የኤርትራ መንግሥት 46 እስረኞችን ለቀቀ።
በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።
የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።
እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።
በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።
የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።
የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።
እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።
በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።
የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba
" ... የተኩስ ልውውጡ የነበረው ከሚሊኒየም አዳራች በሰንሻይን በኩል ወደ ቦሌ መድኃኒዓለም በሚያስወጣው መንገድ ነበር " - የአካባቢው ነዋሪዎች
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቦሌ በፖሊስ እና ፋኖ አባላት መካከል የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች አድርጎ ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ወደ ሚያስወጣው መንገድ ላይ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ገልጸዋል።
በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት እና አንድ መንገደኛ ህይወታቸው ጠፍቷል። ሁለት የፖሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፥ " ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ ወቅት እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው " ብለዋል።
" ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።
ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃላቸው ፥ ቦሌ በነበረው የፋኖ አባላቱና እና የፖሊስ ተኩስ ልውውጥ ፦
- ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ #ሞቷል፤
- አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፤
- ሀብታሙ አንዳርጌ የተባለ የፋኖ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር ውሏል።
ከዚህ ባለፈ ፦
° አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ባለመኪና ‘#አልተባበርም’ ስላሉ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ገድለውታል።
° የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታወት በጥይት መተውታል " ሲሉ ተናግረዋል።
በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ በኩል ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
@tikvahethiopia
" ... የተኩስ ልውውጡ የነበረው ከሚሊኒየም አዳራች በሰንሻይን በኩል ወደ ቦሌ መድኃኒዓለም በሚያስወጣው መንገድ ነበር " - የአካባቢው ነዋሪዎች
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቦሌ በፖሊስ እና ፋኖ አባላት መካከል የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች አድርጎ ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ወደ ሚያስወጣው መንገድ ላይ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ገልጸዋል።
በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት እና አንድ መንገደኛ ህይወታቸው ጠፍቷል። ሁለት የፖሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፥ " ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ ወቅት እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው " ብለዋል።
" ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።
ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃላቸው ፥ ቦሌ በነበረው የፋኖ አባላቱና እና የፖሊስ ተኩስ ልውውጥ ፦
- ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ #ሞቷል፤
- አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፤
- ሀብታሙ አንዳርጌ የተባለ የፋኖ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር ውሏል።
ከዚህ ባለፈ ፦
° አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ባለመኪና ‘#አልተባበርም’ ስላሉ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ገድለውታል።
° የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታወት በጥይት መተውታል " ሲሉ ተናግረዋል።
በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ በኩል ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት ታጋዲዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች 20 ቀናት ሆኗታል። ቤተሰቦቿ " ልጃችንን አፋልጉን " ሲሉ በፈጣሪ ስም ተማጽነዋል። መላው ኢትዮጵያ ህዝብ እና የፀጥታ ኃይል ልጃቸውን እንዲፈልግላቸው ጥሪ አቅርበዋል። የታዳጊ ተማሪ ማህሌት ቤተሰቦች ከትግራይ ዓድዋ ከተማ ያስተላለፉት የአፋልጉን የተማፅኖ ጥሪ ምን ይላል ?…
#Update
"...ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን ነው። በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችም አሉ " - የዓድዋ ከተማ ፓሊስ
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ በታጋቿ ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥቷል።
መጋቢት 10/2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታ ዓዲ ማሕለኻ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች 24 ቀናት ተቆጥሯል።
