TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#CRRSA

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ፤ በጥር ወር አገልግሎትን በገንዘብ በመሸጥ እንዲሁም ሃሰተኛ ሰነድ በማዘጋጀት ላይ የተሰማሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

ኤጀንሲው ፥ በሃሰተኛ ሰነድ ዝግጅት  ላይ የተሰማራ ህገ-ወጥ ደላላ እና አንድ የሌላ ተቋም ሰራተኛ  እንዲሁም ላልተገባ ግለሰብ በገንዘብ አገልግሎት የሰጠ የተቋሙ ሰራተኛ እና ተገልጋዮችን በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉን ነው ገለጸው።

ኤጀንሲው በሰጠን ማብራሪያ ፤ የአቃቂ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 የስራ ዕድል ፈጠራ ጽ/ቤት #ሰራተኛ የሆነ ተጠርጣሪ 30 ሺህ ብር በመቀበል በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 5 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ስም የተዘጋጀ ከጽ/ቤቱ ያልወጣ ሀሰተኛ የነዋሪነት መታወቂያ እና  የጋብቻ ሰርትፍኬት ማዘጋጀቱ ተደርሶበር በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ ፤ በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 8 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ስም የተዘጋጀ ከጽ/ቤቱ ያልወጣ ሀሰተኛ የነዋሪነት መታወቂያ፣ የልደት ሰርተፍኬት እና የመሸኛ ማስረጃ /Clearance / በ10 ሺ ብር  ያዘጋጀውን ግለሰብ ከየካ ከፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጋር በመተባበር በየካ ወረዳ 10  አካባቢ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር አውሎታል።

ኤጀንሲው፤ ከኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በደረሰው ጥቆማ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመቀናጀት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 እና አዲስ ከተማ ወረዳ 9 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት ምዝገባ ጽ/ቤት ሰራተኛ የሆኑ ተጠርጣሪዎች ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ ግለሰቦች የነዋሪነት መታወቂያ እና የልደት ማስረጃ በመስጠታቸው በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ ምርመራ እየተደረገ እንደሚገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

በዚህ ጥር ወር በኤጀንሲው ስነ-ምግባር እና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት በተመራው ክትትል እና ኦፕሬሽን ፦
- ሰባት በተቋሙ ስም የተሰሩ ሃሰተኛ ማስረጃ የያዙ ግለሰቦች፣
- ሶስት የተቋሙ ሰራተኞች ፣
- አንድ የሌላ ተቋም ሰራተኛ እና አንድ በሃሰተኛ ሰነድ ዝግጅት ላይ የተሰማሩ በድምሩ 12 ተጠርጣሪዎች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረግ መቻሉን አሳውቋል።

ኤጀንሲው ፤ " በመዋቅሬ ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ክትትል በማድረግ ከሌብነት የፀዳ ተቋም ለመገንባት ጥረት እያደረኩ ነው " ያለ ሲሆን ህብረተሰቡ  በተቋሙ ስም ከሚያጭበረብሩ ህገ-ወጥ ግለሰቦች እራሱን እንዲጠብቅ አሳስቧል።

" በተቋሙ ጥቂት ሰራተኞች የሚፈፀሙ ህገ-ወጥ ተግባራት በቅንነት እና ታማኝነት የሚያገለግሉ ሰራተኞችንም አይወክልም " ብሎ " በህዝብ የሚታመን አገልጋይ ተቋም ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ነዋሪው አጋዥ እንዲሆን " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
" አንድ የወረዳ ጽ/ቤት አመራር እና አንድ ሰራተኛውን በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርገናል " - የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አንድ የወረዳ ፅ/ቤት አመራር እና አንድ ሰራተኛውን በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉን ገለጸ።

ኤጀንሲው ደረሰኝ ባለው የተገልጋይ ጥቆማ ፦
- የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋዬ አያለው
- የነዋሪ መረጃ፣ ህትመት ስርጭት እና ቁጥጥር ቡድን መሪ አቶ መንግስቱ እጅጉ " በጋራ በመመሳጠር ላለተገባ ሰው አገልግሎትን በገንዘብ ለመሸጥ በ10ሺ ብር ተደራድረው የዲጂታል ምዝገባ በማከናወን ላይ ሳሉ በተደረገው ክትትል እጅ ከፍንጅ ይዘናቸዋል " ብሏል።

የተቋሙ የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ክፍል ከፖሊስ ጋር በመተባበር ላለፉት ሶስት የስራ ቀናት ክትትል ሲያደርግ መቆየቱንና ትላንት በጽ/ቤቱ ውስጥ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉን አመልክቷል።

ተቋሙ በክትትሉ የተደራጁ የድምፅ ቅጂ እና ተጨማሪ ማስረጃዎችን ለፖሊስ ማስረከቡን አሳውቋል።

ነዋሪዎች ከህገ-ወጥ ደላሎች እና አገልግሎትን በገንዘብ ከሚሸጡ ግለሰቦች ራሳቸውን እንዲጠብቁ እራሳቸውም ተባባሪ ከመሆን እንዲቆጠቡ መልዕክት ያስተላለፈው ኤጀንሲው በመሰል ሁኔታዎች በአገልግሎቱ ላይ ሲገጥም በ7533 የነፃ የስልክ መስመር ወይም በፌስቡክ ገፅ በቀጥታ መልዕክት ማስቀመጥ እንደሚቻል አመልክቷል።

#CRRSA

@tikvahethiopia