲጠቀሙ ነው የተገለጸው።

ይህ የሆነው አሁን ላይ ለ3 አመት ውል የገቡ ነጋዴዎች በእቃ መወደድ ምክኒያት ምንም አይነት የምግብ ግብአት ሊያቀርቡልን ባለመቻላቸዉና ይህን ችግር  ተወያይተን መፍትሄ እስክንሰጠዉ ነው።

ሌሎች ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት ከተጠናቀቀ በቅርቡ ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሳሉ። ትክክለኛ ቀኑንም  ለተማሪዎች በይፋ ይነገራቸዋል።

ተማሪዎችን አሁን ላይ መቀበል ያልተቻለው ከምግብ አቅርቦትና አንዳንድ ማስተካከያ የሚፈልጉ ጉዳዮች ስላሉ ነው።

በየጊዜዉ ለ12ኛ ክፍል ፈተና ሲባል ከግቢ መውጣታቸውን ሆነ አሁን ላይ በቶሎ አለመግባታቸው የሚወስድባቸውን ጊዜ  ለማካካስ ዩኒቨርሲቲው መፍትሄዎችን አስቀምጧል። በዛ ይሄዳል።

ተማሪውን የሚያደናግር ማስታወቂያ ያወጣዉ አካል ከኛ እውቅና ዉጭ በመሆኑ ማንነቱን አጣርተን እርምጃ የምንወስድ ይሆናል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ሳይንስ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝደንቱ ተማሪ ደረጀ መንገሻ ምን አለ ?

👉 ኢንተርን ዶክተሮች ከግቢ ባለመውጣታቸዉ እስካሁን መጉላላት አልደረሰባቸውም። ማስታወቂያውም ያለኛ እውቅና ነው የተለጠፈው።

👉 ተማሪውን ሳይፈልግ ወደነን ካፌ መቀየር አግባብ ስላልሆነ ለዩኒቨርሲቲዉ አመራሮች ውሳኔዉ ልክ አለመሆኑን የሚገልጽ ደብዳቤ አስገብተን ምላሽ እየጠበቅን ነው።

👉 ተማሪዎች ሐምሌ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ያልገቡበት ምክኒያት ዩኒቨርሲቲዉ ከበጀት ማስተካከያና ካምፓስ ውስጥ ከሚያስተካክላቸው አንዳንድ ነገሮች ጋር በተያያዘ ምክኒያት ነው።

👉 ተማሪዎች በጊዜ ወደ ግቢ ባለመግባታቸው በቀጣይ ተማሪዎች ላይ የሚከሰተዉን ጫና በተመለከተ ዩኒቨርሲቲው እንዲያስብበት ተነጋግረናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

More - @tikvahuniversity

@tikvahethiopia