TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ኢዜማን ልከስ ነው! Via የጀርመን ራድዮ @tsegabwolde @tikvahethiopia
''ኢዜማ ያለምንም ህጋዊ መሰረት ንብረቶቻችንን እየተጠቀመ ስለሆነ ሊመልስልን ይገባል''- #ኢዴፓ

''በህገወጥ መንገድ የያዝሁት ምንም ንብረት የለም'' - ኢዜማ
.
.
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ /ኢዜማ/ ከኢዴፓ አፈንግጠው በወጡ አራት አባላት የተሰጠውን የፓርቲው ንብረቶች ያለምንም ህጋዊ መሰረት እየተጠቀመ ስለሆነ ሊመልስልን ይገባል ሲል ኢዴፓ ጥሪ አቅርቧል፤ ኢዜማ በበኩሉ በህገወጥ መንገድ የያዝሁት ምንም ንብረት የለም ብሏል፡፡

ከኢዴፓ አፈንግጠው የወጡ አራት ግለሰቦች በምርጫ ቦርድ ፍፁም ህገወጥ የሆነ ትብብር የፓርቲውን ፅህፈት ቤቶች፣ በባንክ የተቀመጠ ገንዘብ፣ መዛግብትና ማህተም ያለአግባብ በህገወጥ መንገድ እንዲረከቡ ተደርጓል ያለው ኢዴፓ ግለሰቦቹ ኢዴፓ ከግንቦት 7 ጋር እንዲዋሀድ የኢዴፓ ጠቅላላ ጉባኤ ተሰብስቦ እንደወሰነ አድርገው የሀሰት መረጃ በማቅረብ ንብረቶቹን በፓርቲዎች ውህደት ሳይሆን በግለሰቦች ስብስብ ለተቋቋመው ኢዜማ ማስረከባቸውን የኢዴፓ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከትናንት በስቲያ በሰጠው መግለጫ ጠቅሷል፡፡

#ኢዜማም ያለምንም ህጋዊ መሰረት እነዚህን የኢዴፓ ንብረቶች እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝ የጠቀሰው ማእከላዊ ኮሚቴው በዚህ የተነሳ የእለት ከእለት ስራዎችን በአግባቡ ለማከናወን መቸገሩን ገልፆ ኢዜማ ግለሰቦቹ የፈፀሙትን #የማጭበርበር ወንጀል ተረድቶ ንብረቶችን እንዲመልስ ጠይቋል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/ET-08-23

@tsegabwolde @tikvahethiopia