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ዋና አዛዥ ተስፋይ ኣማረ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት መረጃ ፥ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባትን የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችን በቁጥጥር ስር ለመዋል ፓሊስ ጥረት እንያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።
የታዳጊዋ መታገት በማስመልከት በተሰቦችዋ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩ ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው የገለፁት የፓሊስ ዋና አዛዡ ፥ " ' ፓሊስ ለእገታው ትኩረት አልሰጠውም ' ተብሎ በማህበራዊ የትስስር ገፆችና በሚድያዎች የሚሰራጨው መረጃ ልክ አይደለም " ብለዋል።
" ይህን ያህል ከባድ የውንብድና ወንጀል ተፈፅሞ ፓሊስ እንዴት ችላ ይለዋል ? " ሲሉ የጠየቁት ዋና አዛዡ ተስፋይ አማረ ፥ ከከተማው እስከ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን በመቀናጀት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች ለመያዝ ሌት ተቀን እየተሰራ ነው ብለዋል።
" ታዳጊዋን ያገቱ ሰዎች ከእገታው በፊት ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉዋት የቆዩ መሆናቸው ከቤተሰቦችዋ የተገኘ መረጃ ይጠቁማል " ያሉት ዋና አዛዡ ፥ " የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውለናል። ለሚድያ መግለጫ ስላልሰጠን ብቻ ስራችን እየሰራን እንዳልሆነ ተደርጎ መውሰድ አግባብነት የለውም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ በተደጋጋሚ መረጃ ያደረሰ ሲሆን ከቀናት በፊት ቤተሰቦቿ በሰጡት ቃል ፥ አጋቾች ለማስለቀቅያ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፈላቸው በጠየቁበት ዕለት ድምጿን ከሰሙ በኃላ ዳግም እንዳላገኟት እነሱም እንዳልደወሉ ፣በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች እንኳን እንደማያውቁ ፤ በዚህም መላው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቅና ሃዘን ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረው ነበር።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
"...ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን ነው። በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችም አሉ " - የዓድዋ ከተማ ፓሊስ
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ በታጋቿ ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥቷል።
መጋቢት 10/2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታ ዓዲ ማሕለኻ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች 24 ቀናት ተቆጥሯል።
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ዋና አዛዥ ተስፋይ ኣማረ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት መረጃ ፥ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባትን የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችን በቁጥጥር ስር ለመዋል ፓሊስ ጥረት እንያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።
የታዳጊዋ መታገት በማስመልከት በተሰቦችዋ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩ ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው የገለፁት የፓሊስ ዋና አዛዡ ፥ " ' ፓሊስ ለእገታው ትኩረት አልሰጠውም ' ተብሎ በማህበራዊ የትስስር ገፆችና በሚድያዎች የሚሰራጨው መረጃ ልክ አይደለም " ብለዋል።
" ይህን ያህል ከባድ የውንብድና ወንጀል ተፈፅሞ ፓሊስ እንዴት ችላ ይለዋል ? " ሲሉ የጠየቁት ዋና አዛዡ ተስፋይ አማረ ፥ ከከተማው እስከ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን በመቀናጀት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች ለመያዝ ሌት ተቀን እየተሰራ ነው ብለዋል።
" ታዳጊዋን ያገቱ ሰዎች ከእገታው በፊት ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉዋት የቆዩ መሆናቸው ከቤተሰቦችዋ የተገኘ መረጃ ይጠቁማል " ያሉት ዋና አዛዡ ፥ " የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውለናል። ለሚድያ መግለጫ ስላልሰጠን ብቻ ስራችን እየሰራን እንዳልሆነ ተደርጎ መውሰድ አግባብነት የለውም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ በተደጋጋሚ መረጃ ያደረሰ ሲሆን ከቀናት በፊት ቤተሰቦቿ በሰጡት ቃል ፥ አጋቾች ለማስለቀቅያ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፈላቸው በጠየቁበት ዕለት ድምጿን ከሰሙ በኃላ ዳግም እንዳላገኟት እነሱም እንዳልደወሉ ፣በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች እንኳን እንደማያውቁ ፤ በዚህም መላው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቅና ሃዘን ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረው ነበር።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
" በህገ-መንግስቱ መሰረት የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር ወደ ቤታችን መልሱን " - የራያ አለማጣ ተፈናቃዮች
ከትግራይ ደቡባዊ ዞን ወረዳ ራያ አላማጣና አለማጣ ከተማ ተፈናቅለው በመኾኒ ከተማ የመጠለያ ጣብያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 5 /2016 ዓ.ም በተካሄደውና ከመኾኒ ከተማ እስከ ኩኩፍቶ ፣ በሪ ተኽላይ የተባለ ቦታ በሸፈነው የተፈናቃዮቹ ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር!!
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
- ወደ ቄያችን መልሱን !!
... የሚሉና ሌሎች መፈክሮች መሰማታቸውን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ቦታው ድረስ በመደወል ለማረጋገጥ ችሏል።
@tikvahethiopia
ከትግራይ ደቡባዊ ዞን ወረዳ ራያ አላማጣና አለማጣ ከተማ ተፈናቅለው በመኾኒ ከተማ የመጠለያ ጣብያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 5 /2016 ዓ.ም በተካሄደውና ከመኾኒ ከተማ እስከ ኩኩፍቶ ፣ በሪ ተኽላይ የተባለ ቦታ በሸፈነው የተፈናቃዮቹ ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር!!
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
- ወደ ቄያችን መልሱን !!
... የሚሉና ሌሎች መፈክሮች መሰማታቸውን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ቦታው ድረስ በመደወል ለማረጋገጥ ችሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
“ ወደ ትግራይ መልሱን የሚሉ ተፈናቃዮች የሉም ” - የአላመጣና አካባቢው አመራር
ከራያ አላላማጣ ከተማ ተፈናቅለው መሆኒ ከተማ በሚገኝ መጠለያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች፣ ወደ ትግራይ እንዲመለሱ ዛሬ (ሚያዚያ 5 ቀን 2016 ዓ/ም) ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።
የአላማጣ ከተማና የአካባቢው አመራር የዛሬውን ሰልፍ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፣ “ በስም የአላማጣ ተፈናቃይ ከማይጨውና መሆኒ አከባቢ ያሉ የ #TDF አባላትን ሲቪል በማስለበስ ‘ተፈናቃዮች ነን’ ብለው ከመሆኒ ወደ አላማጣ አቅጣጫ ጉዞ በማድረግ ተክላይ በር ድረስ ሰልፍ ወጥተዋል ” ብሏል።
አክለውም፣ “ ሲቪሉ ከተክላይ በር አላለፈም። የታጠቀው ኃይል ግን ከተክላይ በር ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ከሚገኘው ጨጓራ ተራራ በመያዝ ቁልቁል ወደ ኮስምና ታኦ አቅጣጫ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ ይህ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የፕሪቶርያውን ስምምነት የሚጥስ ነው። መከላከያ በሰጠን አቅጣጫ የራያ አላማጣና የአላማጣ ከተማ ህዝብ ወደ ግንባር ከመሄድ ተቆጥቧል ” ብለዋል።
“ ሰልፈኞቹ ከያዙት መፎክር መካከል፦
- የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ይከበር
- የራያ ህዝብ ትግራይ እንጂ አማራ ሁኖ አያውቅም
- የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ የለውም ” የሚል ይገኝበታል ሲሉ ገልጸዋል።
ከአላማጣ ከተማ ተፈናቅለው መሆኒ መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች አሉ ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አመራሩ፣ “ ከራያ አላማጣ ተፈናቅለው የነበሩ በሙሉ ተመልሰዋል። መሆኒ ያሉ ተፈናቃዮች አመራር የነበሩ፣ ወጣት ያሳፈኑ፣ እስከ ሽዋሮቢት ድረስ የዘረፉ #ወንጀለኞች ናቸው ” ብለዋል።
“ ወደ ትግራይ መልሱን የሚሉ የሉም። መሆኒ ውስጥ ያሉ የትግራይ ኢንቨስተሮች የአከባቢው ማህበረሰብ አላሰራ ስላላቸው ወደ መቐለ የሚሸሹ አሉ። ከዚህ ውጭ ሌላ የለም። 100% የተረጋገጠ ነው ” ሲሉ አክለዋል።
በትግራይ በኩል ያሉ ታጣቂዎች ባለፈው በነበረው ባደረጉት ተጨማሪ ትንኮሳ ተቆጣጥረውት ከነበረው "ጨጓራ" ከተሰኘው ቦታ፣ "ኮስም፣ ቡበ፣ ታኦ እና አከባቢው ተቆጣጥረዋል። መከላከያ ኃይል ለመጨመር ከላይ ካሉት አካላት እየተጻጻፈ ነው። በዚህ ሰዓት በርካታ አከባቢዎች ጦርነት ውስጥ ናቸው " ያሉት አመራሩ፣ " እኛ ፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሄድ እንፈልጋለን። ጦርነትን አማራጭ አናደርግም " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከራያ አላላማጣ ከተማ ተፈናቅለው መሆኒ ከተማ በሚገኝ መጠለያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች፣ ወደ ትግራይ እንዲመለሱ ዛሬ (ሚያዚያ 5 ቀን 2016 ዓ/ም) ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።
የአላማጣ ከተማና የአካባቢው አመራር የዛሬውን ሰልፍ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፣ “ በስም የአላማጣ ተፈናቃይ ከማይጨውና መሆኒ አከባቢ ያሉ የ #TDF አባላትን ሲቪል በማስለበስ ‘ተፈናቃዮች ነን’ ብለው ከመሆኒ ወደ አላማጣ አቅጣጫ ጉዞ በማድረግ ተክላይ በር ድረስ ሰልፍ ወጥተዋል ” ብሏል።
አክለውም፣ “ ሲቪሉ ከተክላይ በር አላለፈም። የታጠቀው ኃይል ግን ከተክላይ በር ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ከሚገኘው ጨጓራ ተራራ በመያዝ ቁልቁል ወደ ኮስምና ታኦ አቅጣጫ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ ይህ እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የፕሪቶርያውን ስምምነት የሚጥስ ነው። መከላከያ በሰጠን አቅጣጫ የራያ አላማጣና የአላማጣ ከተማ ህዝብ ወደ ግንባር ከመሄድ ተቆጥቧል ” ብለዋል።
“ ሰልፈኞቹ ከያዙት መፎክር መካከል፦
- የትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ይከበር
- የራያ ህዝብ ትግራይ እንጂ አማራ ሁኖ አያውቅም
- የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄ የለውም ” የሚል ይገኝበታል ሲሉ ገልጸዋል።
ከአላማጣ ከተማ ተፈናቅለው መሆኒ መጠለያ ጣቢያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች አሉ ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አመራሩ፣ “ ከራያ አላማጣ ተፈናቅለው የነበሩ በሙሉ ተመልሰዋል። መሆኒ ያሉ ተፈናቃዮች አመራር የነበሩ፣ ወጣት ያሳፈኑ፣ እስከ ሽዋሮቢት ድረስ የዘረፉ #ወንጀለኞች ናቸው ” ብለዋል።
“ ወደ ትግራይ መልሱን የሚሉ የሉም። መሆኒ ውስጥ ያሉ የትግራይ ኢንቨስተሮች የአከባቢው ማህበረሰብ አላሰራ ስላላቸው ወደ መቐለ የሚሸሹ አሉ። ከዚህ ውጭ ሌላ የለም። 100% የተረጋገጠ ነው ” ሲሉ አክለዋል።
በትግራይ በኩል ያሉ ታጣቂዎች ባለፈው በነበረው ባደረጉት ተጨማሪ ትንኮሳ ተቆጣጥረውት ከነበረው "ጨጓራ" ከተሰኘው ቦታ፣ "ኮስም፣ ቡበ፣ ታኦ እና አከባቢው ተቆጣጥረዋል። መከላከያ ኃይል ለመጨመር ከላይ ካሉት አካላት እየተጻጻፈ ነው። በዚህ ሰዓት በርካታ አከባቢዎች ጦርነት ውስጥ ናቸው " ያሉት አመራሩ፣ " እኛ ፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሄድ እንፈልጋለን። ጦርነትን አማራጭ አናደርግም " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia